cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የደሴ አዝሐር መስጅድ ሰለፍይ ወጣቶች ቻናል

http://t.me/Azharmesgiddessie 👉➯➯🔊 አላማችን በአካባቢያችንም ሆነ በመላዉ ሀገራችን ተዉሂድና ሱናን ማስተማርና ዳዓወቱ ሰለፊያን ማሰራጨት ሽርክና ቢድዓን በቻልነዉ አቅም መዋጋት ነዉ 🔊🚦 ጀመዓዉን ማገዝ ለምትፈልጉ የባንክ አካዉንት 1000632376344/ የኢት ንግድ ባንክ / ለአስተያየት 👉 @Azharmesjidbot https://t.me/Azhargroup1

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
207
المشتركون
-124 ساعات
-27 أيام
-430 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የወለድ አደጋዎች ~ ዘመናችን በርካታ የቂያማ ምልክቶች የሚታዩበት አስፈሪ ዘመን ነው። ከነዚህ ምልክቶች ውስጥ አንዱ የወለድ መንሰራፋት ነው። ወለድ በቁርኣን፣ በሐዲሥና በምሁራን ኢጅማዕ የተወገዘ እጅግ አደገኛ ወንጀል ነው። ወንጀሉ ምንም እንኳን አደገኛ ቢሆንም ነገር ግን እንደ ሰደድ እሳት እየተስፋፋ ነው። ከጥፋቱ መስፋፋት በላይ ይበልጥ የሚያሳስበው በተለያዩ ስልቶች የሐላል ቀሚስ ሊያለብሱት አጉል የሚባዝኑ አካላት መኖራቸው ነው። የወለድን ጥፋት ማቃለል በእሳት መጫወት ነው። ለምን? 1. ወለድ ከሰባት ከባባድ ወንጀሎች ውስጥ አንዱ ነው። ነብዩ ﷺ “ሰባት አጥፊዎችን ተጠንቀቁ” ይላሉ። “ምን ምን ናቸው እነሱ?” ሲባሉ፡- (الشرك بالله، والسحر، وقتل النفس التي حرّم اللَّهُ إلا بالحق، وأكل الربا، وأكل مال اليتيم، والتّولّي يوم الزّحف، وقذف المحصنات الغافلات المؤمنات) “በአላህ ማጋራት፣ ድግምት፣ አላህ ጥብቅ ያደረጋት ነፍስ መግደል - በሐቅ ካልሆነ በስተቀር፣ ወለድን መብላት፣ የየቲምን ገንዘብ መብላት፣ በጦርነት ጊዜ መሸሽ፣ ጥብቅና (ከጥፋት) የዘነጉ አማኝ ሴቶችን በዝሙት መወንጀል።” [አቡኻሪይና ሙስሊም] ወለድ ከምን አይነት ወንጀሎች ጋር እንደተቆጠረ ተመልከቱ። 2. ወለድ እንኳን ለአኺራ ለዱንያም አይጠቅምም። ይሄውና አላህ ምን እንደሚል፡- {يَمْحَقُ اللَّهُ الرِّبا وَيُرْبِي الصَّدَقَاتِ} “አላህ አራጣን ያጠፋል። ምፅዋቶችንም ያስፋፋል።” [በቀራህ፡ 276] በየገጠሩ ገበሬውን ባዶውን ያስቀሩት የቁጠባ ተቋማት ናቸው። የወለድ ብድር ውስጥ ገብቶ እንስሶቹ እያለቁ፣ ሰብሉ እየጠፋ፣ ንግዱ እየከሰረ መቀመቅ የገባው እጅግ በርካታ ህዝብ ነው። ወላሂ በአራቱም የሃገሪቱ አቅጣጫዎች የወጣ ከዚህ ጋር የተያያዘ ብዙ ለቅሶ ይሰማል። መሬት ላይ ያለው እውነት በቲቪ እንደሚደሰኮረው አይደለም። ነብዩ ﷺ “አንድ ሰው ከወለድ አያበዛም ፍፃሜው መመናመን ቢሆን እንጂ” ይላሉ። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5/120] 3. ያለ አስገዳጅ ሁኔታ ከወለድ ጋር የሚነካካ በሁሉም አቅጣጫ የተረገመ ነው። ጃቢር ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- ((لعن رسول الله - صلى الله عليه وسلم -: آكل الربا، وموكله، وكاتبه، وشاهديه))، وقال: ((هم سواء)) “የአላህ መልእክተኛ ﷺ ወለድ የሚበላንም፣ የሚያበላውንም፣ ፀሐፊውንም፣ ምስክሮቹንም ተራግመዋል። ‘ሁሉም በወንጀሉ እኩል ናቸው!’ ብለዋል።” [ሙስሊም፡ 1598] “እኔ ቢቸግረኝ ወሰድኩ እንጂ አራጣ አበዳሪ አይደለሁም” ብለህ እንዳትሸወድ። ያለፈውን ሐዲሥ ተመልከት። በተጨማሪም ነብዩ ﷺ “ወሳጅም ሰጪም እኩል ናቸው” ማለታቸውን ያዝ። [ሙስሊም፡ 1584] ስለዚህ ሙስሊም የሆነ ሰው ሌላው ቀርቶ በወለድ ተቋማት ውስጥ ጥበቃና ፅዳት እንኳን ሊሰራ አይገባውም። 4. ወለድ ውስጥ የገባ ሰው ከአላህ ጋር ጦርነት ውስጥ ነው የገባው። አላህ እንዲህ ይላል፡- {يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَذَرُوا مَا بَقِيَ مِنَ الرِّبا إِنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ * فَإِنْ لَمْ تَفْعَلُوا فَأْذَنُوا بِحَرْبٍ مِنَ اللَّهِ وَرَسُولِهِ} “እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ። ከአራጣም የቀረውን ተው። አማኞች እንደሆናችሁ (ተጠንቀቁ።) (የታዘዛችሁትን) ባትሰሩም ከአላህና ከመልእክተኛው በሆነች ጦር (መወጋታችሁን) እወቁ።” [አልበቀራ፡ 278-279] ይቺ በነብዩ ﷺ ላይ መጨረሻ ላይ የወረደች አንቀፅ ነች ይላሉ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ። [አቡኻሪይ፡ 2086] 5. ወለድ የሚበላ ሰው ከቀብር የሚነሳው ልክ በጂን እንደተለከፈ ሰው እየተሳከረ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፡- {الَّذِينَ يَأْكُلُونَ الرِّبَا لا يَقُومُونَ إِلَّا كَمَا يَقُومُ الَّذِي يَتَخَبَّطُهُ الشَّيْطَانُ مِنَ الْمَسِّ} “እነዚያ አራጣን የሚበሉ ያ ሰይጣን ከመንካቱ የተነሳ የሚጥለው ሰው (ከአውድቁ) እንደሚነሳ ብጤ እንጂ (ከመቃብራቸው) አይነሱም።” [አልበቀራ፡ 275] 6. ወለድ ምህረት የለሸ ወንጀል ነው። ነብዩ ﷺ “ምህረት ከማያገኙ ወንጀሎች ተጠንቀቅ። … ወለድን መብላት። ወለድን የበላ ሰው በቂያማ ቀን ሸይጧን የሚጥለው እብድ ሆኖ ነው የሚነሳው” ካሉ በኋላ የላይኛውን አንቀፅ አነበቡ። ስለዚህ ትክክለኛ ተውበት ካልኖነረ ጥፋቱ አደገኛ ነው። 7. ወለድ የከሃዲዎቹ አይሁ.ዳውያን ተግባር ነው። አላህ እንዲህ ይላል፡- {وَأَخْذِهِمُ الرِّبا وَقَدْ نُهُوا عَنْهُ وَأَكْلِهِمْ أَمْوَالَ النَّاسِ بِالْبَاطِلِ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ مِنْهُمْ عَذَاباً أَلِيماً} “ከርሱ በቁርጥ የተከለከሉ ሲሆኑ አራጣንም በመያዛቸውና የሰዎችን ገንዘቦች ያለ አግባብ በመብላታቸውም ሳቢያ (የተፈቀደላቸውን እርም አደረግንባቸው።) ከነሱም ለከሃ .ዲዎቹ አሳማሚን ቅጣት አዘጋጀን።” [አኒሳእ፡ 161] 8. የወለድ መብዛት የቂያማ ምልክት ነው። ነብዩ ﷺ “ቂያማ ሲቃረብ ወለድ፣ ዝሙት እና አስካሪ መጠጥ ይበዛል” ይላሉ። [ሶሒሑ ተርጊብ ወተርሂብ፡ 1861] 9. ወለድ የሚበላ ሰው አሰቃቂ ስቃይ አለበት። ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- “ዛሬ ሌሊት ሁለት ሰዎችን አየሁኝ። ወደተቀደሰች ምድርም ይዘውኝ ወጡ። ደም የሚጎርፍበት ወንዝ እስከምንደርስም ተጓዝን። በውስጡ አንድ የቆመ ሰው አለ። ከወንዙ ዳርቻ አንድ ሰው አለ። ከፊት ለፊቱ ድንጋዮች አሉ። ወንዙ ውስጥ ያለው ሰውየ ሊወጣ ሲያመራ ዳር ላይ ያለው ሰውየ አፍ አፉን በድንጋይ እየመታ ወደነበረበት ይመልሰዋል። ሊወጣ በሞከረ ቁጥር ድንጋይ እየወረወረ አፍ አፉን ይመታዋል። ከዚያም ወደነበረበት ይመለሳል። ‘ማነው ይሄ ወንዙ ውስጥ ያየሁት?’ ስል ‘ወለድ የሚበላ ነው’ ይለኛል።” [አቡኻሪይ፡ 2085] 10. ወለድ ከምናስበው በላይ እጅግ የገዘፈ ወንጀል ነው። ነብዩ ﷺ “ወለድ ሰባ ሶስት አይነት ነው። ከነዚህ ውስጥ ቀላሉ አንድ ሰው እናቱ ላይ ዝሙት እንደመስራት ነው” ይላሉ። [ሶሒሑ ተርጊብ ወተርሂብ፡ 1851] 11. የወለድ መብዛት በምድር ላይ የአላህን ቅጣት ያስከትላል። ነብዩ ﷺ “ዝሙትና ወለድ በአንድ ሃገር ላይ ከበዛ በራሳቸው ላይ የአላህን ቅጣት አስወስነዋል” ይላሉ። [ሶሒሑ ተርጊብ ተርሂብ፡ 1859] ወንድሜ! አላህን ፍራ! እህቴ ሆይ! አላህን ፍሪ! ህይወት ማለት የዱንያ ህይወት ማለት አይደለም። ይቺማ ጤዛ'ኮ ናት። ይልቅ ነብዩ ﷺ ምን እንደሚሉ ተመልከት፡- “አንድ ሰው የሚያገኘው ገንዘብ ከሐላል ይሁን ከሐራም ደንታ የማይኖርበት ዘመን በሰዎች ላይ ይመጣል።” [አቡኻሪይ፡ 2059] ልብህ ካልሞተ ይሄ አስፈሪ መልእክት አለው። ሰው እንዴት ራሱን የቂያማ ምልክት ያደርጋል?! ፍጥጥ ባለ መልኩ ሐራም ላይ መግባት ሲኖርስ? ያውም በአራጣ? አላህ ለሸሪዐዊ ትእዛዝ እጅ የምንሰጥ፣ ከዱንያ ይልቅ ኣኺራን የምናስቀድም ያድርገን። ኣሚን። = (ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 23/2010) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

የሽንት ቤት አጠቃቀም ስነ ስርኣት ~ ① እንዳይሰረቁ ወይም እንዳይጠፋ ካልሰጉ በስተቀር የአላህ ስም ያለበት ነገር ይዞ ሽንት ቤት ውስጥ አለመግባት። ② የሚፀዳዱት ሜዳ ላይ ከሆነ ከሰው እይታ ራቅ/ ሰወር ማለት። [ሶሒሕ ኢብኒ ማጃህ: 1/ 60] ③ በሰው መተላለፊያ መንገድ ላይ ወይ አጠገብ፣ ሰዎች ከሚጠለሉበት ዛፍ ስር፣ ፍሬው ከሚበላ ዛፍ ስር፣ የፍራፍሬ ዛፍና አትክልቶች አጠገብ፣ ወራጅ ባልሆነ ውሃ ላይ፣ የውሃ ምንጭ ላይ፣ መቃብር ውስጥ አለመፀዳዳት። [ኢርዋኡል ገሊል: 1/100] [ሙስሊም: 269፣ 281] [ኢርዋእ: 1/102] ④ ንፋስ ወደሚነፍስበት አቅጣጫ ዙሮ አለመፀዳዳት። ⑤ የተሰነጠቀ መሬት ላይ ወይም ቀዳዳዎች ላይ አለመፀዳዳት። [አቡ ዳውድ: 29] ⑥ ውጭ ላይ የሚፀዳዱ ከሆነ ወደ መሬት ዝቅ እስከሚሉ ልብስን አለመሰብሰብ ወይም አለማውረድ። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 4652] ⑦ ውጭ ላይ በሚፀዳዱ ጊዜ ወደ ቂብላ አለመዞር፣ ጀርባንም ለቂብላ አለመስጠት። ሽንት ቤት ውስጥ ከሆነ ወይም ከፊት የሚጋርድ (ግድግዳና መሰል) ነገር ከኖረ ችግር የለውም። ይህንንም ቢሆን ከተቻለ መጠንቀቅ። [አልቡኻሪይ እና ሙስሊም] [ኢርዋእ: ቁ· 61] ⑧ ሽንት ቤት ሲገቡ ግራ እግርን ማስቀደም። ⑨ ሽንት ቤት ሲገቡ "ቢስሚላህ። አላሁመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚነል ኹቡሢ ወልኸባኢሥ" ብሎ ከሸይጧን መጠበቂያ ዱዓ ማድረግ። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 3611] [አልቡኻሪይ እና ሙስሊም] (10) በሚፀዳዱ ጊዜ ብልትን በቀኝ እጅ አለመንካት፣ በቀኝ እጅ አለመፀዳዳት። [አልቡኻሪይ እና ሙስሊም] (11) በሚፀዳዱበት ጊዜ ያለ ምክንያት ከማውራት መቆጠብ። (12) ቢያንስ በሶስት ድንጋይ፣ ሶፍት፣ ወረቀትና መሰል ነገር መፀዳዳት። አንድም ቢሆን ሶስት የተለያዩ ጎኖች ወይም ገፆች ከኖሩትም በቂ ሊሆን ይችላል። ወይም በውሃ መጠቀም። አጥንት፣ ፋንዲያ፣ ምግብ ነክ ነገር እና ንፁህ ያልሆነ ነገር ለመፀዳጃነት አይውልም። [ሙስሊም፡ 262፣ 263፣ 271] (12) ከሽንት ቤት ሲወጡ ቀኝ እግርን አስቀድሞ መውጣት። (13) ከሽንት ቤት ሲወጡ "ጉፍራነክ" ማለት። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 4707] = (ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 23/2010) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

የሞኝ ቀልድ አትቀልድ! ~ በጩቤ፣ በዱላ፣ በመጥረቢያ፣ በመኪና፣ በጦር፣ በጠመንጃ፣ በሰይፍ፣ … ሰዎች ለማስደንገጥ ከመቀለድ፣ ከመቃጣት ተጠንቀቅ። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:– من أشار إلى أخيه بحديدة فإن الملائكة تلعنه حتى ينتهي. "ወደ ወንድሙ በመሳሪያ የጠቆመ እስከሚታቀብ ድረስ መላእክት ይረግሙታል።" [ሙስሊም] በሌላም ሐዲሥ እንዲህ ብለዋል:– لا يحل لمسلم أن يروع مسلماً. "ሙስሊም ሙስሊምን ሊያስደነግጥ አይፈቀድለትም።" አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ:– "አንድ ሰው የምሩንም ይሁን በቀልድ ወደ ወንድሙ ጠመንጃ ሊያዞር አይፈቀድለትም። መኪናም እንዲሁ (አይፈቀድም)። የከፋ ነውና።" [ሸርሑ ሶሒሒል ቡኻሪ: 9/ 502] = (ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 30/2010) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

"ፈገግ በሉ" በሚለው👇 "አቡ ነዋስ" የሚባል የታወቀ ገጣሚ ነበር። በጊዜው የነበረው አሚር ያስጠራውና አሚሩ "የፃፍኳትን ግጥም ገምግምልኝ" ብሎ ግጥሙን አነበበለት። አቡ ነዋስ የአሚሩ ግጥም ከሰማ በኀላ "ምንም ዓይነት የግጥም ሽታም የለውም" አለው። አሚሩ ተናዶ "ውሰዱና በአህያዎች በረት ለ1 ወር እሰሩት" አላቸው። ከወር በኋላ "መልሳችሁ አምጡት" አላቸውና ድጋሚ ሌላ ግጥም አነበበለት። ልክ አንብቦ ሲጨርስ አቡ ነዋስ ሊወጣ ተነሳ። አሚሩ አስቆመውና "የት ልቴድ ነው?" ሲለው 👇👇👇👇 "ወደ አህዮቹ በረት" ❕
إظهار الكل...
