hanny❤tube
"ያ አላህ ለሰጠኸኝ ፀጋ ሁሉ አመሰግንሀለው በፍጥረታትህ ስፍር ቁጥር ልክ ምስጋና ይገባህ" ለማንኛውም ጥያቄ ወይም አስተያየት @hilarious28
إظهار المزيد789
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
የወንጀል ብዛት ያጎበጠኝ ባሪያህ ነኝ። ረህመትህን ከጅዬ ሁሌ አነባለሁ፡፡ እንደ ሰማይ የራቀኝ ኢማኔ እንዲመለስልኝ ወዳንተ አለቅሣለሁ፡፡
ተራቁቻለሁና የኢማን ልብስ አልብሠኝ፤
ደክሚያለሁና በተወኩል ካስሚያ ደግፈኝ፡፡
ሸብቻለሁና በተቅዋ ካባ አጊጠኝ፡፡፡
ያ ረብ!
@hannyTube
Repost from ABX
የወንጀል ብዛት ያጎበጠኝ ባሪያህ ነኝ። ረህመትህን ከጅዬ ሁሌ አነባለሁ፡፡ እንደ ሰማይ የራቀኝ ኢማኔ እንዲመለስልኝ ወዳንተ አለቅሣለሁ፡፡
ተራቁቻለሁና የኢማን ልብስ አልብሠኝ፤
ደክሚያለሁና በተወኩል ካስሚያ ደግፈኝ፡፡
ሸብቻለሁና በተቅዋ ካባ አጊጠኝ፡፡፡
ያ ረብ!
https://t.me/MuhammedSeidAbx
እነሆ
ከእንኳን አደረሳችሁ ወደ እንኳን አደረሳችሁ ተሸጋገርን። ለዚህ መድረስም ትልቅ መታደል ነው። ለረመዷን መድረስም፣ ጀምሮ በሰላምና ጤና መጨረስም ግዙፍ ፀጋ ነው። ሲመጣ በበረከቱ መምጣት ተደሰትን። ሲወጣ የጌታችንን ትዕዛዝ የቻልነዉን ያህል በመፈፀማችን፣ ትሩፋቱ መልካም ይሆናል ብለን በማሰባችን ተደሰትን። ሥራ ከኛ ዉጤት ከአላህ ነው። እሱ የመልካም ሠሪን ምንዳ ቅንጣት ታክል አይዘነጋም።
@hannyTube
#ረመዳን 24
وَٱلَّذِينَ هُمْ لِأَمَٰنَٰتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَٰعُونَ
እነዚያም እነርሱ ለአደራዎቻቸውና ለቃል ኪዳናቸው ጠባቂዎች፡፡
ይህ አንድ ሰው ሙዕሚን ለመሆን ከሚያሟላቸው መስፈርቶች አንዱ ነው።
አማኝ ሰው የሰውን አደራ አይበላም። ቃል ለመግባትም አይቸኩልም ከገባ ግን ለመፈፀም ይቻኮላል።
መልካም የኢባዳ ቀን😍😍
@hilarious28
ረመዷን - 21
***
ኢዕቲካፍ ከዱንያ ግርግርና ሁካታ በመራቅ ለቀናት አሊያም ለሰዓታት በተለያዩ የአምልኮ ተግባራት መስጊድ ዉስጥ የመቆየት ሁኔታ ነው፡፡ ዓላማው ወደ አላህ መቅረብ፣ ቀልብን ማለስለስ፣ ኢማንን ማደስ፣ በመንፈስ ከፍ ማለት ነው፡፡
ለሁሉም ነገር የተሻለ ጊዜ አለው። ለኢዕቲካፍ ይበልጥ ተመራጩ ጊዜ እነኚህ አሥር ቀናት ናቸው። ይህንኑ በማሰብ ባሮች ወደ አላህ መስጊድ ይመጣሉ።
አሁን አሁን ላይ ብዙ መስጊዶች ላይ ኢዕቲካፍ ይደረጋል፡፡ ጉጉቱ እንዳለ ሆኖ ስህተቶችም ሲፈፀሙ ይስተዋላል።
