cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

مشاركات الإعلانات
11 831
المشتركون
+124 ساعات
+47 أيام
+15430 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ክፍል# 16 #ሸርህ ኡሱሉ አሰላሳ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ለሰለፍዮችና ለሐቅ ፈላጊዎች በሙሉ (እየተሰጠ ነው።) •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• የኪታብ ዝግጅት:-በተከበሩ ሸይኽ ሙሀመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን ረሂመሁሏህ المؤلف:- لفضيلة الشيخ  محمد صالح العثيمين رحمه الله •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ደርሱ የሚሰጠው:- በኡስታዝ አቡ ዓብዱልዓዚዝ ዩሱፍ ብን አህመድ ሃፊዘሁሏህ ➴➴➴➴➴ ================ መስጂድ:- አል ቡኻሪ፣ባህር ዳር •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ከጁሙዓ ቀን ውጪ ሳምንቱን ሙሉ ዘወትር ከ6:00 እስከ 6:45 ድረስ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•   ተለቀቀ። •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ➴➴➴➴➴ ================= ለሌሎች እንዲደርስ share/ሼር/ በማድረግ የበኩላችንን እናበርክት ባረከሏሁ ፊኩም። ➴➴➴➴➴ ==================== የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• كن على بصيرة ➴➴➴➴➴ https://t.me/alateriqilhaq
إظهار الكل...
_شرح أصول الثلاثة -١٦-.mp38.81 MB
↪️ የጁመዓ ኹጥባ (ምክር) ↩️ خطبة الجمعة؛ ➴➴➴➴➴ ✅ ርዕስ፦ « የኢስልምና አፍራሾች በሚል» በሚል አንገብጋቢ  ወቅታዊ ርዕስ ➴➴➴➴➴ 🎙በኡስታዝ አቡ ዓብዱልዓዚዝ ዩሱፍ ብን አህመድ ሀፊዘሁሏህ 🎙للآستاذ أبوا عبد العزيز يوسف بن أحمد -حفظه الله- 🗓 መስከረም ‐10  ‐ 01 - 2017 E.C 🕌ባህር ዳር ከተማ መስጅሰለፍ 🕌 بمدينة بحردار [إثيوبيا]؛ في مسجد السلفية ዝርዝሩን ገብታችሁ አዳምጡ ይ ደ መ ጥ share/ሼር/አድርጉ ባረከሏሁ ፊኩም። #size መጠን 8.78 MB #length 33:39 min 🕌መስጅድ:-አስ-ሰለፍ 🌎ባህር ዳር፣ ኢትዮጲያ የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
إظهار الكل...
የእስልምና አፍራሾች_20-09-24_18-13-34-928.mp38.37 MB
