cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ወርቃማ ንግግሮች

ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና። አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot https://youtube.com/channel/UCgP-E0miz3BhJ0YAGJ2zCHg

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
15 960
المشتركون
+1024 ساعات
+3737 أيام
+31830 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ስሜ ሑርያ ይባላል። የ60 ዓመት የዕድሜ ባለ ጸጋ ነኝ።ሥራ የለኝም። ትምህርቴንም አልጨረስኩም። ቆንጆ አይደለሁም። ከዉበት መዐድ ተቆርሶ የተሰጠኝ በጣሙን ጥቂት ነው። ዕድሜዬ 30 ዓመት እስኪያልፈዉ ድረስ፡ ማንም ለጋብቻ አልጠየቀኝም። አንድ ቀን በድንገት የሰፈራችን የትዳር አገናኝ አሮጊት አናገረችኝ። ለትዳር የሚፈልግሽ ሰዉ አለ።የ33 ዓመት ወጣት ነዉ። ከዚህ በፊት አግብቶ አያዉቅም። ከአባቱ ጋር የግል ኩባንያቸዉ ዉስጥ ነው የሚሰራዉ ብላ ፎቶዉን አሳየችኝ።ሃብታም ናቸዉ። ፎቶዉን አይቼ ደነገጥኩ ።ማሻ አላህ፡ በጣም ቆንጆ ነዉ።ግን እራሴን መጠየቅ ጀመርኩ። ለምን መረጠኝ? ከሁሉም በሁሉም ነገር የበታች ነኝ። ከትምህርት ትምህርት የለምኝ። ከዉበትም ነፃ ነኝ፡ እያልኩ ሳሰላስል፡ የትዳር አገናኟ፡ አንድ ችግር ግን አለበት ብላ፡ ከነበርኩበት አነቃችኝ። ከአምስት ዓመት በፊት የማየት አቅሙን በአደጋ ምክንያት አጥቷል። በተለያየ ግዜያት የቀዶ ህክምና ተደርጎለት አልተሳካም ስትለኝ።ወይ እዳሌ ብዬ ማማረሬን ቀጠልኩ። የትዳር አገናኟ አስቢበት ብላ ጥላኝ ሄደች። ቤተሰቦቼን አማከርኩ። ሁሉም ዝምታን መረጡ። ሴት አያቴ ግን አላህ በዚህ ማየት በተሳነዉ ሰዉ ምክንያት በደስታ ዕንባ ሊያጥለቀልቅሽ አስቦ ይሆናል ፡ እስቲ አግኚዉና አናግሪዉ፡ ከዛ በኋላ ወስኚ አለችኝ። አገኘሁት። ተነጋገርን። ተጫዋች ነው። አንደበተ ርቱዕ። በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ልቤን ተቆጣጠረዉ።