አይባልም! ~ "ስንት ወንዶች አሉ - በየወንዛ ወንዙ እንደጥቅምት ማር - የተንቆረዘዙ እንደወለዱት ልጅ - አላህን የሚያዙ።" . ያሻቸውን ቢጠይቁት አላህ ዱዓቸውን ይሰማቸዋል ማለታቸው ነው። ግን ከአደብ የራቀ ነውረኛ ንግግር ነው። አላህን እንደፈለጉ በሚያሽከረክሩት ልጃቸው እየመሰሉት ነው ያሉት። ከአላህ ጋር በተያያዘ የምንጠቀማቸው ቃላት በአደብ የተሞሉ ሊሆኑ ይገባል። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ሐዲሦችን ሐፍዘዋል። 5ሺ አካባቢ የሚሆኑ የደዕዋና የፈትዋ ካሴቶችን አበርክተዋል። ከመቶ የሚበልጡ በሐዲሥ ጥናት ላይ ብቻ ያተኮሩ ኪታቦችን ፅፈዋል። እንዲሁም በሌሎች ኢስላማዊ የእውቀት ዘርፎችም የተፃፉ እጅግ ውድና በርካታ ድርሳናትን ለኡማው አበርክተዋል። በዓለም-አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆኑ ተማሪዎችን አፍርተዋል። የነቢዩን ﷺ ሐዲሦችን ደረጃ በማጣራትና በመልእክተኛው ስም የሚወሩ መሰረተ-ቢስና ደካማ “ሐዲሦችን” አበጥሮ በማውጣት ለኡማው ባደረጉት ታላቅ አስተዋፅኦ ኢስላምን ላቅ ባለ ሁኔታ ላገለገሉ ምሁራን የሚበረከተውን አለም አቀፉን የንጉስ ፈይሰል ሽልማት በ1419 ዓመተ-ሂጀራ (1999 እ.ኢ.አ) ተሸላሚ ሆነዋል። ባጠቃላይ ሸይኹ በተለይም በሙስጦለሐል ሐዲሥ (የሐዲሥ ጥናት) ዘርፍ ሑጃ ናቸው ይላሉ ዓሊሞች። በመጨረሻም ጁማደሣኒያ 1419 ዓመተ-ሂጅራ (እ.ኢ.አ. ኦክቶበር 1999) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ረሒመሁላህ ረሕመተን ዋሲዓህ። ስለ ሸይኹልአልባኒ ታላላቅ ዓሊሞች ምን ብለዋል? ጥቂት ብቻ ልጥቀስ:- 1. ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ ብኑ ባዝ ረሒመሁላህ (የቀድሞው የሰዑዲያ ጠቅላይ ሙፍቲ)፡- “በዚህ ዘመን ከሰማይ በታች እንደታላቁ ዓሊም ሙሐመድ ናሲሩዲን አልአልባኒይ ሐዲሥን የተገነዘበ ሰው አላውቅም።” በአንድ ወቅት ሸይኽ ኢብኑ ባዝ፡ “ረሱል ﷺ በሐዲሣቸው በየመቶ ዓመቱ ለዚህ ኡማ አላህ ዲኑን የሚያድስለት እንደሚልክለት ተናግረዋል። በዘመናችን ይሄ ሙጀዲድ (የተሀድሶ አራማጅ) ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር። ምላሻቸው፡ "እንደኔ እይታ የዚህ ዘመን ሙጀዲድ ሸይኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አልአልባኒ ነው፣ ወላሁ አዕለም” የሚል ነበር። 2. ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ሷሊህ አልዑሠይሚይን ረሒመሁላህ፡- “አልአልባኒ ከአህለሱና ነው ለሱና ዘብ የቆመ። በሐዲሥም ኢማም ነው። በዘመናችን ከሱ ጋር የሚነፀፀር አንድም አናውቅም።” “የተገናኘነው ለጥቂት ጊዜ ቢሆንም በተገናኘንበት አጋጣሚ ያስተዋልኩት በዐቂዳም በተግባርም ሱናን ለመተግበርና ቢድዐን ለመዋጋት ወደ ኋላ የማይል እንደሆነ ነው። ሰውየው በዘገባም ይሁን በግንዛቤ እጅግ የገዘፈ ዕውቀት ባለቤት ሲሆን በዒልሙም በመንሀጁም ወደ ሐዲሥ ዒልም ሰዎችን በማዞርም የላቀው አላህ በርካቶችን ጠቅሞበታል። ይህ ለሙስሊሞች ትልቅ ስኬት ነው።” 