cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ወግ ብቻ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch@zefenbicha Creator @leul_mekonnen1

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
18 867
المشتركون
-824 ساعات
-607 أيام
-24530 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የሄደበትን የመጨረሻ ቀን አስባለሁ። ኩራቱን ተገፎ ሀፍረትን ተከናንቦ እርቃኑን እንደቆመ ሠው ዐይኔን ሽሽት አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬት እያየ "እሜትዬ በድዬሻለሁ…" ያለበትን ቃና እሰማለሁ። ምህረት ፍለጋ ለይቅርታ አልመጣም ነበር። አንዳንድ ሀጥያቶች ስርየት የላቸውም፤ ስለአንዳንድ በደሎቻችን ከራሳችንም እርቅ አይኖረንም። ለዋለው ክህደት ይቅርን አልፈለገምና የኔ ይቅር ማለት ትርጉም አልነበረውም። የኔ ምህረት መስጠት ኩራትና ክብሩን ከወደቀበት ሊያነሳለት አቅም አልነበረውም። አንገቱን ደፍቶ በገባበት በር አንገቱን ደፍቶ ሲወጣ ቃል አልወጣኝም። አልተከተልኩትም በዐይኔ አልሸኘሁትም። ልቤ መመለሱን ቢሻ ከበደሉ ሊያልቀው ግን አልተቻለውም። በሰው ለውጦሻል ተይው ይሂድ አለ፡፡ ተውኩት፣ ሄደ…አልተመለሠም ። ዘመናቶቼ መኸል ግን እጠብቀው ነበር። አንዱን ቀን ይመጣል ብዬ በር በሩን አማትሬያለሁ። ወሬውን ፍለጋ ጆሮዎቼ እልፍ ጊዜ ቆመው የደጁን ድምፅ ሲቃርሙ ኖረዋል። ብዙ ጠብቀዋል፤ ለማንም ሳልነግር በደሉን ውጫለሁ። ባሻዬ ከዳኝ ሳልል ይቅር ብዬ ነበር። ፍለጋ ባልወጣ የት ሄደ ባልል በልቤ በእየዕለቱ 'አንተ ትሻላለህ፤ ተመለስ ግድ የለም' እል ነበር። እወደው ነበር፤ ኩራት በሸበበው ፈገግታ ቢደበቅም ቅሉ ሳየው ልቤ የፈካ ቀለምን ትፈነጥቅ ነበር። እንደነዛ የመጀመሪያ ቀናት ጠጁን እየተጎነጨ ጓዳውን ሲያማትር በዐይኑ ሲፈልገኝ ትንሿ ልቤ በመጋረጃ ተከልላ እያየች ትደልቅ እንደነበረው፤ እንዲያ…እንዲያ እወደው ነበር። እነዛ ጊዜ ሸምኗቸው ጋቢ ሆነው የለበሳቸው የጥጥ ማጎች ስለሱ እያሠብኩ ሳሾራቸው፤ ተበጥሰው እንደተንከባለሉ ስንት ወድቀው ስንት እንደተነሱ፤ ስንት እንዝርት እንደሰበሩ አያውቅም፤ አልነገርኩትም ለፍቅር ሰነፍ ነበርኩ ። By Beza Wit @wegoch @wegoch @paappii
إظهار الكل...
9👍 6🔥 3
< "እናርግ" አለኝ እኮ፣ ያ ውሻ > ምናለበት እሺ ብትዪው ? ምትወጂው ከሆነ ስሜቱ ለጋራ ነው ፣ አይደለም እንዴ? < አንተ ሐይሚን አርገሀታል? ንገረኝ። > "አድርገሀታል" ማለት? ምን አደረኳት? " < ሒይ ! እያወክ አትገግም። > "በድተሀታል ወይ ? ማለት ፈልገሽ ከሆነ ፣ በድቻታለሁ። ብድትድት ነው ያረኳት። ካንቺ ጓደኞች ያልበዳሁት የለም። " < እህ ? ውሻ! ውሻ ነህ ።> አዎ ነኝ ! ዉው ዉው ኣዉዉዉዉዉ ። ሀያትንም በድቻታለሁ። ሀያት ነች ያስተዋወቀችን። ሀያት የጥቁር ቆንጆ ፣ እንደ እሳት ቅልብልብ ፈጣን ውልብልብ እጅግ ብልህና በትምህርትም ጎበዝ ተማሪ የነበረች ናት። ኤለመንተሪ ከሀያት ጋር ስንማር ጥያቄ ና መልስ ውድድር እኔና እሷ ከፍላችንን እየወከልን ዞረናል። ሀይስኩል እንደገባን ሀያት ናት ከዚህችኛዋ አለም ጋር ያስተዋወቀችን። ከአስረኛ ክፍል በሁዋላ ሀያት የት እንደገባች አናውቅም። እኔና አለም ግን አስር አመት ሆነን። በጓደኝነት። ንፁህ የሚባለው አይነት ጓደኝነት። *_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_* አለም < ወዬ > " አለም የሚል ስም ይዘሽ እንዴት መንፈሳዊት አማኝ ሆንሽ ? " < አንተማ ለይቶልሀል። > ሁሌም ከፍቅረኞቿ ምትለያየው የወሲብ ጥያቄ ሲያቀርቡላት ነው። እሷ "ከጋብቻ በሁዋላ" ትላቸዋለች። እነሱ ጥለዋት ሲሄዱ መጥታ እኔ ላይ ታለቅስብኛለች። ይበዳኛል ብላ ሰግታ አታውቅም። እኔ ብበዳሽስ ? እላታለሁ። ሁሌም < ሐይሚን አርገሀታል? እስካሁን ስንት ሴት አወጣህ? > ትለኛለች። "ስንቷን ሴት ስንት ስንት ጊዜ እንዳወጣሁ ልንገርሽ ? ሐይሚን ...