📌መውሊደኞችና የቀን ቅዠታቸው (የመጨረሻ ክፍል) መውሊደኛው ዶ/ር እድሪስ፣ “ለአለማት እዝነት አድርገን እንጂ አልላክንህም” (አል-አንቢያ፣ 107) የሚለውን የቁርአን አንቀፅ ካነበበ በኋላ እንዲህ ይላል፡- “ለአለም እዝነት እንድትሆን” ካለ በኋላ ፈገግ በማለት ጭምር ጋዜጠኛውን፣ “'መድሀኒያለም' እንላለን አይደል?” በማለት ይጠይቀዋል፡፡ ልብ በሉ፣ “'መድሀኒያለም' ትላላችሁ አይደል?” አይደለም ያለው፡፡ እሱ ራሱን፣ እየሱስን “መድሀኒያለም” የሚሉት የክርስቲያኖች አካል አድርጎ ነው የጠየቀው፡፡ ይህ “መድሀኒያለም' እንላለን…” የሚለው የመምህር እድሪስ ንግግር፣ “ሁላችን የእዝጊያብሄር ልጆች ነን” ያለውን የኡስታዝ አቡቦክርን ንግግር አስታወሳችሁ? ያውላችሁ - መገለባበጥ፣ ማስመሰልና ቀለምን እንደ እስስት መቀያየር የኢኽኖች አንዱ መለያቸው ነው፡፡ ዶ/ር እድሪስም ያደረገው ይሄንኑ ነው፡፡ “'መድሀኒያለም' እንላለን አይደል?” ካለና የጋዜጠኛውን “እም” የሚል አዎንታዊ ምላሽ ካገኘ በኋላ፣ “መድሀኒት እድትሆን፣ ለአለም እዝነትን፣ መተዛዘንን፣ ፍቅርን፣ ሰላምን፣ ልታጎናፅፍ ነው የተላከው ይላል፡፡ የነብዩ ሙሀመድ መወለድ አላማ ከእዝነት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ከሰላም ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ከስሙሙነት፣ ከውህደት ጋር፣ ከመከባበር ጋር፣ የተያያዘ ነው፡፡ ትልቁ ተልኮ ይሄ ነው፡፡” በማለት ይደመድማል፡፡ “ለአለማት እዝነት አድርገን እንጂ አልላክንህም” (አል-አንቢያ፣ 107) የሚለውንና ስለመላካቸው አላማ የሚገልፀውን የቁርአን አንቀፅ፣ ስለመወለዳቸው የተወረደ አንቀፅ አድርጎ በማቅረብ፣ ከፍተኛ የማጭበርበር ተግባር ፈፅሟል፡፡ በልደት ቀን ማክበር ፍቅር ልቡ ክፉኛ የተነደፈው መውሊደኛው ዶ/ር እድሪስ፣ “እንኳን አይደለም የታላላቅ ነብያት ሁሉ ቁንጮ ናቸው ተብለው የሚታመኑትን ነብዩ መሀመድን አይደለም… ሰው የራሱንም ውልደት ሊያደንቅ ይገባዋል፡፡ ለዚህ ነው አንድ ሰው ልጅ ሲወለድለት፣ በሰባተኛው ቀን እርድ አርዶ (አቂቃ) ሴሮሞኒ እንዲያካሂድ ይጠየቃል…” በማለት እርስበረሱ የተምታታና የማይገኛኝ ነገር ደበላልቆ ይናገራል፡፡ አዲስ ለተወለደ ልጅ በሰባት ቀን የሚፈፀም እርድና ግብዢያ በምን መንገድ ነው ከመውሊድ በአል አከባበር ጋር የሚገናኘው? አንድ ሰው ሳምነት ለተወለደ ልጁ፣ ዛሬ ደግሶ ቢያበላ ድግሱም፣ ማብላቱም ዛሬውን አለቀ፡፡ አንደኛ፡- አቂቃው የሚደረገው አመት ጠብቆ በልደት ቀኑ ሳይሆን በሰባት ቀኑ ነው፡፡ ሁለተኛ፡- ከዚህ በኋላ በምንም መንገድ ደግሞ አይደረግም፡፡ የመውሊደኞቹ መውሊድስ? አንደኛ፡- በያመቱ የግድ ይደረጋል፡፡ ሁለተኛ፡- ያሰኘው ሰው ደግሞ አመት ሳይሞላም ሊያደርገው ሁሉ ይችላል፡፡ አቂቃንና መውሊድን ሊያገናኘው የሚችለው ነገር ቢኖር ምናልባት የሚታረድ ነገር መኖሩና ሰዎች መመገባቸው ነው፡፡ ይሄ ከሆነ ደግሞ ከሰርግም ጋር እያነፃፀሩ ያብራሩልን እንጂ የእኛ አዋቂዎች! የመውሊደኞቹ የቀን ቅዠት እንዲህ ነው የሚያስቀበጣጥራቸው፡፡  መውሊደኛው እድሪስ፣ መውሊድን የኢስላማዊ አምልኮ መነሻ አድርጎ እስከማቅረብ በደረሰ መልኩ፣ የመውሊዳዊ የቀን ቅዠቱን ለጥጦ ነው ያቀረበው፡፡ የሚከተለውን ንግግሩን በፅሞና እንመለክት፡- “ስለዚህ እያንዳንዱ ሰው… እዚህ  