3. ሸይኽ ሙቅቢል ብኑ ሃዲ አልዋዲዒይ ረሒመሁላህ (የየመን ሀገር ሙሐዲሥ)፡- “ዛሬም በሸይኹልአልባኒይ ኪታቦች ትግላችንን አጠናክረን ቀጥለናል።” “ስለ ሸይኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አልአልባኒ አላህ ይጠብቀውና በተደጋጋሚ ተጠይቄያለሁ። በርካታ ሰለፎች ከነሱ ስለሚበልጥ ሰው ሲጠየቁ ይሉ የነበረውን ነው የምለው። 'እኔ ነኝ ስለሱ የምጠየቀው? ወይስ እሱ ነው ስለኔ የሚጠየቀው?!' ችግሩ ያለንበት ዘመን በርካቶች ዓሊምና ጠንቋይ ሙእሚንንና ከ.ሀዲ ሶሻሊስትን የማይለዩበት ዘመን ነው።… አህለሱና ያልሆኑ ሰዎች እንጂ በሸይኹልአልባኒይ እውቀት ማንም አይጠራጠርም። እኔ የማምነው ሸይኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አልአልባኒይ ‘አላህ በየመቶ ዓመቱ ለኡማው ዲኑን የሚያድስለት ይልካል' የሚለው ሐዲሥ ከሚያረጋግጣቸው ሙጀዲዶች እንደሆነ ነው።” 4. ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ ኣሊሸይኽ (የአሁኑ የሰዑዲያ ጠቅላይ ሙፍቲ)፡- “ሸይኹልአልባኒይ ሐዲሥን በተግባር የሚወድ ለሐዲሥ ጥናት ጥበቃና እንክብካቤ የሚያደርግ ታማኝ የሸሪዐ ምንጭ የሆነ ቅርብ ወንድማችን ነው።” = (ኢብኑ ሙነወር፣ 2001) የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ታላቁ የሐዲሥ ፈርጥ ከአውሮፓዊቷ አልባኒያ ምድር ~ የዘመናቸው ምሁራን አላህ በየክፍለ ዘመኑ ዲኑን እንዲያድሱ ከሚልካቸው የለውጥ ሰዎች አንዱ እንደሆኑ ያምናሉ። በሐዲሡም በፊቅሁም መስክ የነጠረ እውቀት ያካበቱ ለመሆናቸው ሁለት ሚዛናዊ ሰዎች አይወዛገቡባቸውም፣ ሸይኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አል አልባኒይ ረሒመሁላህ። ሸይኹል አልባኒይ በ1332 ዓመተ ሂጅሪያ (1914 እ.ኢ.አ) በጊዜው የአልባኒያ ዋና ከተማ በነበረችው አሽቆድራ ተወለዱ። ቤተሰባቸው ድሃ ግን ኢስላማዊ ድባብ ያከበረው ነበር። አባታቸው ሐጂ ኑሕ ከኢስታንቡል የሸሪዐ ተቋም የተመረቁ ሲሆኑ በአካባቢያቸው እውቅ የሐነፊያ መዝሀብ አስተማሪ ነበሩ። በአልባኒህ የልጅነት ዘመን ሀገራቸው አልባኒያ አሳዛኝ በሆነ ታሪካዊ ቀውስ ውስጥ ወደቀች። በጊዜው የሀገሪቱ መሪ የነበረው አህመድ ዛጉ ሀገሪቱን መርዛማ ዝገት አለበሳት። ሀገሪቱ ፅንፈኛና ለኢስላም ጥላቻን የደቀነ ምእራብ-ወለዱን የክህ .