ሐያትን ደሞ እእእ ?" < ኡህ! አንተስ ባልገሀል > ትለኛለች። *_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_* በስጋ እናትም አባትም። ቤተሰቦቿ አሳዳጊዎቿ ናቸው። እና እኛ። እኛ ማለት እኔና ሌላ ማላውቃቸው ጓደኞቿ። < አንተ ቤተሰብ ስላለህ እድለኛ ነህ > ትለኛለች። " እኔ ቤተሰብ እዳ ነው " እላታለሁ። *_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_* ያኔ ሐያት ከእሷ ጋር ካስተዋወቀችን ማግስት ወደኔ ክላስ እየተጎተተች መጣች። ፀይም ነበረች ግን አመዳም። ፀጉሯ ረጅም ነው፣ ግን ደረቅ ነው። ጥቁር ሻርፕ አንገቷ ላይ ጣል ታደርጋለች ፣ ለምን እንደምታደርግ አይገባኝም። እናም ያግባባን ብቸኛ ነገር እኔ ብልህ እንደሆንኩ ማሠቧ ና እሷ ብርቱ ስለሆነች ከእሷ ጋር እንደምስማማ ስለምታስብ ነው። እኔስ ? እኔ ትምህርት ላይ እየቀነስኩ አሪፍ መስሎ መታየት ላይ እየበረታሁ ነበረ። ቀንደኛ ቀልደኛ ሚባሉት ተማሪዎችን ጎራ ተቀላቀልኩ። ሁሉም ጓደኞቼ ድንግል ሆነው ሳሉ ቀድሜ ገርልፍሬንድ ያዝኩ፣ ቆንጆ ሴት፣ ከሌላ ክፍል፣ ሐይማኖትን ። በርግጥ ኤለመንተሪ እያለሁ የሔርሜላን አንገት ስሜያለሁ። ከነሱ መፍጠኔ ለእኔ አይገርመኝም። እና ይህቺ አለም < ትምሕርትህ ይበጅሀል። እሷን ተዋት። ገና ልጅ ነህ። ደግሞም ቆንጆ አይደለችም።> ትለኝ ነበረ። ግን ሁለታችንም በእድሜ እኩያሞች ነን። እሷን መካሪ እኔን ተመካሪ ያደረገን እሷን ለይቶ የመከራት ኑሮ ነው። ኑሮ ያስተማራትን ትምህርት በደንብ ይዛዋለች። ፈተናውንም አልፋዋለች። አሁን ዘናጭ ነች። ፀይም መልኳም ፀጉሯም ወዝ ኖሮታል። ለስራ ሌላ ሀገር የሄደች ጊዜ ገንዘብ እኔ አበድራት ነበረ። ሁለት ጊዜ ሌባ ሙልጭ አድርጎ ዘርፏታል። አሁን እኔ ገንዘብ ሲቸግረኝ ከእሷ ነው የምበደረው። የወር ገቢዋ ከእኔ የወር ደመወዝ አስር እጥፍ ነው። *_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_* አስረኛ ክፍል ተዋወቅን ፣ አስር አመት አብረን አሳለፍን ። አሁን ልታገባ ነው። ሰርጓ በቅርብ ነው። <አንተ መቼ ነው ምታገባው ? > ብዙ ፍቅረኞች አሉኝ ። የቷን ላግባ? < ባለጌ ሐይሚን አሁን ብታገኛትስ ? > አስር አመት ሙሉ ሐይሚን ያልረሳሻት ለምንድን ነው ? < ሐይሚን አይደለም ያልረሳሁት። ያንን የግቢውን ቆንጆ፣ ብልህና ትንሽዬ ልጅን ልረሳው ያልቻልኩት። የአስራስድስት አመቱን ያንን ናሁ መሆን እፈልግ ነበር። አሁን ላይ ግን እዚህ ሆነን ደግሜ እሱ ራሱን ሆኖ ማየት እመኛለሁ > " እመኚኝ። እኔ ምንም ከስሬ አላውቅም። እናም የራሴን መንገድ አገኛለሁ። ሚስትም አገባለሁ። አንቺ ትንሽ ቀደም ብለሽ ሒጂ። አግቢ። እኔ ባንቺ መንገድ አልሄድምና። መልካም መንገድ። መልካም ጋብቻ። ለባልሽ የምነግረው ነገር አለኝ ፦ " እሷን እቅፌ ላይ ለብዙ ቀን እንዳሳደርኳትና ከእሷ ገላ ላይ የወሰድኩት ምንም ነገር እንደሌለ ነው። ስላልፈለኩ። ወይ ፈልጌ ስላልቻልኩ። ወይ ችዬም ታማኝ ሆኜ ይሆናል። እኔ ባለቤቷ ነኝ። አሁን አንተ ባሏ ልትሆን ነው። ይትባረክ" By Nahu senay @wegoch @wegoch @paappii
إظهار الكل...
👍 30🤔 11🥰 7👎 4😁 4🔥 2😱 2 1