አለም መምጣቱን 'ተቀብዬዋለሁ' ብሎ ለፈጣሪው እጅ መስጠቱ ትልቁ የአምልኮ ስርአት መነሻ ነው፡፡ በመፈጠሩ ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው፤ በመፈጠሩ ደስተኛ ያልሆነ ሰው ከዚያ ነብይ ተልኮለት፣ ቁርአን-መፅሀፍ … መመሪያ ተልኮለት 'በዚያ መመሪያ ተጓዝ' ብትለው 'ከመጀመሪያውኑ እኔ'ኮ በመፈጠሬም አልተስማማሁም' ሊልህ ይችላል፡፡ ስለዚህ መወለድን ማድነቅ የእምነቱ አካል ነው - እንደ ግለሰብ፡፡” ይሄውላችሁ፣ አቶ ዶ/ር ኢስላማዊ ጥሪ ከዚህ መጀመር አለበት እያለን፡፡ አንድ ሰው ቁርአንንም ሆነ ኢስላማዊ መመሪያን ይቀበል ዘንድ፣ ዳእዋው መጀመር ያለበት፣ ግለሰቡ መወለዱን እንዲያደንቅ በማድረግ ነው፡፡ መወለዱን ካላደነቀ፣ መወለዱን የሚራገም፣ በመፈጠሩ የማይስማማ ከሆነ፤ “ወደ ኢስላም ጥሪ ልታደርግለት አትችልም” እያለን ነው፡፡  ስለዚህ እንደ ዶክተሩ ቅዠት ከሆነ፣ የአሏህ መልእክተኛ (አለይሂ ሶላቱ ወሰላም) ለቁረይሽ አጋርያን “'ከአሏህ ውጭ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም' በሉ፣ ትድኑ ዘንድ” በማለት  የኢስላማዊ ጥሪያቸውን መጀመራቸው “ተገቢ አልነበረም” ብቻ ሳይሆን “ትልቅ ስህተት ሰርተዋል” ማለት ነው፡፡ መጀመሪያ ማድረግ የነበረባቸው፣ እነአቡ ጀህልን፣ እነአቡለሀብን፣ እነአቡ ጧሊብን… መወለዳቸውን እንዲያደንቁ ማድርግ ነበር… ይሄን ሲቀበሏቸው ነበር ወደ ሌላው የእምነት ጉዳይ መሄድ የነበረባቸው፡፡ አኡዙ ቢሏህ፡፡ ሙአዝንም ወደ የመን ሲልኩ፣ “እዚያ ከመፅሀፉ የሆኑ ሰዎችን ታገኛለህ፡፡ ከሁሉ መጀመሪ መወለዳቸውን እንዲያደንቁ፣ በመፈጠራቸው እንዲስማሙ ታደርጋለህ…” በማለት መላክ ነበረባቸው…  ስለዚህ እንደ ዶክተሩ ቅዠት ከሆነ፣ የአሏህ መልእክተኛ (አለይሂ ሶላቱ ወሰላም) ብቻ ሳይሆኑ፣  አሏህ የላካቸው ሌሎቹም ነብያት ሁሉ፣ ተውሂድን የመጀመሪያ ተልእኮ አድርገው መስበካቸው ስህተት ነበር፡፡ የመውሊድ ፍቅሩ የቀን ቅዠት ውስጥ የከተተው ዶ/ር እድሪስ እንዲህ ይላል፡-“…በዚያ መመሪያ ተጓዝ ብትለው ከመጀመሪያውኑ እኔ'ኮ በመፈጠሬም አልተስማማሁም ሊልህ ይችላል፡፡ ስለዚህ መወለድን ማድነቅ የእምነቱ አካል ነው…” ስለዚህ ነብያት ሁሉ የሰሩት የጋራ ስህተት አንድ ነው - የተላኩላቸውን ሰዎች መወለዳቸውን ማድነቅ ሳያስችሉ ወደ ተውሂድ መጥራታቸው፡፡ የመውሊደኞቹ የመውሊድና የጫት ፍቅር ከቅዠትም አልፎ እንዲህ እንደ ትኩስ እብድ ያገኙትን ሁሉ እንዲቀበጣጥሩ፣ የመሰላቸውን ሁሉ እንዲዘለባብዱ እያደረጋቸው ነው፡፡ (ጫትን የጨመርኩት፣ መቼም ያለጫት መውሊድ አይታሰብምና ነው፡፡)   አንድ የቁርአን ወይም የሀዲስ ማስረጃ ስለማይገኝለት መውሊድ፣ ከሸሪአው ጋር ፍፁም በሚጋጭ መንገድ የቋጥ-የባጡን ከዘባረቀ በኋላ እንዲህ ይላል - መውሊደኛው ዶ/ር እድሪስ፡- “የእስልምና ዋና መርሁ ላኢላሀ ኢለሏህ ነው፤ ከዚያ ሙሀመድ ረሱለሏህ ትላለህ፡፡ ላኢላሀ ኢለሏህ ማለት የእሳቸው ትልቁ ተልእኮ ይሄ ነው፡፡ በምድር ላይ ብዙ አምላክት አሉ፡፡ ገንዘብ አንድ አምላክ ነው፡፡ ስልጣን… አምላክ ነው፤ ስሜት