ኢዕቲካፍ ዓላማው ይሳካና ትርፍም ይገኝበት ዘንድ ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡
* ኒያ ይቀድማል፤ ኒያችሁን አሳምሩ፣ ሰው ስለገባ ብቻ አትግቡ፣
* ሙሉ ትኩረታችሁን ዒባዳ ላይ ብቻ አድርጉ፣
* ዱንያን እዉጭ ትታችሁ ግቡ። መንፈሳዊ ስኬትን አስቡ፣
* ራሳችሁን ፈትሹበት፣ ዉስጣችሁን እዩበት፣ የጥሞና ጊዜ አድርጉት፣
* በአምልኮ ወደ አላህ ይበልጥ ለመቃረብ አጋጣሚ ነዉና ተለወጡበት።
* ሱቃቸዉንና ስልካቸዉን ሁሉ ዘግተው ኢዕቲካፍ የሚገቡ ደጋግ ባሮች አሉ፣
* ዱንያዊ ወሬዎችንና ወጎችን ይራቁ፣
* የግድ ለሆነ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመስጊድ አትውጡ፣
* ቁርኣን፣ ዚክር፣ ዱዓ፣ ሶላትና ሶለዋት አብዙ።
አስታውሱ - ኢዕቲካፍ
* እንቅልፍ ሲለጥጡ የሚዉሉበት አጋጣሚ አይደለም፣
* ሶሻል ሚዲያ ላይ ተጥደው የሚያሳልፉበት ቦታም መሆን የለበትም፣
* ኢዕቲካፍ ነኝ ብለው ለዚህም ለዚያም አይለፍፉ፣ አላህ ያሉበትን ቦታና ሁኔታ ያውቃልነሰ፣
* የሀሜት ቦታ፣ ወሬ መሰልቀጫ፣ ምግብ ማማረጫ ቦታም እንዳይሆን ይጠንቀቁ።
* ቁጭ ብለው በስልክ የመነገጃ መድረክም አያድርጉት።
ኢዕቲካፍ ለትልቅ ዓላማ ነዉና የተደነገገወ በአግባቡ እንጠቀምበት።
ባረከሏሁ ፊኩም
@hannyTube
Repost from ABX
ረመዷን - 21
***
ኢዕቲካፍ ከዱንያ ግርግርና ሁካታ በመራቅ ለቀናት አሊያም ለሰዓታት በተለያዩ የአምልኮ ተግባራት መስጊድ ዉስጥ የመቆየት ሁኔታ ነው፡፡ ዓላማው ወደ አላህ መቅረብ፣ ቀልብን ማለስለስ፣ ኢማንን ማደስ፣ በመንፈስ ከፍ ማለት ነው፡፡
ለሁሉም ነገር የተሻለ ጊዜ አለው። ለኢዕቲካፍ ይበልጥ ተመራጩ ጊዜ እነኚህ አሥር ቀናት ናቸው። ይህንኑ በማሰብ ባሮች ወደ አላህ መስጊድ ይመጣሉ።
አሁን አሁን ላይ ብዙ መስጊዶች ላይ ኢዕቲካፍ ይደረጋል፡፡ ጉጉቱ እንዳለ ሆኖ ስህተቶችም ሲፈፀሙ ይስተዋላል።
ኢዕቲካፍ ዓላማው ይሳካና ትርፍም ይገኝበት ዘንድ ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡
* ኒያ ይቀድማል፤ ኒያችሁን አሳምሩ፣ ሰው ስለገባ ብቻ አትግቡ፣
* ሙሉ ትኩረታችሁን ዒባዳ ላይ ብቻ አድርጉ፣
* ዱንያን እዉጭ ትታችሁ ግቡ። መንፈሳዊ ስኬትን አስቡ፣
* ራሳችሁን ፈትሹበት፣ ዉስጣችሁን እዩበት፣ የጥሞና ጊዜ አድርጉት፣
* በአምልኮ ወደ አላህ ይበልጥ ለመቃረብ አጋጣሚ ነዉና ተለወጡበት።