«ካባዬ» (ከለእርቃን ሩብ ጉዳይ መፅሐፍ) ክፍል አንድ ------------ ይሄንን ኮንዶሚኒየም ቤት ለማግኘት ከሦስት ወር በላይ ተንከራትቻለሁ። ኪራይ ነው። ዛሬ ዛሬ አዲስአበባ ላይ ፍላጎትንም፣ አቅምንም አጣጥሞ የሚገኝ የኪራይ ቤት ማግኘት ሕልም ነው። እኔ ደግሞ የብር ችግር እንደሌለበት ሰው ስመርጥ ዐይን የለኝም። ሀብታም ስላልሆንኩ ጠባብ ቤት መኖር ይፈረድብኝ፣ ግን ጠባብም የተግማማም መሆን አለበት? የለበትም። ለዚህ ነው ይህንን አራተኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ በጣም ጠባብ ግን ንጹህና ሰላማዊ ስቱዲዮ ኮንዶሚኒየምለማግኘት ሦስት ወራት የፈጀብኝ። ከንጽሕናው ፀጥታው፣ አራተኛ ፎቅ ጥግ ላይ ክትት ብሎ መገኘቱ ማረከኝና ተከራየሁት። ግን ይሄ ታሪክ ስለ ተከራየሁት ስቱዲዮ ኮንዶሚኒየም አይደለም። ስለንጽሕናውና ስለፀጥታውም አይደለም። ስለሰፈሩ ከተማ መሀል መገኘትም አይደለም። ስለ አዲሷ ጎረቤቴ እትዬ እማዋይሽ ነው። ታኅሳስ ላይ ቤቱን ቀለም አስቀብቼ፣ እቃዎቼን ሸክፌ ገባሁ። በገባሁ ዕለት ነው እትዬ እማዋይሽን ያገኘኋት እና የተዋወቅኳት። ቅዳሜ ነበር። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዐት ይሆናል። እሷ፣ ፎቁን እያረፈች እንደወጣች በሚያስታውቅ ሁኔታ ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለና እያለከለከች በሬ አጠገብ የሚገኘው በሯ ጋር የቤቷን ቁልፍ እያንቀጫቀጨች ስትደርስ፣ እኔ ደግሞ ውስጥ ያለውን እስካስተካክል ውጪ የተውኳቸውን ኮተቶቼን ወደ ቤት ለማስገባት ስወጣ ነው፣ ፊት ለፊት የተገጣጠምነው። እንዳየኋት የተሰማኝ ነገር ያለቦታዋ የምትገኝ ሰው መምሰሏ ነበር። በዕድሜ ስልሳ ቤት ትሆናለች። ነገር ግን ሙሉ በሙሉ የሸበተው ጸጉሯ ብዙ ጊዜ ዕድሜያቸው የሄደ ሰዎች ላይ እንደማየው ስስና እንክብካቤ ያጣ አልነበረም። ዘንፋላና በሥነ-ሥርአት የተተኮሰ ነበር። አለባበሷ አሁንም በእሷ ዕድሜ ያሉ ሴቶች እንደሚዘወትሩት ሰፊ ልብስ ላይ ሌላ ሰፊ ልብስ፣ ግራጫ ቀለም ላይ ቡናማ፣ ወፍራም ሹራብ ላይ ወፍራም የአንገት ልብስ ዓይነት አልነበረም። ደልደል ያለና ውብ ሰውነት አላት። በልኳ ግን ሳይጠብ የተሰፋ ቆንጆና ደማቅ ቢጫ ቀሚስ፣ አጠር ካለ ሰማያዊ ክፍት ሹራብ ጋር ለብሳለች። ተረከዙ አጭር፣ ፊቱ ሹል ጥቁር ጫማ አድርጋለች። የምታምር ትንሽዬ ቡናማ ቦርሳ አንግታለች። ደርባባ ነች። ዘንጣለች። “እንዴት ዋልሽ ልጄ?” ስትለኝ ነው ዕድሜዋን ከዝነጣዋ ያስታረቅኩት። “ደህና ይመስገን” አልኩኝ ፈጠን ብዬ። “ጎረቤትሽ ነኝ… እንኳን ደህና መጣሽ… እማዋይሽ እባላለሁ” “አመሰግናለሁ… ኤደን እባላለሁ” መለስኩላት። “ሳናግዝሽ ገባሽ… አሁን ምን ልርዳሽ?” አለች ዐይኖቿን ተመሳቅለው የተኮለኮሉት ውጪ የተዘረገፉ እቃዎች ላይ አሳርፋ። “ግዴለም ብዙ አይደለም ጨርሻለሁ” አልኩ አሁንም ፈጥን ብዬ። “በይ ስትረጋጊ ቤቴ ነይና ቡና ጠጪ” አፈር አልኩና፣ “አይ…. እሱ እንኳን ሌላ ቀን” አልኩ። እያግደረደረችኝ ከሆነ መግደርደሬ ነበር። “ኖንሴንስ… እያግደረደርኩሽ አይደለም… ጎረቤት መተዋወቅ አለበት። ቡና ማፍላቴ ስለማይቀር እቃሽን ቦታ ቦታ አስይዢና እንጠጣለን” አሁን ጥያቄ አልነበረም። ትልቅ ሰውም ስለሆነች፣ ጥያቄም ስላልነበር ምርጫ አጥቼ እሺ አልኳት። ዐሥራ አንድ ሰዐት ገደማ ላይ የብረት በሬ ተንኳኳች። እማዋይሽ ነበረች። “ነያ ቡናው ደርሷል” አለችኝ። በሬን ቆልፌ ተከትያት ቤቷ ገባሁ። ቤቷ፣ አዲስ በተቆላ የቡና ጠረንና ለአፍንጫ በሚጥም ዕጣን ጭስ ተጨናንቃ ተቀበለችኝ። ረከቦትና ስኒዎቹን በዐይኔ ብፈልግ የሉም። ዕጣን ማጨሻውን ለማግኘት ብሞክር አልቻልኩም። ከመቀመጤ፣ “ዛሬ ገብተሽ መቼስ ምግብ አልሠራሽም” ብላ ምን የመሰለ ፍርፍር አበላችኝ። ጎንደር ያለችውን ባለሙያ እናቴን አስታወሰኝ። (ይቀጥላል) By Hiwot Emishaw @wegoch @wegoch @paappii
إظهار الكل...
👍 27 18🔥 2🥰 1
USDT ( ዶላር ) የሚከፍሉ ኤርድሮፕ ናቸው። Start ካላችሁ በኋላ ታስኮችን ስሩ ኢንቫይት አድርጉ የሰበሰባችሁትን ነጥብ ወደ USDT Swap አድርጋችሁ Withdraw ማድረግ ትችላላችሁ 👇👇👇 1, https://t.me/major/start?startapp=397965184 2, https://t.me/blum/app?startapp=ref_RqjqTLkZw4
إظهار الكل...