አምላክ ነው፤ ላኢላሀ ኢለሏህ ስትል ገንዘብን ከታች ታደርጋለህ፤ ላኢላሀ ኢለሏህ ስትል ስልጣንን ዝቅ አድርገህ ነው፡፡ ስልጣን ለፈጣሪ ነው ብለህ ነው የምታምነው… ለስሜት ተገዢነትም ይገደባል… በምድር ላይ ሀያሉ ፈጣሪ ነው፡፡ ጉልበት አይደለም፤ ቴክኖሎጂ አይደለም… ሀይል ለእግዚአብሄር፣ ሀይል ለአምላክ ነው ብለህ ትነሳለህ…” ላኢላሀ ኢለሏህን ለማስረዳት ከሰባ በላይ ቃላትን ባባከነበት በዚህ ንግግሩ ውስጥ፣ የላኢላሀ ኢለሏህን ዋናውንና ትልቁን ጉዳይ ዘሎታል፡፡ ከስልጣንም፣ ከስሜትም፣ ከገንዘብም አምላክ በላይ የሆነውን   የጣኦታት አምልኮን ሳይጠቀስ ትቶታል፡፡ የጣኦታት አምልኮን ለማንኮታኮት ነው ነብያት የተላኩት፣ የተገደሉለትን፣ የተሰደዱት፣ ስንትና ስንት የነብያት ባልደረቦች የተሰውት… ትልቁን የጣኦታት አምልኮ ግን ዘሎታል፡፡
إظهار الكل...
ለምን? በእለተ መውሊድ በዳና፣ በመጅት፣ በጀማ ንጉስ፣ በቃጥባሬ… ልጅ፣ ሀብትና ጤና እንዲሰጡ የሚለመኑት ጣኦታት እንዳይነኩበት... ወይስ በክርስትና ሀይማኖት የሚመለኩት ጣኦታት እንዳይነኩ አስቦ ይሆን? ለማንኛውም ላኢላሀ ኢለሏህን ሲያብራራ ትልቁን የጣኦት አምልኮ የዘለለው ሆን ብሎ ለመሆኑ አትጠራጠሩ! የሚጠራጠር ካለ፣ መጠራጠሩ ኢኽዋን እባብ ሲደመር እስስት መሆኑን በውል ያለማወቁ ውጤት ነው፡፡ ቀስ ብሎ ይገባዋል፡፡  በመውሊድ ፍቅር ክፉኛ የተለከፈው የመምህር እድሪስ ሌላው የቀን ቅዠት፣ መውሊድን የማያከብር ሙስሊም የሌለ አድርጎ ለማቅረብ የሄደበት ርቀት ነው፡፡ በጣም ነው የተጋጋጠው፤ ትዝብት ላይ እስከሚወድቅ ድረስ ነው የተላላጠው፡፡ በየሳምነት የተወለዱበትን ቀን መፆም እሳቸውን ማክበር እንደሆነ በመጥቀስ፣ ያን እለት መፆም ልደታቸውን ማክበር እንደሆነ ይናገራል፡፡ “ቁምነገሩ ግን አውደ አመት ይሁን አውደ ሳምንት ይሁን? ነው ጥያቄው” ይላል፡፡ ዶክተሩ ጤነኛ ነው ብላችሁ? መልእክተኛው (አለይሂ ሶላቱ ወሰላም) የተወለዱበትን ቀን እሳቸው በሰሩት መሰረት በየሳምንቱ ፁሞ መዋልና በአመት አንዴ ተሰብስቦ ምግብ ሲበሉና ጫት ሲያመነዥጉ መዋል እንዲሁም ሲጨፍሩ ማደር በምን መንገድ ነው የሚገናኘው? ከማንኛውም መጠጥና ምግብ ተቆጥቦ፣ ርሀብ እየሞረሞረውና ጥም እያቃጠለው የሚዋልበትን የፆም ቀንና ሲበላና ሲጠጣ የሚዋልበትን የበአል ቀን ምን ያገናኛቸዋል? በአለማችን በፆም የሚከበር በአል ካለ፣ ዶ/ር እድሪስ የነገረን ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ በስሙ በአለም ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ እንዳይሰፍርለት ያለው ችግር አንድ ብቻ ነው - ይህ የፆም በአል ያለው በዶ/ሩ ቅዠታዊ አለም እንጂ በምድር ላይ በተግባር የሌለ መሆኑ፡፡  ግለሰቡ ያልዘባረቀው ነገር የለም፡፡ የመውሊድን በአል ከደነገጉት ሰዎችም አንዱ እሱ እንደሆነ በሚያሳብቅና እጅግ ግብዝነት በተሞላው መንገድም እንዲህ ብሏል፡- “የተወለዱበትን ቀን ነብዩ አክብረዋል - በፆም፡፡ ያው በእኛ አገር ድህነት በጣም ስለሚበዛ፣ ሰውን ከምናስፆመው 'ብናበላው ይሻላል' ብለን፣ በማብላት