cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

gambella educational media

ትምህርታዊ መረጃዎችን ይከታተሉ

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
2 286
المشتركون
-124 ساعات
+257 أيام
+19330 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

በጋምቤላ ክልል የትምህርት ሥራውን ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና ሊጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ። በክልሉ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡ መስከረም 7/2017 ዓ.ም(የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ) የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ማበር ኮር እንዳሉት የትምህርት ጥራትን የማረጋገጡ ስራ ለመንግስት ብቻ የሚተው አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለማሻሻል የህብረተሰቡ ድጋፍና እገዛ ሊጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል። የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጥረት መሳካት የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል። የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ውጤታማ እንዲሆን የትምህርት ዘርፍ አመራሮች፣ መምህራን እና ወላጆች በቅንጅት እንዲሰሩም አቶ ማበር አሳስበዋል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ፖክ ካዊች በበኩላቸው በ2017 የትምህርት ዘመን የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ ቢሮው ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ይሰራል ብለዋል። በትምህርት ዘመኑ የትምህርት ቁሳቁስ እጥረት እንዳይኖርና ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቋረጡ የድጋፍ ስራዎችን እንደሚሰሩ  አስረድተዋል። በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት ወላጆች እንዳሉት የተማሪዎች የውጤት ማጣት በትምህርት ዘመኑ እንዳይኖር ትምህርት ቤቶች በአግባቡ እንዲያስተምሩ ጠይቀዋል። ተማሪዎች ከትምህርት ቤት መማር ማስተማር ሂደት በተጨማሪ ወደ ቤታቸው ሲመጡ እንዲያጠኑ የክትትል ስራዎችን እንደሚያከናዉኑ ወላጆቹ አረጋግጠዋል። በዕለቱም የትምህርት ቁሳቁስ መግዛት ለማይችሉ ተማሪዎች ድጋፍ ተደርጓል። @ከጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት
إظهار الكل...
👍 1👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታችሁን በሚከተሉት  የውጤት መግለጫ አማራጮች ከጳጉሜ 4 ቀን ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ማየት ትችላላችሁ። (ጷጉሜ 4/2016 ዓ.ም) 1. ፖርታል፡- https://result.eaes.et 2. በቴሌግራም ቦት (Telegram Bot):- https://t.me/EAESbot 3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 6284 ላይ ‘R’ን በማስቀደም የመለያ ቁጥር በማስገባት (ምሳሌ R1234567) መልዕክት በመላክ ውጤትዎን ማወቅ ይችላሉ፡፡ ይህ አማራጭ ኢትዮ ቴሌኮም የሚያስከፍለው መደበኛ የSMS ክፍያ ይኖረዋል። ከውጤት መግለጫ ፖርታልና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማታም ይችላል፡፡ በተጨማሪም ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላቸው  ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መምጣት ሳያስፈልግ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ Compliant የሚለውን በመጫን የቅሬታቸውን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ይችላሉ። የቅሬታቸውን ምላሽ ቅሬታቸውን ባቀረቡበት ተመሳሳይ አድራሻ የሚሰጥ  ይሆናል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
إظهار الكل...
👍 16 3🥰 1😱 1🎉 1
👍 8 2
Photo unavailableShow in Telegram
👍 9🙏 5🤗 3
Photo unavailableShow in Telegram
6
Photo unavailableShow in Telegram
የጋምቤላ ክልል ትምህርት ቢሮ 13ኛውን ክልል አቀፍ የትምህርት ጉባኤ "በተደራጀ የህዝብ ተሳትፎ የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ"በሚል መሪ ቃል ያካሂዳል። (ነሀሴ 28/2016 ዓ.ም) ጉባኤው ነገን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በ2016 የትምህርት ዘመን በትምህርት ዘርፉ የተመዘገቡ ውጤቶችን እና ተግዳሮቶችን በመገምገም በ2017 የትምህርት ዘመን የሚተገበሩ ስራዎች ላይ ተወያይቶ የትኩረት አቅጣጫዎችን የሚያስቀምጥ ይሆናል፡፡  
إظهار الكل...
👍 12👏 3
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
👍 5 2
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.