😁 7👍 4 1
ሌሶቶ በዝግታ የሚራመዱ ሰዎች ሃገር (Kingdom of the mountains ይላሉ ራሳቸውን ሲያቆላምጡ) ከፍ ካለ ተራራማ ሃገር ስለመጣሁ "Kingdom of the slow walkers" እላቸዋለሁ እኔ ደግሞ። ማሴሩ ተራሮች መሃል የከተመች ከተማ ። ፀጥ ያለች የተረጋጋች ወከባ የማይታይባት። እግረኞቿና አሽከርካሪዎቿ ብንሮጥም የትም አንደርስም የሚሉ ይመስላሉ። በጠራራ ፀሃይ ብርድልብስ እና ቦት ያደረገ በግ ነጂ ከጂፕ ነጂ ጋር የሚተላለፍባት፣ ደረቅ፣ ነፋሻማና ቀዝቃዛ (መዘዞ፣ መሃል ሜዳ ወዘተን የምታስታውስ)፣ ሁሉንም ሱቆቿን 12 ሰአት ላይ ዘግታ ወደ ቤቷ የምትከተት፣ በአንዱ የተራራ ጫፍ ትልቅ ነጭ መስቀል የሰቀለች፣ በዚህም አዲግራትን የምታስታውስ። ባገሬ መስከረም መጋቢትን የመሰለ ደረቅ ወቅት ላይ ተገኘሁ። እዚህ የክፍል ማሞቂያ 25 ላይ ይደረጋል ከቅዝቃዜ ለመሸሽ (እንደ ኳታር ባለ ሃገር ደግሞ ማቀዝቀዣ 25 ላይ የሚደረገው ከውጪው ሙቀት ለመሸሽ ነው።) 2800 ሜትር አናት ላይ አድጌ 1600 ሜትራቸውን ማድነቅ አልቻልኩም። በመጓዝ ብዛት የገባኝ ተራራ ለብዙ የአፍሪካ ሃገራት ብርቅ መሆኑ ነው /ደብረሲናን፣ ደሴን፣ አሰላን፣ አርሲ ቀርሳን፣ አዲስአበባን ላየ ሰው ማሴሩ የጉብታ ከተማ ነው/። የዚህ ሃገር ሰዎች ንጉሳቸውን ይወድዳሉ። ወይም የሚወዱ ይመስላሉ። ከባድ ባለስልጣን የተባለው ብርድልብስ ለብሶ ስብሰባ ሊመጣ ይችላል። ሁሉም በሚባል ሁኔታ ክብ ባርኔጣ ያደርጋሉ። ዶላር ወደ ሌሶቶ ሎቲ መቀየር ፈልገን ካረፍንበት ሆቴል ፊትለፊት ወዳለ ካፌ ነገር መሩን። ሃበሾች ተሰብስበው ያወራሉ። የካፌውም ባለቤት፣ ዶላር ቀያሪውም የኛው ሰዎች ናቸው። ባልተለመደ ሁኔታ እዚህ የሚኖረው ሃበሻ አብዛኛው Expat ነው። የ አፍሪካ ህብረት፣ የ UN ሰራተኛ ወይንም በፕሮጀክቶች የተቀጠረ ሃኪምና ኢንጂነር። " አንድ የሃበሻ ሬስቶራንት አለ ለበአል እዚያ እንወስዳችኋለን" አሉን። ድሮ ድሮ የበአል መንገድ ያማርረኝ ነበርና አንድ ቀን እናቴን "መንገድ አማረረኝ የበአል ሰሞን ልቅርና በአዘቦት ቀን እየመጣሁ ልጠይቅሽ?" አልኳት። መለሰች " ስንት በአል የምናከብር ይመስልሃል ከዚህ በኋላ? ስሞት ትቀራለህ አትቸኩል።" ዛሬ የአደይ አበባ፣ የበአል ግርግር፣ የመስከረም ምልክት አንዱም በማይታይበት ከተማ ሆኜ ንግግሯን አስታወስኩ። እንቁጣጣሽ ሲያመልጠኝ ሁለተኛዬ ነው (የዛሬ አመት በጦርነት ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ፣ ዘንድሮ በስራ)። ስንት እንቁጣጣሽ እንደቀረኝ ባላውቅም፣ ለኔ ለራሴ የበአል ጉጉቱ ባይኖረኝም ከቤተሰቤ ጋር(ከምወዳቸውም ሁሉ ጋር) የሚኖረኝ ጊዜ የተገደበ ነውና አለመገኘቴ አስደበረኝ። የመንገዱ ሰልፍና ምሬት፣ የበአል ገበያ፣ የበአል ዘፈኖች፣ የእናቴንና እህቴን ቤት ውስጥ ወዲያ ወዲህ ማለት፣ የአባቴን ደጁን ለእርድ ማስተካከል፣ የወንድሜን ለቅዳሴ ለመሄድ መዘጋጀት፣ አልፌ የምሄድባቸውን አረንጓዴና አበባ የለበሱ ሜዳዎችና ተራሮች እናፍቃለሁ። ከቤተክርስቲያን መልስ ስለምንበላው ጥብስ፣ ከፋዘር ጋር ተጋግዘን ስለምንገፈው በግ፣ በደምብ ስለማላውቃቸው ጎረቤቶች፣ ስለ ብዙ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች፣ ስለ ድፎ ዳቦ፣ ስለ ቡና አስባለሁ። እዚህ ያለው ቡና በጣም ቢቀጥንብኝ ከኢትዮጲያ መሆኔን አውቃ "ሰላም ነው?" ያለችኝን አስተናጋጅ ፈልጌ ጠራሁ። "This coffee is too weak I need somthing strong" "Our coffee is not like yours". የጀበና እጣቢ የሚመስል ነገር እየጠጣሁ አለሁ። ሆድ ለባሰው .... ከበአል ድባብ ያላመለጠኝ ብቸኛ ነገር የፌስቡክ ፖስትና የቴሌግራም ስቶሪ ነውና .... ሁላችሁንም እንኳን አደረሳችሁ። መልካም አዲስ አመት። ወንድማችሁ ነኝ ከጉብታዎች አናት ማሴሩ። By haileleul Aph @wegoch @wegoch @paappii
إظهار الكل...
27👍 18😢 3🔥 1🥰 1
"ትንሽ ቦታ" ስሜታዊ ሆኖ ለተናገረን ፣ ሊረዳን ፈልጎ ለሳተ ፣ ኑሮ አስክሮት ለገፋን ፣ ንዴት ገፍቶት ላጠፋ ፣ ግዜ አጣሁ ብሎ ላልጎበኘን ፣ ስናሸንፍ ላላጨበጨበ፣ ስንወድቅ ላላነሳን ፣ ስናስብለት ላልተረዳን ፣ ማደጋችንን ላላየ ፦ "ትንሽ ቦታ ለይቅርታ" አኑረናል አማረልን ብለን ላሳዘንን ፣ አጉል ተስፋ ለሰጠነው ፣ ውድቀት ላይ ለሳቅነው ፣ ብልግናን ላጎላናው ፣ ድድብናን ላነፈስነው ፣ ማድረግ ችለን ላላደረግነው ፣ ችለን ለተጣመምነው ። ለራሳችን ይቅርታ አደርገናል... ቺርስ ለአዲስ ዘመን ቺርስ ለተስፋችን ቺርስ❤🙏. By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii
إظهار الكل...