እያከበርነው ነው፡፡ ገብቶሀል፤ ደሀ በማብላት እናከብረዋለን፡፡ ከአመት አንድ ቀን የስጋ ሽታ የማያይ በርካታ ህዝብ ስላለን እሱን ፁም አንለውም፡፡ አመቱን ሙሉ እየፆመ ነው፤ ፈስኮ አያውቅም፡፡” ሸሪአዊ ማስረጃ አልባ ለሆነው መውሊድ፣ መውሊደኞች ከቻሉ ከቆሻሻ ገንዳም ሳይቀር ማስረጃ መሰል ቡትቶ ፍለጋ ሲዳክሩ እንደሚኖሩ ማወቅ የፈለገ፣ ዶ/ር እድሪስ መውሊድን ማክበር አስፈላጊ መሆኑን ለማሳየት የጠቀሰውን የሚከተለውን ንፅፅራዊ ምሳሌ ማየት ከበቂ በላይ ነው፡፡ እንዲህ ይላል፡- “ልክ ለኤች አይቪ፣ ለውሀ ቀን፣ የላባደር ቀን፣ የሴቶች ቀን፣ ብለን የምናስታውሰው በሌላ ቀን ያንን ጉዳይ አናስታውሰውም ማለት አይደለም፡፡ የተሻለ ትኩረት ለመስጠት ነው… በዲፓርትመንታችን ውስጥ ጉባኤ እናካሂዳለን እኮ፡፡ ማነው ስለዚህ… ህገወጥነት የሚጠይቀኝ፡፡” አቶ ዶ/ር ስለዲፓርትመንህ ጉባኤ ህጋዊነት ወይም ህገ ወጥነት የዩኒቨረሲቲህን አመራሮች ጠይቅ፡፡ እኛ ምናገባን፡፡ ስለመውሊድ ህገ ወጥነት ግን የሚጠይቅህ፣ አትጠራጠር “ሀይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ” ያለው ሀያሉ አሏህ ነው፡፡ ስለመውሊድ ህገ ወጥነት የሚጠይቅህ፣ አትጠራጠር “በዲን ላይ የሚደረግ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ የእሳት ነው” በማለት ያስተማሩት ምርጡ የአሏህ መልእክተኛ ናቸው፡፡ ወንድሜ፣ ትእቢቱንና መኮፈሱን ትተህ ብትቶብት ይሻልሀል፡፡ በአሏህ ዲን ላይ ተቀጥፎ የተለጠፈው መውሊድ ብሄራዊ የበአል ቀን ሆኖ መዋሉንም፣ እንደ ትልቅ ድል ነው ሰውዬው የሚዘክረው፡፡ እንዲህ ይላል፡- “ሙስሊም የሆነውም ሙስሊም ያልሆነውም ህብረተሰብ ለምን ነው ስራ የማትገባው ብትለው፣ ዛሬ የነብዩ ሙሀመድ ልደት ነው” ይልሀል፡፡ ሰውዬው በዚህ አላቆመም፡፡ ቢድአ አራማጆች ምን ያህል አቅላቸውን እንኳን የማይጠቀሙ የስሜት ባሪያዎች መሆቸውን በሚያሳይ መንገድ እንዲህ ይላል፡- “ነብዩ መሁመድን እኛኮ ብሄራዊ ጀግናችን አድርገናቸዋል፡፡” በምድር ላይ ከተፈጠሩት ሰዎች ሁሉ ታላቁ ሰው የሆኑትን ነብይ፣ ከነብያት ሀሉ ታላቁና የነብያት ሁሉ አለቃ የሆትን ነብይ፤ የመንደራችን ጀግና አድርገናቸዋል በማለት ይመፃደቃል፡፡ ይሄ ምን አይነት “ፍልስፍና” ወይስ ድድብና ነው?   የሰውዬው ድፍረትም፣ ጅህልናም፣ ቅዠትም፣ ቅጥፈትም … ልክም፣ ድንበርም የለውም፡፡ የመውሊድ በአል ከኢድል አልፈጥርና ከኢደል አድሀ በላይ መሆኑን እስከመናገር መድረሱ፣ ለዚህም አንዱ ማሳያ ነው፡፡ እንዲህ ይልላችኋል፡- “(መውሊድ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከኢድል ፈጥርም፣ ከኢደል አድሀም በላይ ነው፡፡ የመውሊድ ፕራክቲካል ፋይዳ የሰፋ ነው፡፡ ለምን ኢድል ፍጥር ላይ ሰው አይሰባሰብም፡፡ አንድ አካባቢ፣ አንድ ወረዳ… አውራጃ ላይ ያሉ በጋራ ሊሰግዱ ይችላሉ፡፡ የነብዩ መውሊድ እለት ግን ከተለያዩ አካባቢዎች… ይሰባሰባሉ፡፡ ህብረ ብሄራዊ እኮ ነው፤ ሰውን ሰበሰብከው እኮ፡፡ ለአንድ አላማ፡፡ ዱአ ያደርጋል፤ መተዋወቅን ያመጣል፤ ነጋዴው