በሁለት ወራት ዉስጥ ትዳር መሰረትን። በዕዉነቱ፡ መጀመርያ በብዙ ነገር ምክንያት ሰግቼ ነበረ። አንደኛዉ እራሱ ስለራሱ የዓን ብርሃኑን ከማጣቱ በፊት የነገረኝ ሁሉ በጣም አሳስቦኝ ነበር። አላፊነት ወዉሰድ እንደማይወድ፡ ምሽቱን እንዴት እንደሚያሳልፍ እንደነበረ፡ ከቆነጃጅት ጋር ስለነበረዉ ተሞኩሮ ሲነግረኝ በጣም ሰጋሁ ። ሁለተኛው የስጋት ምንጬ፡ ከሰዉ እገዛ ዉጭ ምንም ማከናወን እንደማይችልና ሸክም እንደሚሆንብኝ ሲነግረኝ ነዉ ፍርሃት ያደረብኝ። ትዳር ዓለም ዉስጥ ስንገባ ያልጠበኩትን አየሁ። እገዛ አይሻም ሁሉንም ነገር እራሱ ነው የሚፈጽመው። ይህም ብቻ ሳይሆን ሁሌም ያግዘኛል። አብረን እናበስላለን፡ አብረን እናጥባለን። ሱቅ እንኳን እንድሄድ አይፈልግም። እንዳልደክምበት።በጣም ሩህሩህ አዛኝ ባል ነው። በፍቅሩ አሳበደኝ። በአስር ዓመታት ዉስጥ 3 ልጆች ወለድን። አንድም ቀን የባልና የአባትነት ድርሻዉን ሳያጓድል አመታት እንደ ደቂቃዎች አለፉ። አንድ ነገር ብቻ ይረብሸኝ ነበር። ዓይኑን በተመለከተ ተስፋ አልቆረጠም። ሐኪም ቤት ይመላለሳል።የዓይን ብርሃኑ ከተመለሰለት ወደ ቀድሞው ባህሬዉ ሊመለስ ይችላል ።ሊጠላኝ ይችላል። ሲያየኝ እደብረዉ ይሆናል እያልኩ። በየግዜው ይሞክራል ግን ዉጤት የለም። የአሁን የቀዶ ህክምና ተሳክቶለት ማየት እንደሚችል ዶክተሩ መርዶዉን አብስሮኛል። ሶስቱን ልጆች ይዤ የተኛበት ክፍል ገባን።ልጆቹ አጠገቡ ቆመዋል። ራቅ ብዬ በሩ አጠገብ ተቀመጥኩ። ፋሻዉ ተነሳለት። ያያል። ማመን አብቅቶታል ። ልጆቹን እያገላበጠ ሳመ። እንዲሁም አባቱንና እናቱን። ክፍሉን መቃኘት ጀመረ። በዓይኑ ፈለገኝ። አየኝ። ጠራኝ። ነይ እንጂ ዉቧ ሙሽራዬ ብሎ ጠራኝ። ነይ እንጂ ቀረብ በይ በደንብ ልይሽ። ከገመትኩት በላይ በጣሙን ቆንጆ ነሽ አለ። እንባዬን መቆጣጠር ተሳነኝ። ስጋቴ ጨመረ።ሄድኩኝ። እጄን እፍፍ አርጎ ሳመኝ። ሰይጣን ስራውን ቀጠለ። ሰዉ ፊት ስለሆነ ነዉ። ዉሸቱን ነዉ። እያልኩኝ እራሴን በራሴ ማናገር የዕለት ተዕለት ስራዬ ሆነ ። ግና ለኔ ያለው ፍቅር እየጨመረ ሄደ አንዲት ቆንጆ ሴት ቀና ብሎ አይቶ አያዉቅም ልቡ ሁሌም ከኔ ጋር ነዉ ። አባትና እና እናቴ አረፉ አባትም እናትም ሆነኝ። ሐዘን ደጃፌ እንዳይደርስ አደረገ። እነሆ 60ኛዉን እድሜዬን ይዣለሁ። አያቴ እንዳለችዉ በደስታ ዕንባ ርሻለሁ። በራሕመቱ። ለናንተም የማይጠግባቹህን የማትጠግቡትን ይስጣቹህ። አሚን በሉ።
إظهار الكل...
40👍 24
😍😄😌😉 🛜    ጀ🛜      መ🛜          ረ  ✅ 🖋ኪታብ ፦ የመልካም ሚስት ባህሪ 🎤አቅራቢ ፦ወንድማችን አቡ ሂበቲላህ ደርሱ የሚተላለፍበት ሊንክ🤪 t.me/tdarna_islam?livestream t.me/tdarna_islam?livestream
إظهار الكل...