67👍 20🔥 3👏 2
ብ-ት-ን-ት-ን ----------------------- ወላጆቼና አያቴ የጎረቤቶቻቸው ቤት ዘወትር በቦምብ እየተደበደበ፣ ጥይት እንደ ወፍ በጣራቸው ላይ እየበረረ ከዚህ ቦታ ሽሹ ብላቸውም አንገታችን ይታረዳል አሉ፡፡ ይሄ የወንድማማቾች ጦርነት ከተጀመረ አንስቶ ነጋ ጠባ ቀብር ላይ ናቸው፡፡ ባለፉት ጥቂት ወራት ማህበርተኞቻቸውን፣ አብሮ አደጎቻቸውን፣ ጎረቤቶቻቸውን፣ ዘመድ ወዳጆቻቸውን በየተራ፣ በሰልፍ ቀብረዋል፡፡  ትላንት ማታ ራሱ ወይዘሮ ታየች- የእማዬ የሴት ማህበር አጣጭ፣ የስንት ዘመን ባልንጀራና የታናሽ እህቴ የክርስትና እናት በሯ ላይ ተገድላ ተገኘች፡፡  ተባራሪ ጥይት ነው አሉ፡፡ ‹‹በፈጠራችሁ ተለመኑኝ! አሁንም ከዚህ ሳይብስ ከዚህ እንሂድ›› ብዬ ተለማመጥኳቸው፡፡ ዛሬ ልመናዬ ውሃ ቢያነሳ ብዬ የደብራችንን ቄስ ለምኜ ይዤ መጥቻለሁ፡፡ አጠገቤ ቆመዋል፡፡ ካልሄድን ብዬ ልማለድ ስመጣ ይሄ አራተኛዬ ጊዜዬ ነው፡፡ ብዙ ሳትርቅ የምትገኘው ከተማ ውስጥ አነስተኛ አንድ ክፍል ቤት ተከራይቼ እኖራለሁ፡፡ ደልቃቃ ቤት አይደለችም ግን ቢያንስ ከጦር ሜዳው ሩቅ ናት፡፡ ‹‹ልጄ! ቤታችን እዚህ ነው፡፡ ቀያችን ይሄ ነው፡፡ የት ነው ጥለነው የምንሄደው…?ለማን ጥለነው ነው የምንሄደው…? ጎጇችን ምን ይሆናል…እንስሶቻችንስ ማን ይይዝልናል?››  ብለው እንደ ሁልጊዜው አፍ አፌን አሉኝ፡፡ ቄሱ እምብዛም አላገዙኝም፡፡ ‘አረ እባክዎ እርዱኝ ! ›› ብዬ ብጠይቃቸው ይባስ ብለው፤ ‹‹ተያቸው በቃ!  እንደ ፈቀዳቸው ይሁኑ፡፡ እዚሁ ይቆዩ›› አሉ፡፡ ‹‹አባ! እዚህ ቆይተው ይሙቱ ነው የሚሉት?›› ብዬ እንደ መጮህ አደረገኝ፡፡ እማዬ አፍታም ሳትቆይ ቄሱን ልቆጣ በመድፈሬ ክፉኛ ተቆጣችኝ፡፡ ወዲያው ደግሞ ሁሉ ነገር ሰላም ይመስል ራት ሰርታ አብልታን ‹‹በይ አንቺ ነገ በጠዋት ወደ ሃገርሽ…ነገር ሳይጋጋል›› አለችኝ፡፡ እኔ እንድሄድ ይፈልጋሉ፡፡ እኔ እንዳልጎዳ ይፈልጋሉ፡፡ የአብዛኞቹ ከመንደሩ ወጥተው ከተማ የሚገኙ እኩዮቼ እጣ ፈንታ እንደሚደርሰኝ አውቀው ነበር፡፡ አንዱን ቀን ተደውሎ ቤታችሁ ጋዬ፣ እናት አባትሽ፣ አያትሽ ተገደሉ እንደምባል አውቀው ነበር፡፡ የእኔም ቤተሰቦች ተራ አሃዝ እንደሚሆኑ ልቦናዬ ያውቀው ነበር፡፡ ለመጨረሻ ልመናዬ ከመጣሁ ሳምንት እንኳን ሳይሞላኝ እንደማይቀርልኝ ያወቅሁትን መርዶ ተረዳሁ፡፡  ቤታችሁ በመትረየስ ተመቷል አሉኝ፡፡ እናትሽም.፣ አባትሽም፣ አያትሽም ሞተዋል አሉኝ፡፡ ከቀናት  ለቅሶ በኋላ ነገር ተረጋግቷል ሲባል እኔና ታላቅ ወንድሜ አውቶቢስ ይዘን ወደ ድሮ ቤታችን ተጓዝን፡፡ አይ ቤታችን እቴ! ቤታችን ወደነበረበት ባዶ ሜዳ ብል ይቀላል፡፡ ማልቀሱንስ ሳለቅስ ነው የከረምኩት፡፡ ነገር ግን እማዬ አባዬ እንደነገሩ አጣጥሮላት እንደ ጭስ ቤት የምትጠቀምበት ቦታ ላይ ያ የምወደውን ምስር ወጥ የምትሰራበት ሸክላ ድስት ብትንትን ብሎ ሳየው ግን ለአባባይ እስካስቸግር ማንባት ጀመርኩ፡፡ እኔ ልበታተንልሽ አባዬ፡፡  እኔ ብትንትን ልበል የኔ ዓለም፡፡ @wegoch @wegoch @paappii By Hiwot emishaw
إظهار الكل...
😢 62👍 11
‹‹አልተበላሸም›› ÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷ 1989 ዓ.ም. አስራ ስድስት ዓመቷ ነበር፡፡ የአስረኛ ክፍል ተማሪ ነበረች፡፡ ድርስ ነፍሠ ጡር ነበረች፡፡ የልጇ አባት (የልጅሽ አባት ሲባል ደስ አይላትም፡፡ ያስረገዘኝ  ወንድ በሉ ትላለች) የሰባት ወር ቦይፍሬንዷ ነበር፡፡ ማርገዟን እንደሰማ ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያፈቀረችው ወንድ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የሳማት፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰውነቷን የሰጠችው፡፡  ከብዙ ማባበል በኋላ ስትለምደውና ስትወደው በአንዱ ቀን እንዲህ አላት፤ ‹‹አጎቴ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት እዚሁ ቤላ ጋር ነው፡፡ ለስራ ሐረር ሲሄድ ቁልፍ ሰጥቶኛል፡፡ ለምን እዚያ ሄደን በነጻነት ስናወራ አንውልም?›› ‹‹አጎቴ ቤት ልወስድሽና ድንግልናሽን ልወሰደው ›› የሚል ወንድ የለ መቼስ፡፡  እጁን ይዛ ተከተለችው፡፡  የአጎቱ አንድ ክፍል ቤት በአግባቡ ከተነጠፈ ፍራሽ፣ ከብዙ መፅሐፍትና ከትልቅ ቴፕና አጠገቡ ከተዘረገፉ ካሴቶች በስተቀር ዐይን የሚገባ ነገር አልነበራትም፡፡ ፍራሹ ላይ አደላድሎ እንዳስቀመጣት ሰንደል ለኮሰ፡፡ ‹‹ዘና እንድንል ነው፡፡ በዚያ ላይ ቤቱ ተዘግቶ ስለዋለ ይናፈስ ብዬ ነው›› ብሎ፡፡  ‹‹ሰንደል በየት ሃገር ነው የታፈነ ቤት የሚያናፍሰው..?ይልቅ ለምን መስኮቷን አትከፍታትም?›› አላለችውም፡፡ ‹‹አጎቴ ሙዚቃ በሃይል ይወዳል፡፡ የወጣ ካሴት አያመልጠውም፡፡ ቆይ ሰሞኑን የወጣ የፍቅራዲስ ካሴት አለ፡፡ እሱን ልክፈተው ለሙድ›› አላት ቀጥሎ፡፡ ለሙድ፡፡ ምንም አላለችውም፡፡ ከዚያ…. ፍቅርአዲስ ቤቱን በአስረቅራቂ ድምፅዋ ስትሞላው የእሱ ከንፈሮች አንገቷ ላይ ነበሩ፡፡ ሰላማዊት ተነክታ የማታውቀው ቦታ ስትነካ ፍቅርአዲስ አትርሳኝ እያለች በሚያባብል ድምፅዋ ታለቃቅስ ነበር፡፡ ፍቅርአዲስ ፣ ‹‹ሄደሃል አሉ ብዙ ርቀህ እንደኔ ሆነህ አንተም ናፍቀህ ምናለ ሆዴ ብትመጣልኝ ብታስብልኝ››  ብላ ስትለማመጥ ‹‹እንዲመችሽ ጃኬትሽን አውልቂው›› ብሎ እየተለማመጣት ነበር፡፡ በስልምልም ዐይኖቹ ሲለማመናት፣ በምትወደው ድምፁ ሲያባብላት ታዘዘችለት፡፡ በዚያ ላይ ቀኑን ሙሉ እህል አልበላችም ነበር፡፡ ከምሳ በፊት አስፎርፏት ስትወጣ ምሳቃዋን ረስታ፡፡ ሲገቡ ከሱቅ ካስመጣላት ሙቅ ሚሪንዳ በቀር ሆዷ ባዶ ነበር፡፡  እንደማቅለሽለሽ እያላት ነበር፡፡ እስከዛሬ ድረስ ሙቅ ለስላሳ አልጠጣም ብላ ስትከላከል ብዙ ሰዎች ‹‹ብርድ አይደል…ምን ማለትሽ ነው?›› ሲሏት አታብራራም፡፡ ግን ካልቀዘቀዘ ለስላሳ፣ በተለይ ሚሪንዳ አትነካም፡፡ እስከዛሬ ድረስ ፍቅርአዲስን ስትሰማ ዐይኖቿ በእምባ ይሞላሉ፡፡  ምን ሆንሽ ብሎ የሚጠይቃት ሲኖር መልሷ አንድ ነው፡፡ ‹‹ድምጽዋ ደስ ስለሚለኝ ነው›› ግን ውሸቷን ነው፡፡ ፍቅርአዲስ በአትርሳኝ ሙዚቃ አጃቢነት በአንዲት ቀን አስረግዞ የረሳት የመጀመሪያ ቦይፍሬንዷን ስለምታስታውሳት ነው፡፡ ድምፅዋ ሃዘን የሃዘን በረዶ ያወርድባታል፡፡ ከሶስት ወራት በኋላ የኮከበ ፅባህን ግምብ ተደግፈው እያወሩ ‹‹አርግዣለሁ›› ስትለው አመዱ የጨሰው ሳሙኤል ብን ብሎ ጠፋ፡፡ ምስጢረኛ ጓደኞቿ ‹‹ድሮስ ከቅምቢቢት ዱርዬ ምን ይጠበቃል?›› ብለው አብረዋት አለቀሱ፡፡ አማራጭ ስላልነበራት ቤት ሄዳ የሆነችውን ስትናገር አባቷ ያለችውን የሰሙበትን ጆሯቸውን ማስቆረጥ ቢችሉ ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እናቷም ከአንግዲህ ዐይኔ እንዳያይሽ አለቻት፡፡ ልብሷን ሸክፋ ወደ ብቸኛ መሸሸጊያዋ - ወደምትወዳት አክስቷ- ከመሄዷ በፊት ግን እናቷ ለሚቀጥሉት ሃያ አመታት ላትዘነጋው የወሰነችውን ነገር ተናገረቻት፡፡ ‹‹ሕይወትሽን ጨርሰሽ አበላሽተሽዋል፡፡ ከእንግዲህ የትም አትደርሺም›› ብላ፡፡ እርግዝናዋ የኮከበጽባህ ትምህርት ቤት ርእሰ ሃሜት ሆኖ ቢከርምም በአክስቷ ፍቅርና ማበረታቻ ተደግፋ አስረኛ ክፍልን ከገፋ ሆዷ ጋር አገባደደችና ሰኔ 12/1989 ልጇን ወለደች፡፡ ሚካኤሏ አለቻት፡፡ የሰኔ ሚካኤል ልጅ ስለሆነች፡፡ አክስቷ ጥላ፣ አክስቷ ግድግዳና ማገር ሆናላት ሚካኤላን ከልጆቿ ጋር ስታሳድግላት መራር የእናቷን የእርግማን ቃል እንደምታመክን ቃል አስገብታት ነበር፡፡ ‹‹ዛሬ ተሳስተሻል ማለት እስከወዲያኛው ሕይወትሽ ተበላሽቷል ማለት አይደለም፡፡ ይሄን እውነት ኖረሽ ካሳየሽኝ ልፋቴን ካስሽው ማለት ነው›› ብላ  የልጅነትእኩያ ልጇን ከጎኗ፣ የሰላማዊትን ጨቅላ በእቅፏ አድርጋ ስትመክራት ጉልበት ሆናት ነበር፡፡ ጥር 2016 የአርባ አራት ዐመቷ ሰላማዊት ከሃያ ስድስት ዐመት እኩያ ልጇ ሚካኤሏ ጋር እስክስታ ትወርዳለች፡፡ የሚካኤሏ ሰርግ ነው፡፡ በቅርበት የማያውቃቸው ሰው ሁሉ ደጋግሞ እንዲህ ይላል፡፡ ቀልዳችሁን ነው…እናቷ ልትሆን አትችልም፡፡ ታናሽ እህቷ ናት! አይሆንም! እውይ ደስ ሲሉ! ታድለው! ትንሽ ቆይቶ፣ ጭፈራው አድክሟት በሚዜና አጃቢዎቿ ታጅባ ከአዲሱ ባሏ ጋር የምትጨፍረውን ሙሽራ ልጇን እያየች ቁጭ ያለችው የሙሽሪት እናት ሙቅ ሚሪንዳዋን እየጠጣች ለራሷ- ‹‹ምንም የተበላሸ ነገር የለም፡፡ ሁሉም ነገር ግሩም ነው›› አለችና፤ ወዲያው በሰዎች ምርጫ ሙዚቃ ወደሚያጫውተው ዲጄ ለመሄድ ወሰነች፡፡ ‹‹የፍቅርአዲስ ዘፈን ይኖረው ይሆን?›› ብላ እያሰበች፡፡ By Hiwot Emishaw @wegoch @wegoch @paappii
إظهار الكل...