ይነግዳል… ምግብ ያቀርባል፡፡ አልባሳት ያቀርባል… አመታዊ ኮንፈረስም ነው፡፡” እናም ይሄውላችሁ፣ የሸርክና የወንጀሎች መናኻሪያ የሆነውን መውሊድን፣ ይሄ የለየለት ሙብተዲእ፤ ከሰባቱ ሰማያት በላይ በመጣ ትእዛዝ ለሙስሊሞች ከፀደቁላቸው ሁለቱ ብርቅዬ ኢዶች አብልጦ አስቀመጠው፡፡ ምን አይነት ጠማማና አጥማሚ ሰው አደረገው? ሲጠቃለል፡- ዶ/ር እድሪስን በአሏህ ዲን ላይ እንዲህ የባጥ-የቆጡን እንዲቀበጣጥር፣ በዲን ስም የሱፍይነትን ቆሻሻ አምልኮ ኢስላማዊ አድርጎ ለማቅረብ ክፉኛ እንዲላላጥ፣ በመልእክተኛው (አለይሂ ሶላቱ ወሰላም) ላይ እንዲቀጣጥፍ ያደረገው ምንድነው? በአይሁድ ሰርጎ ገቦችና በሺአ ሴራ ተጠልፈው በወደቁ ሙስሊም ተብዬ ዱኩማኖች በሚከበር የቢድአ ፍቅር መለከፍ፣ ለሀቅ እጅ ከመስጠት ይልቅ የስሜት ባሪያ መሆን… ቢድአን አምልኮ አድርጎ ከያዘ ሰው የበለጠ እውር፣ ስሜቱን አምላክ አድርጎ ከያዘው የበለጠ ጠማማ ማን አለ? “ዝንባሌውን አምላኩ አድርጎ የያዘውን፣ አላህም ከዕውቀት ጋር ያጠመመውን፣ በጆሮውና በልቡ ላይም ያተመበትን፣ በዓይኑም ላይ ሺፋን ያደረገበትን ሰው አየህን! ታዲያ ከአሏህ በኋላ የሚያቀናው ማነው? አትገሠጹምን?” (አል-ጃሲያህ፣ 23) ዝግጅት/በዶክተር ጀማል ሙሐመድ - ሀፊዞሁሏህ - https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
إظهار الكل...
•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ክፍል# 15 #ሸርህ ኡሱሉ አሰላሳ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ለሰለፍዮችና ለሐቅ ፈላጊዎች በሙሉ (እየተሰጠ ነው።) •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• የኪታብ ዝግጅት:-በተከበሩ ሸይኽ ሙሀመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን ረሂመሁሏህ المؤلف:- لفضيلة الشيخ  محمد صالح العثيمين رحمه الله •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ደርሱ የሚሰጠው:- በኡስታዝ አቡ ዓብዱልዓዚዝ ዩሱፍ ብን አህመድ ሃፊዘሁሏህ ➴➴➴➴➴ ================ መስጂድ:- አል ቡኻሪ፣ባህር ዳር •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ከጁሙዓ ቀን ውጪ ሳምንቱን ሙሉ ዘወትር ከ6:00 እስከ 6:45 ድረስ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•   ተለቀቀ። •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• ➴➴➴➴➴ ================= ለሌሎች እንዲደርስ share/ሼር/ በማድረግ የበኩላችንን እናበርክት ባረከሏሁ ፊኩም። ➴➴➴➴➴ ==================== የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• كن على بصيرة ➴➴➴➴➴ https://t.me/alateriqilhaq
إظهار الكل...