ቢድአ(ጭማሪ) ፤ መውሊድ(መወለድ) ሙስሊሞች ባለፉት ዘመናትም ሆነ አሁኑ ዘመን ከካህዲያን ጋር በመመሳሰል ከፈፀሟቸው ጥፋቶች ሁሉ ይበልጥ የጎላው የክርስቲያኖችን ፈለግ በመከተል የሚፈፀሙት የመውሊድን በዓል የማክበር ባህል ነው ። ማህይማንና ሰዎችን ለስህተት የሚዳርጉ ዑለሞች በየአመቱ በወርሃ ረቢ ዓል አወል ከነብዩ መሀመድ የልደት ዕለት ጋር በተያያዘ ይህን በአል ያከብሩታል ። ከፊሎቹ ከመስጊዶች ላይ ÷ ሌሎች ደግሞ በየቦታቸው ወይም ለዚሁ አላማ በተዘጋጁ የተለያዩ ስፍራዎች ሲያከብሩ ይስተዋላሉ ። ተራው ህዝብ ከዚህ በዓል ላይ በስፋት ይሳተፋሉ ። ይህን የሚፈፅሙት #የዒሳን የልደት ቀን በዓል ከሚያደርጉት ክርስቲያኖች ጋር በመመሳሰል ነው ። ይህ መውሊድ በዓል በራሱ ቢድአ ከመሆኑም በላይ ብዙ የሽርክና ሌሎችም ሊወገዙ የሚገቡ ተግባራት ይፈፀሙበታል ። መልእክተኛውን ( ሰ ዐ ወ ) ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ የሚያደርጉ እርሳቸውን መማፀን እና እገዛ መጠየቅን የሚያሰተምሩና ግጥሞች ሙገሳዎች በዕየለቱ ከሚፈፀሙት ውጉዝ አንዱ ነገር ነው ። ❥… ነብዩ ( ሰ ዐ ወ ) ከመጠን በላይ መሞገስና መወደስን አጥብቀው አውግዘዋል> … "ክርስቲያኖች የመርየመን ልጅ ከመጠን በላይ እንዳሞገሱት እናንተም እኔን ከልክ በላይ አታወድሱኝ ። እኔ ባሪያ ነኝ ። የአላህ መልዕክተኛ ባሪያ ብቻ በሉኝ ። = ቡኻሪና… ሙስሊም ከነኝህ የዋህ የበዓሉ አክባሪያን መካከል መልዕክተኛው ( ሰ ዐ ወ) ከበዓሉ ላይ ይገኛሉ የሚል እምነት ያላቸው አይጠፉም ከዚህ በዓል ጋር በተያያዘ የሚፈመው  ሌላው ስህተት በከበሮ አጀብ በጋራ የሚባሉ የሱፍያህ ቢድአ ዚክሮችና ነሽዳዎች ናቸው በሴቶችና በወንዶች መካከልም የመቀላለቀል ሁኔታ ይፈጠራል ። ይህም ለመጥፎ ነገር ምክንያት ይሆናል ። ብልግና እንዲፈፀም በመነሻነት ያገለግላል ። ይህ በዓል ከነኝህ ውግዝ አድራጎቶች የፀዳ ተሰባስቦ በመመገብና ደስታን በመግለፅ ብቻ የተወሰነ ሊሆን ቢችልም እንኳን በዓሉ በራሱ ቢድዓ ነው ። አዲስ የተፈጠረ ነገር ። « አዲስ ነገሮች ሁሉ ቢድአዎች ናቸው ። ቢድአ ሁሉ ደግሞ ጥመት ነው ። » ቀስ በቀስም እያደገ ሄዶ ከሌሎች በዓላት ላይ የሚስተዋለው የተወገዙ ነገሮች ሁሉ የሚፈፀሙበት በዓል ይሆናል ። ይህ በዓል ቢድዓ ያልነው ከቁረአንና ከሐዲስ እንዲሁም ከሰለፉሷሊሂን ከመልካሞቹ ምዕተ አመታተት መሰረት የሌለውና ከሂጅሪያ አራተኛው ምእተ አመት ቡሃላ ፋጢዩን የተሰኙ የሺአ አንጃ ተከታዮች የፈጠሩት በመሆኑ ነው ። ……>ኢማሙ አቡ ሐፍስ ታጁዲን አል ፈሰሐኒ እንዲህ ሲሉፅፈዋል ። "አንዳድ ሰዎች በወርሃ ረቢኤል አወል መወሊድ በሚል ስያሜ በሚጠሩት ቀን መሰብሰባቸው ሸሪአዊ መሰረት አለውን?  