79👍 32🔥 7😢 5
"እማዬኮ ሔዱ" . . ባውሮፕላን ሔዱ። ጎረቤቶቻቸው አዋጥተው በአውሮፕላን አበረሯቸው። ፎቶ እንኳ እንደሌለን ያወቅኩት ሲሔዱ ነበር። ሙሉ ጊቢውን ጠየቅኩ ማንም የለውም። "ሳላገኘው ልሔድ ነው?" እያሉ ሳለ ትናንት ከአዲስ አበባ መጣሁ። "እማዬ ማናቸው?" የዩቲዩብ ትምህርቶቼን የሚከታተል ድምጻቸውን ሳይሰማ አይቀርም። .. "ለምን ሔዱ?" . ምክንያታቸውን ሲናገሩ... "ደከመኝ! የሽንት ውሀ ማንጠልጠል እያቃተኝ መጣ" " ደጁ ላይ አስቀምጡልኝ ብለው አላቀብሎትም ያለ ሰው አለ? መሔድ ደስ ካላሎት ለምን አይቀሩም ?" 🥺 " ላዬ ላይ ሲያመልጠኝስ? ምን ታደርጋላችሁ?" . እማዬ ለምን በዚህ መሆን ፈለጉ? . 1. ሀሜት አለ። አራት አመት ገደማ ሆኗቸዋል ድሬዳዋ ከገቡ። የወሎ ሰው ናቸው። ተመልሶ ወደ ልጆቻቸው መሔድ ደስ አላላቸውም። ስጋ እንደ ባዳ እንደማይደላ ደመነፍሳቸው ነግሯቸዋል። ዘመድ ስጋን እንጂ ስነልቦናን አይረዳም። . ባዳ መሀል ሀሜት አለ። ሀሜትኮ ንሰሀ ነው አይምሮን ያጸዳል። ቅርጥፍ አድርጎ ማማት ያልቻለ ሰው paranoid የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። በአጭሩ ሀሜት #የአይምሮ_ሰገራ ይመስላል። ቆሻሻ ነው ግን መውጣት አለበት ልክ እንደ አር። አማናዊው ሰገራ በባለቤቱ ግፊት በምጥ ይወጣል! የአይምሮ ሰገራ ለማውጣት ግን #ባዳ ይፈልጋል። . #ባል ባዳ ነው። ለዛ ነው ሚስቱን #የሚበዳው። ባዳው ባል ከሚስቴ ጋር ይሕ #ስጋዬ ነው ይህ #ስራዬ ነው #ሳይል በሀሜት ከተንበለበለ አይምሮው ጤነኛ ይሆናል! ረጅም ይኖራል። "ሴትንኳ ስራዋ ነው" 🤭 አላልኩም ስርአት!!! ሚስትም ከጎረቤት ማማት ትታ ከባሏ ጋር በማማት ከተባበረች #እባብ ፈጣሪን የሚያሳማው ባዳ አያገኝም። .. 2. ትዕዛዝ አለ። . ዘመድ እንደባዳ እርጅናን አያከብርም። አሮጊቷን አንቺ ሲል ያቀረበ ይመስላል። ፍቅር ክብርን የሚበልጥ የሚመስለው ይኖራል። በፍቅር እንደልብ መታዘዝ የለም በክብር እንጂ። አልገባንም ከምናፈቅረው ለምናከብረው እንታዘዛለን። ከእናት በላይ ለአባት እንደማለት። . የምናፈቅረው ላይ የምናከብረው ነገር ከተገኘ አቤት መታደላችን። . #እማዬ ይከበራሉ። #ደም ለማየት ወራት የቀሯትን የደረሰች ልጅ ሲልኩ በሞገስ ነበር። ማንም የእርጅና ዘውዳቸውን እያየ ይታዘዝላቸዋል። ምናልባትምኮ ልጅቱን ከ 20 ሜትር የጠሯት አንድ እርምጃ ርቀት ላይ ያለች ከሰል እንድታቀብላቸው ነው። ፊቷን ቅጭም እንዳደረገች አቤት ሳትል ታቀብላቸዋለች። እግረመንገድ ለሚያወሯት ዝብዛብ አትመልስም! አቀብላቸው ስትመለስ እየተጉመጠመጠች ነው። "አንቺ አስቀያሚ ስለምወድሽ ነውኮ!" ምናምን ይላሉ። "ኧረ ጎረመሰች" ይላሉ። ሌላ ትእዛዝ እንዳይደግሟት እየጸለየች አጎንብሳ ትፈተለካለች። የልጅ ልጃቸው ብትሆንስ?😁 (አንድ የልጅነት ጓደኛዬ አጨባሽ አያቱ በመላክ አማረውት "ጂፓሱ ሸርተት ብሎ በወደቀባቸው" ይለኝ ነበር) . . 3. ሰላምታ ያገኛሉ። ኦኦ እማዬ ሰላምታ ነፍሳቸው ነው። ማንም ሰላም ሳይል አያመልጣትም! በጊቢው 12 ተከራይ አለ። ከአንዱ ቤት ቢያንስ 2 ሰላምታ አያጡም። ሀያአራት ደና አደርክ እና ደና አመሸህ። አንዳንዴም እድል ከቀናም ስምንት ደናእደሩ ይደርሳቸዋል። . በሳቸው እድሜ ይሔ ቀላል ሀብት እንይመስልህ። ደሞ ትንሽ ስኳርና ሌላም በሽታ አላቸው/አለባቸው። ስለዚህ በትንሹ ሁለት ረዘም አድርጎ ጤናቸውን ጠያቂ ይገኛል። እግረመንገድህን ስለጤናህ ተመክረህ ታልፋለህ። ምናልባት ከትናንት ወዲያ አንዷ ጎረቤትህ እናትህ ከሪፍትቫሊ #የገዛችውን(ማነው ያገኘችውን! No ያመጣችውን! ይሔም አይሆንም ብቻ whatever u call it) የዲግሪ ወሬ ሰምተዋል። "እንኳን ደስ አላት...