شرح_أصول_الثلاثة_١٥_19_09_24_11_38_29_791.mp310.55 MB
🟢“ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ ” ለነሲሃ ቲቪ ተፃፈው የተባለው “በመውሊድ ስንጨፍር በካሜራ ቅረፁን” አይነት ደብዳቤ አሳዛኝም አስተማሪም ነው። 👉አሳዛኙ በሱና ማማ ከፍ ካሉ በኋላ ወድቆ ለሙብተዲዕ መሳለቂያ መሆን እጀግ ያሳዝናል። እነ አጅሬ "ነሲሃዎች" ከዚህ በፊትም በርካታ የተጠለፉባቸው ወጥመዶች በደብዳቤ የጀመሩ ናቸው። ከሱፊዮችና መሰሎቻቸው ጋር በተለያዩ የሙጃመላ መድረኮች ላይ ስለሚተዋወቁ ነው የተናቁት ። “ ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ ” እንደሚባለው ነው። በሱና ላይ የነበራቸው አቋም እንደቀለጠ ከጀይላን ጀምሮ ወዳጅም ጠላትም ነገራቸው ። ከዚህም በከፋ ጉዳይ እንደለመዱት እንተባበር ይሉ ይሆናል። 👉አስተማሪው 1️⃣አቋም በወረደ ልክ በጠላት መደፈርና ውርደት ይመጣል ።የአላህ እርዳታም ይርቃል። عَنْ ثَوْبَانَ قَالَ : قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : " يُوشِكُ الْأُمَمُ أَنْ تَدَاعَى عَلَيْكُمْ كَمَا تَدَاعَى الْأَكَلَةُ إِلَى قَصْعَتِهَا ". فَقَالَ قَائِلٌ : وَمِنْ قِلَّةٍ نَحْنُ يَوْمَئِذٍ ؟ قَالَ : " بَلْ أَنْتُمْ يَوْمَئِذٍ كَثِيرٌ، وَلَكِنَّكُمْ غُثَاءٌ كَغُثَاءِ السَّيْلِ، وَلَيَنْزِعَنَّ اللَّهُ مِنْ صُدُورِ عَدُوِّكُمُ الْمَهَابَةَ مِنْكُمْ، وَلَيَقْذِفَنَّ اللَّهُ فِي قُلُوبِكُمُ الْوَهْنَ ". فَقَالَ قَائِلٌ : يَا رَسُولَ اللَّهِ، وَمَا الْوَهْنُ ؟ قَالَ : " حُبُّ الدُّنْيَا وَكَرَاهِيَةُ الْمَوْتِ ". أخرجه أبو داود (4297) وصححه الألباني ሰውባን አሉ ፥ የአላህ መልእክተኛ (ﷺ)አሉ፦" የጥመት ህዝቦች (ለጥቃት) ሊጠራሩባችሁ ይቀርባሉ ፤ ልክ በላተኞች ተሻምተው ወደ ሚበሉት ማዕድ እንደሚጠራሩት ።" ጠያቂ እንዲህ አለ ፥ ያኔ በቁጥር አናሳ በመሆናችን ነውን ? ነቢዩ (ﷺ) አሉ ፦ " እንዲያውም የኔ ብዙ ናችሁ ፤ ነገር ግን እንደ ጎርፍ ግሳንግስ ደካማ ናችሁ ፤ አላህም በእርግጥ ከጠላቶቻችሁ ልብ ውስጥ ለእናንተ የነበራቸውን ክብር ነቅሎ ያስወጣል ፤ አላህም በእርግጥ በልባችሁ ውስጥ ውርደትን ይጥልበታል ።" ጠያቂ እንዲህ አለ ፥ ከምን የመጣ ውርደት ነው ? ነቢዩም (ﷺ) አሉ ፦ "የዱንያ ውዴታ እና ሞትን መጥላት (አኺራን መርሳት) ።” 2️⃣ለጠላት ማባበያና ማቀራረቢያ አንዴ በር የከፈተ ዲኑን እና ክብሩን ለአደጋ አጋልጧል። ከዕብ ኢብኑ ማሊክ ከገሳን ንጉስ የመጣለትን ማባበያ ደብዳቤ ምን ነበር ያደረገው ⁉️ ✍  ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊያ) http://t.me/Abuhemewiya https://t.me/bahruteka/5368
إظهار الكل...
🎤 ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ) ✍

የጠራ እውቀት ከተቃና አቐምና ተግባር ጋር የተረዘቀ ታድሏል !!

🔹ወደ አላህ በሚደረገው ዳዕዋ ፣ እንዲሁም ከሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት መቸ ነው የምንለዝበው ፣ መቸ ነው የምንጠነክረው?  ፈዲለቲ አሽሸይኽ ዶክተር ረቢዕ ብን ሃዲ ኡመይር አልመድኸሊ - ሀፊዞሁሏህ - መልስ:- የዳዕዋ መሰረቱ ለዘብታ ፣ እዝነት ፣ ጥበብ ነው። ይህ ነው መሰረቱ። ስለዚህ - ባረከሏሁ ፊክ - የሚቃወም ታገኛለህ ፣ ሀቅን የማይቀበል ፣በእርሱ ላይ ሁጃ ታቆማለህ (መረጃውን ታደርሳለህ)፣  ይቃወማል ፣ በዚህ ጊዜ ረድ ትጠቀማለህ (ምላሽ ትሰጣለህ)፣ ባለስልጣን ከሆንክ ይህ በሰይፍ ስርአት ለማስያዝ ቀስቃሽ ይሆናል። ብልሹነትን በማሰራጨት የሚዘወትር ከሆነ ወደ መገደል ይደረሳል። ከተለያየ መዝሀብ የዚህ ብልሹነት ከሽፍታ የከበደ ነው የሚል እይታ ያላቸው ኡለሞች አሉ። ይህ ይመከራል ፣ ሁጃ ይቆምለታል (ማስረጃው እንዲደርሰው ይደረጋል)። እምቢ ካለ ፣  የሸሪአ ዳኛ ወደ ቅጣት ይሄዳል። (ቅጣቱ) በእስር ሊሆን ይችላል። ከአገር በማባረር ሊሆን ይችላል። በመግደል ሊሆን ይችላል። በጀህም ብን ሶፍዋን ፣ በሌላውም ላይ ፣ በቢሽር አልሚሪሲ - ባረከሏሁ ፊክ - በሌሎችም ላይ - ባረከሏሁ ፊክ - ሞት ነው የወሰኑት። ከእነርሱ መካከል ጀዕድ ብን ዲርሀም ይገኝበታል።  ይህ የኡለሞች ብይን ነው ፣ በእምቢተኛ ላይ ቢድዓውን ዘወትር በሚያሰራጨት  ላይ ፣ አላህ ጠቅሞት ከተመለሰ ይህ ተፈላጊ ነው። (الحث على المودة والإأتلاغ) https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
إظهار الكل...
متى نستعمل اللين ومتى نستعمل الشدة في الدعوة إلى الله وفي المعاملات مع الناس؟ فضيلة الشيخ الدكتور ربيع بن هادي عمير المدخلي حفظه الله الجواب : الأصل في الدعوة اللين والرفق والحكمة، هذا الأصل فيها، فإذا -بارك الله فيك- وجدت من يعاند ولا يقبل الحق وتقيم عليه الحجة ويرفض حينئذٍ تستخدم الرد، وإن كنت سلطانا وهذا داعية فتأدبه بالسيف، وقد يؤدي إلى القتل إذا كان يصر على نشر الفساد، فهناك من العلماء من شتى المذاهب يرون أن هذا أشد فسادا من قطاع الطرق، فهذا يُنصح ثم تقام عليه الحجة، فإن أبى فحينئذٍ يلجأ الحاكم الشرعي إلى عقوبته، قد يكون بالسجن، قد يكون بالنفي قد يكون بالقتل، وقد حكموا على الجهم بن صفوان وعلى غيره وعلى بشر المريسي وعلى -بارك الله فيك- غيرهم- بارك الله فيك- بالقتل، منهم الجعد بن درهم، وهذا حكم العلماء على من يعاند ويصر على نشر بدعته، وإذا نفعه الله وتراجع فهذا هو المطلوب. [الحث على المودة والائتلاف]
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.