በሚለው በርካታ ጥያቄዎች በተደጋጋሚ። ጠያቂዎቹ ለዚህ ጥያቄአው የተብራራ ምላሽ ይሻሉ ። በአላህ እገዛ ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል ። ለዚህ የመውሊድ በዓል ከቁረአንም ከሐዲስም መሰረት አላገኘሁለትም ። የቀደምቶችን ፈለግ ከሚከቱሉና በአርአያነታቸው ከሚጠቀሱ ኡለሞች መካከል ይህን በዓል ያከበረ አንድም ሰው አናውቅም ። በዓሉ መጥፎ ሰዎች የፈጠረት ቢድዓ ለሆዳቸው ያደሩ ወገኖች የሚጠቀሙበት የግል ስሜት ፍሬ ነው ። • • • #በኢስላም ስም ፈጠራ ( ቢድአን ) የማስፋፋት አደጋ ↩ የኢስላም ህግጋት የሚመነጩት ከቁረአን ከነብዩ ሙሐመድ ( ሰ ዐ ወ ) ንግግር ሃዲስ ብቻ ነው ። በሃይማኖት ውስጥ ቢድአ ( ፈጠራ )ማለት በሃይማኖት ላይ የሌለን ነገር መጨመር ወይም መቀነስ ማለት ነው ። « ፈጣራም ሁሉ ጥመት ነው ፣ ጥመትም ሁሉ የእሳት ነው ። »  አህመድና ሌሎችም ዘግበውታል " የእኛ ትእዛዝ የሌለበት ( የሃይማኖት ) ተግባር የፈጠረ ተመላሽ ይሆንበታናል " ማለትም ተቀባይነት አይኖረውም  = ሙስሊም ዘግበውታል አላህ ሙስሊሞች እርስበርሳቸው እንዳይከፋፈሉ አዟል ። ሙስሊሞች በሃይማይኖት እና በአምልኮ ተግባራት ላይ የሚያካሂዷቸው ፈጠራዎች እና መከፋፈሎች በኢስላም እንደ ብክለት ፣ ስህተት እና ማፈገንጥ ይቆጠራል ። ( ሆኖም በሌሎች የህይወት ዘርፎች ለምሳሌ በሳይስና ቴክኖሌጂ የሚካሄዱ የሰው ልጅ ህይወትን የሚለውጡ ፈጠራዎች በኢስላም በእጅጉ ይበረታታል ) ።     ቀደም ባለ ዘመናት የተካሄዱ ፈጣሪን ከመገዛት እምነት የማፈንገጥ ተግባራት የአላህን ውግዛት እና ውድመት አሰከትለው አልፈዋል ። ምሳሌ እናንሳ አንድ ሰው አላህን በጣሙን አጥብቄ እገዛለሁና ዙሁርን አምስት አድርጌ ልስገድ ይላል ይህ አሁን ቢድአ ነው ። እሺ ይህ ሰው ሰገደ እንበልና የሰውየውልጅ አባቱ ሲሰግድ አይቶ አምስት ይሰግዳል ። ልጁም ሲሰግድ ሲሰግድ አሁንም ልጁ ዙህሪን ስድስት ረከአ አድርጌ እሰግዳለሁ ይላል ። እያለ እያለ በዲን ላይ ጭማሪው በዛ የኋላው ትውልድ ኢስላምን ይበርዙታል። ብዙ ማለት ይቻል ነበር… • • ኢስላም ምንም ጭማሪም ሆነ ቅናሽ የሚያስፈልገው እምነት አይደለም ሀቢቡና ሙሀመድ በሳቸው ላይ ሰላትና ሰላም ይውረድና ሽንት ቤት ሲገቡ የሚባል ዚክር እንኳን ሳይቀር አስተምረውን አልፈዋል ። እጅግ አሰዛኝ የሆነው አላህ በነብዩ ሙሐመድ  እድሜ መጨረሻ አካባቢ በወረደው የቁረአን አንቀጽ የኢስላም እምነትን እንዳሟላልን ገልፇል  አላህ አዘወጀል እንዲህ ይላል الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكُمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا ۚ ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለናንተ ሞላሁላችሁ፡፡ ጸጋዬንም በናንተ ላይ ፈጸምኩ፡፡ ለእናንተም ኢስላምን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ፡፡                             