ምን ተማረች...አንተን የመሰለ አድራሳ ምነው እስካሁን...😁" ብዙ ወሬ! ቲክቶክና ፌስቡክ የማይጠቀሙ ሰዎች መሰንበቻ የሚሆን ወሬና ጨዋታቸውን ከየት ያመጣሉ? እንደዚህ ነዋ የሚሸቃቅሉት። በስጋቸው መሀል ይሔም የለም። . . 5. ከሰል ይሸጣሉ። ይሔ ደሞ እንድሜ ለመብራትሀይል መላ ሰፈሩን ወደሳቸው ይነዳዋል። በህጻን አዋቂው "እማዬ የሉም" መባል ቀላል አይምሰላችሁ። በቀደም በመልክ የማያውቀኝ አንዱ "የበሀይሉ መጸሀፍ አለ?" ሲሉት ጃፈር ጎን ቆሜ የተሰማኝን ሙቀት አልረሳም። 😊 ጃፊ በአይኑ አይኔን እያጠቀሰ "አልቃለች..." ሲልማ እዛው ገልቤ ልመታ ምንም አልቀረኝ።😁 እማዬ... "ዝርዝር ይዛችሗል? ማነው ስምህ አንተ? አባትህ ይቅማል? በል ቀጣይ ስትመጣ ፌስታል ይዘህ ከመጣህ ለበጎቻችሁ የተረፈ ሰላጣና ድንች አዘጋጅልሀለሁ። ምነው አጠርክብኝ ደሞ" " ኧረ እናቴ ላጭታኝ ነው" " በልሺ ሒድ አጭበርባሪ ቁመትህን የማላውቅ መስሎህ ነው አ?" (ይቺ ሁለት መስመር እንኳ ነገር አማረልኝ ብዬ ልቦለድ ሳደርጋት ነው። እማዬ አይሞጣሞጡም። አይናፋር አሮጊት ናቸው) . ልጆቻቸው ጋር ሲሔዱ ቅላታቸውን እና ክብራቸውን የሚፈታተን ከሰል መሸጥ አይችሉም። ከሰል መሸጥ እናት ማውረድ መስሏቸው። የዋህነታችን! . . 6. ትረባ ትረባ አስለምጃቸው ነበር። የተለመደ ሰላምታቸው ሲያሰለቸኝ የፈጠርኩት መላ ናት። ለተፈሳው ለተገሳሁ ሁሉ ሊመክሩኝ ሲሞክሩ ቤት ገብቼ መሀል ጣት እስከማውጣት ስፈተን ትረባ አስለመድኳቸው። . "ምንስለሆኑ ነው እርሶ ሚካኤልን የማያስገቡት" ሙስሊም ናቸውና ይቀኑ ይሆናል ነጭ የለበሱ ጎረቤቶቻቸው ግቢውን አስታቅፈዋቸው ሲጠፉ። ሳቁ አይገልጸውም ፈነዱ! የወለቀ ሶስት ጥርሳቸው ፊት ሻሻቸውን ሳይጎትቱ። ተመልሰው ለመጡ አንጋሽ ጎረቤቶቻቸው እያወሯት ሰላምታቸውን አረዘሙ። . በቀደም ከውጪ ሲገቡ አይቼ.. "ከየት ነው?" ስላቸው ገቡልኝ " ወክ ወጥቼ። ጠበስኩኮ!" 😂😂 ኦቲስቲኩ በሀይሉ ከውስጤ ምን ይላል... "እንዴ በስተርጅና" ግም! አፌ " መቼ ነው የሚያስተዋውቁን?" አፋቸውን አፍነው 🤭 " በል አልችልህም ውጣልኝ" . ከሗላዬ... "ሰላም ይመልስህ በል! ደና እደር..." መቼም አመል ቶሎ አይለቅ። . እኚ ናቸው የሔዱት። #በሃይሉ_ሙሉጌታ @wegoch
إظهار الكل...
👍 40👎 4
⌚️ በቀጣይ List የሚደረጉ ፕሮጀክቶች 👇👇👇 ትንሽ ጊዜ ነው ያላችሁ! #LOST_DOGS https://t.me/lost_dogs_bot/lodoapp?startapp=ref-u_454803628__s_573809 1, MAJOR ⭐ https://t.me/major/start?startapp=454803628 2, BLUM🤢 https://t.me/blum/app?startapp=ref_4AQg09PDzR 2,CATS 🐈 t.me/catsgang_bot/join?startapp=dMdTmv--6IkmR-lKi1dWy 3, X-EMPIRE 🔥 https://t.me/empirebot/game?startapp=hero454803628 5,HAMSTER COMBAT 🐀 https://t.me/hamster_Kombat_bot/start?startapp=kentId454803628 6,HRUMME 💥 t.me/hrummebot/game?startapp=ref454803628 ለሌሎችም ያጋሩ!
إظهار الكل...
👍 5 4
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.