* ሱቃቸዉንና ስልካቸዉን ሁሉ ዘግተው ኢዕቲካፍ የሚገቡ ደጋግ ባሮች አሉ፣
* ዱንያዊ ወሬዎችንና ወጎችን ይራቁ፣
* የግድ ለሆነ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመስጊድ አትውጡ፣
* ቁርኣን፣ ዚክር፣ ዱዓ፣ ሶላትና ሶለዋት አብዙ።
አስታውሱ - ኢዕቲካፍ
* እንቅልፍ ሲለጥጡ የሚዉሉበት አጋጣሚ አይደለም፣
* ሶሻል ሚዲያ ላይ ተጥደው የሚያሳልፉበት ቦታም መሆን የለበትም፣
* ኢዕቲካፍ ነኝ ብለው ለዚህም ለዚያም አይለፍፉ፣ አላህ ያሉበትን ቦታና ሁኔታ ያውቃልነሰ፣
* የሀሜት ቦታ፣ ወሬ መሰልቀጫ፣ ምግብ ማማረጫ ቦታም እንዳይሆን ይጠንቀቁ።
* ቁጭ ብለው በስልክ የመነገጃ መድረክም አያድርጉት።
ኢዕቲካፍ ለትልቅ ዓላማ ነዉና የተደነገገወ በአግባቡ እንጠቀምበት።
ባረከሏሁ ፊኩም
https://t.me/MuhammedSeidAbx
ረመዷን (20)
ከዐስር በኋላ አንድ ማዕድ ነበረን፣ እስከ መግሪብ ድረስ የሚዘልቅ። ከተራዊሕ በኋላም አንድ ማዕድ ነበረን፣ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ የሚረዝም። ከሱብሒ በኋላም ሌላ ማዕድ ነበረን፣ እስኪነጋ ድረስ የሚቆይ። ረመዷን የቁርኣን ወር ነዉና እነኚህ በቀን ዉስጥ የቁርኣን መማማሪያ ማዕዶቻችን ነበሩ።
በዚህ መልኩ መስጂዶች በቡድን ቡድን ሆነው ቁርኣንን በሚማማሩ ሐለቃዎች ይደምቃሉ። የዛሬዉን ሳይሆን የድሮዉን ነው የማወራችሁ። አላህ ይዘንልህ ሙሐመዱ፤ ምን ሆነህ ነው እንዲህ የደከምከው!።
ሰብሰብ ብሎ ተቀምጦ ቁርኣንን በዙር ማንበብ በርካታ ፋይዳዎች አሉት። ያላወቁትን ለመማር፣ ያጠፉትን ለማስተካከል ያግዛል። ለማስተዋልና ለማስተንተንም ይጋብዛል።
በአላህ ቤት ዉስጥ ቁርአንን ስብስብ ብሎ ማንበብና መማማር አላህ ዘንድ ያስወድዳል፣ የዉጭና የዉስጥ ሰላም ይሰጣል፣ የአላህን እዝነት ያስገኛል፣ በመላእክት ያሰከብባል፣ በላዕላዩ ዓለም ያስወድሳል።
የ20ኛ ቀን ፀሐይ እየጠለቀች፣ የረመዷን 21ኛው ቀን ገባሁ እያለ ነው። አላህ ረሃብ ጥማታችሁን፣ ድካማችሁን ሁሉ ይቁጠር።
@hannyTube @hilarious28
ረመዷን 20
በርግጥ ትናንት ነበር አላህ ሆይ ለረመዷን አድርሰን ብለን ስንማፀን የነበረው።
ዛሬ ስለ ዐሽረልአዋኺር እያወራን ነው። 10ቱ ወሳኝ የረመዷን የመጨረሻ ቀናት።
ጌታዬ ሆይ ሁሌም የእዝነትህ ከጃዩች ነን። ለባሮችህ እዘንልን።
@hannyTube
اختر خطة مختلفة
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.