ሱረቱ አል-ማኢዳህ - { ³ } በአምልኮ ተግባራት ላይ የሚካሄድ ማንኛውም ለውጥ በጥብቅ የተከለከለ ነው ። በሸይጧን ተጽዕኖ ስር የሆነውን የሰው ልጅ የሚያደርገው ለውጥ አሏህ ምሉእና ፍፁም አድርጎ ያወረደውን የእስልምና እምነት ከማቆሸሽ ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም ። ኢስላም ላይ የሚተገበሩ ፈጠራዎች ሁሉ ቀጥተኛውን መንገድ ያሰረታሉ ። ቀጥተኛውን መንገድ መሳት ደግሞ ለጀሀነም ያደረረጋል ። ሙስሊሞች የዚህ አይነት ፈጠራ ( መጨመር ሆነ መቀነስ ) የብናኝ ያህል ቢሆን እንኳን ሲፈፀም በቸልታ ማለፍ የለባቸውም ። ፈጠራዎች በቸልታ ከታላፈ በሚቀጥሉት ትውልዶች እንደ መደበኛ የዒበዳ ተግባራት ተደርገው በመወሰድ አሏህ ምሉእ አድርጎ ካወረደው ኢስላም ውጭ የሆነ ሰው ሰራሽ ሁሉ ሃይማኖት የመፍጠር አደጋ ለደቀኑ ይችለሉ ። በዒባዳ ተግባራት ላይ ከተገኝበት ሁሉ የመቃረን ወይም የሃይማኖት አባቶችን በጭፍን የመከተል አዝማሚያ በኢስላም ተቀባይት የለውም ። የአሏህ ህጎችን መቀየር በኢስላም የተከለከለ ነው ። አሏህ መለኮታዊ መመሪያዎች የሚለውጡ የሃይማኒት መሪዎችን አውግዟል ። እነዚህ መመሪያዎችን ለመለወጥ የሞከረ ሰው ራሱን ከአሏህ ለማስተካከል  እና ባእድ አምልኮ ፈፅሟል ። የአላህ ህግጋት ፍፁም ስለሆነ ምንም ዓይነት ዝመና አያስፈልጋቸውም ። አሏህ የእሱን እምነት በመከተል የመታዘዝ አሊያም የራሳችንን ስሜት በመከተል ያለመታዘዝ ሙሉ ነፃነት ሰጥቶናል ። ሆኖም የእርሱ መመሪያዎች ላይ ፈጠራን በመጨመር መቀየርን አልፈቀደልንም ።
إظهار الكل...
👍 11 4
Photo unavailableShow in Telegram
🍂 ⇛ የአላህ መልእክተኛ (ሰ ዐ ወ) እንዲህ ብለዋል… ~ ከመካከላችሁ አፀያፊ ተግባር ሲተገበር ያስተዋለ ሰው በእጁ ያስወግደው። ካልቻለ በምላሳ። ካልቻለ በቀልቡ ይጥላ። [ሙስሊም]
إظهار الكل...
👍 23
💡ጥያቄ❓ ✍ ከሚከተሉት መካከል የአላህን እርግማን የሚያስከትለው የቱ ነው ❔ ➦ትክክለኛው መልስ ስታገኙ ተጨማሪ ጥቆማ ያገኛሉ✈️ 👇
إظهار الكل...
👍 5
ሀ// ወላጆችን መራገም
ለ// የመሬት ይዞታን ምልክት መቀየር
ሐ// ከአላህ ውጭ ላለ አካል የሚያርድን
መ// ሸሪአዊ ቅጣት ብይን  የተወሰነበትን ሰው ያስጠጋ
ሠ// ሁሉም መልስ ነው
ረ// መልስ የለም
Photo unavailableShow in Telegram
🍂 ~ የሰው ልጅ የህይወትን አጭርነት የሚረዳው ማለቂያዋ ላይ ሲደርስ ብቻ ነው። (መሐመድ አልገዛሊ)
إظهار الكل...
17👍 5
Photo unavailableShow in Telegram
~ 🌺 ከአንተ ቡሃላ የዱኒያ ሁኔታ ለመመልከት ከፈለግክ ከሌላው ሰው ሞት በኋላ የሆነውን ነገር መመልከት ነው። (ረዋዒዑን ሚነል ፊከር)
إظهار الكل...
👍 12 7
~ የገንዘብ በረከት አቡ ሓሚድ አል-ገዛሊይ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- ‹አንዲት ብር ትባረክና ለአንድ ሰው በዚህች ምድርም ሆነ በሃይማኖቱ ደስተኛ ይሆን ዘንድ ምክንያት ልትሆንለት ትችላለች፡፡ በርካታ ሺህ ገንዘቦችን ደግሞ አላህ ከውስጣቸው በረከትን ያነሳና ለባለቤቱ መጥፋት ምክንያት ልትሆን ትችላለች፡፡ የገንዘቡ ባለቤት ምነው ባልኖረኝ ይላል፡፡ በአንዳንድ ነገሮች ውስጥም ድህነትን እስከመመኘት ይደርሳል፡፡› አቡ ዳዉድ እንደዘገቡት አስማእ ቢንት አቢበከር (ረ.ዐ.) እጁ ላጠረና ገንዘብ ለሌለው ሰው ስለመመጽወት የአላህን መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ጠየቀች፡፡ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያለው ገንዘብ ዙበይር ለጥሎሽ የሰጠኝ ብቻ ነው፡፡ ከዚሁ ገንዘብ ብሰጠው ይቻላልን› አለቻቸው፡፡ እርሣቸውም ‹ስጪ አትቋጥሪ፤ አላህ ይቋጥርብሻል (አይሰጥሽም)› አሏት፡፡ ትርጉሙ… ያለሽን ሰስተሸ አታስቀምጪ፡፡ በእጅሽ ያለውን አትከልክይ፡፡ ሲሳይ ሊቋረጥብሽ ይችላልና፡፡ በሌላ ዘገባ ደግሞ አትቁጠሪ አላህ ይቆጥርብሻል› ብለዋታል፡፡ ይህ ውድ የሆነ ሥነምግባር በበጎ አናጭ የሆነ ምክር ነው፡፡ የዚህን ዓይነቱን ጥልቅ እና ምርጥ ምክር ሊመክር የሚችለው የነፍስን የውስጥ ሁኔታ እና የሸይጣን መግቢያ የሁለት ዓለም ጀነት መንገዶች የሚያውቅ ብልህ ሰው ብቻ ነው፡፡ ትርጉሙም የምትሠጪውን ነገር አትቁጠሪ፣ መቁጠሩ እና እንዲህ እንዲህ ሰጥቻለሁ ብሎ መመዝገቡ ከሸይጣን ድብቅ ወጥመድ ላይ ይጥልሻል፡፡ የሰጠሽው ነገር ብዙ እንደሆነ አድርጎ ያቀርብልሻል ፣ ያታልልሻል፡፡ አንቺ ግን የሰጠሽው ነገር ትንሽ ሆኖ ሳለ ያጃጅልሻል፡፡ በዚህም የተነሳ ብዙ የሰጠሸ መስሎሽ በሂደት እስከመከልከል ሁሉ ትደርሺያለሽ፡፡ መመፅወት ታቆሚያለሽ፡፡ የከለከልሽ እንደሆነ ደግሞ አላህም ስጦታውን ይከለክልሻል አይሰጥሽም፡፡ ሰው በሥራው ነውና የሚመነዳው፡፡ የባሪያ እና የንጉስ፣ የፈጣሪ እና የፍጡራን ምርመራ እና ሚዛንና መለኪያው የተለያየ ነው፡፡ አስማእ በየቀኑ እየመፀወተች ገንዘቧ አለማለቁ የገረማት ይመስላል፡፡ በዚህም እጅግ ተደነቀችና የቀረው ምን ያህል እንደሆነ ለማወቅ ጣረች፡፡ ሰዎች ሁሉ እንዲሁ ነው የሚያደርጉት፡፡ በዚህን ጊዜ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) አትቁጠሪ አሏት፡፡ የዚህ ዓይነቱ ቆጠራ በረከትን ይነሳልና፡፡ የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ዱዓእ በረከት
إظهار الكل...
👍 22 11
ብልትን መንካት ውዱእ ያፈርሳልን? ~ ብልትን መንካት ውዱእ ያፈርሳል ወይስ አያፈርስም የሚለውን በተመለከተ ከዑለማዎች የተለያዩ ሃሳቦች ተሰንዝረዋል። የልዩነቱ መነሻ ሁለት የተለያየ የሚመስል ይዘት ያላቸው ሐዲሦች መኖራቸው ነው። እነሱም፦ ▶️ በአንድ በኩል ከቡስራ ቢንት ሶፍዋን ረዲየላሁ ዐንሃ የተላለፈው "ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ያድርግ" የሚለው ሐዲሥ ሲሆን ▶️ ሌላኛው ደግሞ ከጦልቅ ብኑ ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁ የተላለፈው "በሶላት ውስጥ ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ማድረግ አለበትን?" ተብለው ሲጠየቁ ነብዩ (ﷺ) "የራስህ ቁራጭ አካል ነውኮ" ብለው መመለሳቸው ነው። * ሁለቱም ሐዲሦች ከሰነድ አንፃር ትክክለኛ (ሶሒሕ) ናቸው። ታዲያ የቱን ይዘን የቱን እንተው? ዑለማዎች በዚህ ጉዳይ ላይ የተለያዩ አቋሞችን አንፀባርቀዋል፦ 1⃣ኛ አቋም፡- የቡስራን ሐዲሥ ይዘው "ብልትን መንካት ውዱእ ያፈርሳል" ያሉ አሉ። 2⃣ኛ አቋም፡- የጦልቅን ሐዲሥ ይዘው ''የለም ብልትን መንካት ከነጭራሹ ውዱእ አያበላሽም" ያሉ አሉ። * "ውዱእ ያፈርሳል" የሚለው የመጀመሪያው አቋም "የራስህ አካል ነውኮ" የሚለውን ሐዲሥ ያለ በቂ ምክንያት ስለሚገፋ ልክ አይደለም። * "አያፈርስም" የሚለው 2ኛው አቋም "ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ያድርግ" የሚለውን ሐዲሥ በሚገፋ መልኩ ከተተረጎመ ትክክል አይሆንም። "አንዱ ሐዲሥ ሌላኛውን ሽሮታል" በማለት መግፋት ደግሞ አጥጋቢ መረጃ ያስፈልጋል። መረጃ ደግሞ የለም። "ይሄኛው ሐዲሥ የቀደመ ነው፤ ያኛው የዘገየ ነው" የሚለው ሙግት ብቻውን በቂ አይደለም። ያለ ተጨባጭ መነሻ፣ ያውም ሁለቱ ሐዲሦች የሚጣጣሙበት አቅጣጫ እያለ አንዱን ሐዲሥ ይዘን ሌላኛውን ልንገፋ አይገባም። እና እንዴት ይሁን? ወደ ሌላኛው የዑለማዎች እይታ ይወስደናል፦ 3⃣ኛ አቋም፡- "ብልትን በመንካት ውዱእ የሚጠፋው በስሜት ከሆነ ነው። ካልሆነ ግን ውዱእ አይጠፋም'' በሚል ሁለቱን ሐዲሦች ሊያጣጥሙ የሞከሩ አሉ። አንዱን ሐዲሥ ይዘው ሌላኛውን ከሚጥሉት የመጀመሪያዎቹ አቋሞች አንፃር ሲታይ ይሄኛው የተሻለ ነው። ነገር ግን "በስሜት" እና "ያለ ስሜት" ብሎ ለመክፈል ግልፅ መረጃ የለም። በዚህ የተነሳ ይሄኛውም ድምዳሜ አጥጋቢ አይሆንም። ስለዚህ ሁለቱ ሐዲሦች ተጣጥመው የሚሄዱበት ሌላ የዑለማእ ምርጫ ማየት ሊኖርብን ነው። ይሄውና፦ 4⃣ኛው አቋም፡- የሁለቱ ሐዲሦች መልእክት የሚጋጭ አይደለም የሚል ነው። "የራስህ ቁራጭ አካል ነውኮ" የሚለው ብልትን መንካት ውዱእ እንደማያጠፋ ሲገልፅ፤ በሌላ በኩል "ብልቱን የነካ ሰው ውዱእ ያድርግ" የሚለው ሐዲሥ ደግሞ ብልቱን ለነካ ሰው ውዱእ ማድረጉ እንደሚወደድ ይጠቁማል። ትእዛዝ አዘሉን መልእክት ከግዴታነት ወደ 'ሙስተሐብነት' ያወረደው "የራስህ አካል ነውኮ" የሚለው ሐዲሥ ነው። በዚህ መልኩ ሁለቱን ሐዲሦች አጣጥሞ መረዳት የተሻለው ምርጫ ነው። ይሄ የኢብኑ ተይሚያ አቋም ነው። ስለዚህ በስሜትም ሆነ ያለ ስሜት፣ የራስንም ሆነ የሌላን፣ የህፃንንም ሆነ የአዋቂን ብልት መንካት ውዱእ አያበላሽም የሚለው ይበልጥ ጠንካራ ምርጫ ነው ማለት ነው። ግዴታ አይሁን እንጂ ታዲያ ውዱእ ማድረጉ ተወዳጅ ነው። ነገር ግን በስሜት ነክቶ ፈሳሽ (መዝይ) ከወጣ ያኔ ውዱኡ ይፈርሳል። በዚህን ጊዜ ብልትን አጥቦ ውዱእ ማድረግ ግዴታ ይሆናል። ወላሁ አዕለም። = ኢብኑ ሙነወር (ጥር 04/2014)
إظهار الكل...
👍 18 2
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.