ደት ስርዓት/ሴኩላሪዝም የሀገሪቱ ስርዓት አድርጎ አወጀ። የዚህን ጊዜ ነበር የአልባኒይ አባት ሐጂ ኑሕ ከነቤተሰባቸው ኩፍርን ሸሽተው ሂጅራ ያደረጉት፣ እትብታቸው ከተቀበረበት አልባኒያ ወደ ደማስቆ ሶሪያ። ለአላህ ሲባል የተከፈለ ታላቅ መስዋእትነት! አልባኒይ ይሄንን የአባታቸውን ውለታ እንዲህ ሲሉ ደጋግመው ያነሱት ነበር። “ጌታዬ በኔ ላይ የዋለውን ፀጋ ቆጥሬ አልዘለቀውም። ምናልባትም ከዋለልኝ ፀጋዎች ሁሉ ትልልቆቹ የአባቴ ወደ ሻም መሰደድና የሰዓት ጥገና ሙያውንም ለኔ ማስተማሩ ነው።” ሸይኹል አልባኒይ በደማስቆ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በከፍተኛ ውጤት ቢያጠናቅቁም መደበኛው ትምህርት የአባታቸው ፍላጎት አልነበረምና ሳይገፉበት ቀርተዋል። ይሁን እንጂ በቁርኣን፣ በተጅዊድ፣ በነሕውና ሶርፍ እንዲሁም ፊቅህ በሐነፍያ መዝሀብ አጠናክረው ቀጠሉ። ቁርኣንን ካባታቸው ላይ የሐፈዙት ሸይኹልአልባኒይ የሰዓት ጥገና ሙያንም በሚገባ ቀስመዋል። በሙያውም ታዋቂ ከመሆናቸውም በላይ እየጨመረ ለመጣው ዲናዊ ትጋታቸው ጊዜ እንዲኖራቸው አስችሏቸዋል። የሐነፊያን መዝሀብ አጥብቀው የሚከተሉትና ከሱ ውጭ ግራ ቀኝ ማየት የማይፈልጉት የአልባኒይ አባት ልጃቸውም በዚሁ ፈለግ እንዲጓዝ ካላቸው ፍላጎት የተነሳ በሐዲሥ ጥናት ላይ እንዳይሰማሩ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ነበር። ይሁን እንጂ የአንድን መዘሀብ ጭፍን ተከታይነት በፅኑ ለሚያወግዙት አልባኒይ ይሄ ነገር ፈፅሞ የሚዋጥላቸው አልሆነም። ገና በሀያ ዐመታቸው አካባቢ ነበር የሐዲሥ ጥናታቸውን አፋፍመው የጀመሩት። ለጥናታቸው አጋዥ የሆኑ ኪታቦችን አቅማቸው በፈቀደ እየገዙ ከዚህ ባለፈም ደማስቆ ከሚገኘው “አዟሂሪያ” ቤተ መጻህፍት እየተዋሱ ይጠቀሙ ነበር። በጥናታቸው በገፉ ቁጥር ሱቃቸውን እየዘጉ ሰፊ ጊዜያቸውን በቤተ መጻህፍቱ ማሳለፉን ተያያዙት። ትጋታቸውን ያስተዋሉት የቤተ መጻህፍቱ ሀላፊዎችም ባሰኛቸው ጊዜ መጠቀም ይችሉ ዘንድ አንድ ልዩ ክፍልና የቤተ መጻህፍቱን ቁልፍ በማስረከብ ለሸይኹ ብቻ ሳይሆን ለሙስሊሙ ዐለም ባጠቃላይ ትልቅ ውለታን ጥለው አልፈዋል። ከዚህ በኋላ አልባኒይ ከሶላት ውጭ ከማለዳ እስከ ዒሻ በኋላ ቤተ መጻህፍቱን ቤታቸው አደረጉት። ጥናታቸውን አጠናክረው የቀጠሉት ሸይኹልአልባኒይ የኋላ ኋላ በሐዲሥ ጥናት መስክ ብቻ ከመቶ በላይ ኪታቦችን ለኡማው አበርክተዋል። በዘርፉ ከተሰማሩ ሌሎች ዐሊሞች ጋር ሲታዩ ሸይኹል አልባኒይ ጫፍ የደረሱ ነበሩ ማለት ይቻላል። እንዲያውም ዐሊሞች “የነኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላኒን፣ ኢብኑ ከሢርንና የሌሎችንም ሙሐዲሦች ዘመን እንደ አዲስ አመጣው” ሲሉ አወድሰዋቸዋል። የተውሒድና የሱናን ባንዲራ ሶሪያ ምድር ላይ ቀላል ለማይባል ጊዜ ያውለበለቡት ሸይኹል አልባኒይ ከተቀናቃኞቻቸው ጋር በዐቂዳ፣ በኢቲባዕ (ረሱልን ﷺ በመከተል)፣ በመዝሀብ ጭፍን ተከታይነትና በቢድዐ ዙሪያ በርካታ ውይይቶችን አድርገዋል። በሂደቱም በመዝሀብ ጭፍን ተከታዮችና በሱፊያ ሸይኾች ቀስቃሽነት ብዙ ፈተና ደርሶባቸዋል። በተመሳሳይ ጊዜ ደማስቆ ውስጥ ከሚገኙ ስመ ጥር ዓሊሞች በአቋማቸው እንዲገፉ ያላሰለሰ ማበረታቻ ከጎናቸው ነበር። ትግላቸውን አጠናክረው የዩኒቨርሲቲ አስተማሪዎች ጭምር የሚካፈሉበት ደርስ እንዲሁም ወደተለያዩ የሶሪያና የዮርዳኖስ ከተሞች እየተዘዋወሩ ወርሃዊ ደዕዋ ማድረግ ቀጠሉ። ኳታር፣ ግብጽ፣ ኩዌት፣ ዐረብ ኢማራት፣ አውስትራሊያ፣ እንግሊዝና ስፔን በተለያዩ ጊዜያት ለደዕዋ ከተጓዙባቸው ሃገራት ውስጥ ናቸው። ስራዎቻቸው ለህትመት ከበቁ ስማቸው በሰፊው ከታወቀ በኋላ በዝነኛው የመዲና ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ ሆነው ተመርጠው ለሶስት ዓመታት አገልግለዋል። ከዚህ በኋላ ሱቃቸውን ለአንድ ወንድማቸው በመተው ሙሉ ለሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ጥንታዊው የ“አዟሂሪያ” መክተባ ተመለሱ። ኢማሙል አልባኒይ ምንም እንኳ ከፖለቲካ የራቁ ቢሆኑም በተለያዩ ጊዜያት መንግስት በዐይነ ቁራኛ ይከታተላቸው ነበር። ሁለት ጊዜም ለእስራት ተዳርገዋል። በሁለተኛ እስራታቸው ከታላላቅ ዐሊሞች ጋር የተገናኙ ሲሆን በእስራት ላይ እያሉም የሙንዚሪን “ሙኽተሶሩ ሶሒሕ ሙስሊም ‘ተሕቂቅ' አድርገዋል። ለሐቅ ባላቸው ፅኑ አቋምና ለለውጥ ባላቸው የማይታጠፍ ተጋድሎ የሚታወቁት ሸይኹል አልባኒይ ውጫዊ የአመለካከት ወረራዎችን ብቻ ሳይሆን የኢስላምን ውበት ያደበዘዙ ውስጣዊ ወረራዎችንም በመዋጋት ፋና ወጊ ነበሩ። አልባኒይ ለተስፊያና ተርቢያ ማለትም ኢስላምን ከቢድዐ፣ ከሺርኪያት፣ ከደካማ ማስረጃዎችና ሰርጎ-ገብ አመለካከቶች ማፅዳት እንዲሁም ትውልድን ቁርኣንና ሶሒሕ ሱና ላይ በተመሰረተው ንፁሁ ኢስላም ላይ ኮትኩቶ የማውጣት አካሄድ ልዩ ትኩረት ይሰጡ ነበር። ከግማሽ ክፍለ-ዘመን በላይ የተጓዙበትን ይህን አካሄዳቸውን በርካቶች እንዲያጤኑበትና እንዲሄዱበት ያላሰለሰ ጥረት አድርገዋል። ለኡማው አንድነት እጅግ የሚጨነቁት አልባኒይ ለአንድነት የሚደርገው ጥረት ፍሬ ያፈራ ዘንድ ግን ከባዶ የ”አንድ እንሁን” ጩኸት ባለፈ የግድ ወደ ቁርኣንና ሱና መመለስ እንደሚያስፈልግ በፅኑ ያሳስባሉ። እዚህ ላይ በአንድ ወቅት ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡትን መልስ ብናነሳ አይከፋም። ጥያቄ፡- “ትክክለኛ ነገር ካልያዝን ብለን ከምንበታተን በስህተት ላይ ሆነን ብንሰባሰብ ይሻላል። መክንያቱም ሐቅ ሁሉ ትክክል አይደለምና። እንዲሁም ባጢል (ውድቅ ነገር) ሁሉም ስህተት አይደለምና!” አልባኒይ፡- “ይሄ ምናባዊና ቅዠታዊ ንግግር ነው። በስህተት ላይ ከሆንን መሰባሰባችን ምንድን ነው ፋይዳው? ከፊላችን በስህተት ላይ ከፊላችን ደግሞ በሐቅ ላይ ከሆንን ብንለያይ ምንድን ነው ጉዳቱ? አሸናፊና የላቀው ጌታችን እንዲህ ይላል:- {ከሐቅ በኋላ ጥመት እንጂ ምን አለ?} ሸይኹል አልባኒይ በጠንካራ የሰለፊያ አቋማቸው የተነሳ ብዙ ሰቃይና እንግልት ደርሶባቸዋል። ለኢስላም ሲባል ከአልባኒያ የተጀመረው ስደት ደማስቆን መጨረሻው አላደረገም። በተለያዩ ጫናዎች ምክንያት ከሶሪያ ወደ ዮርዳኖስ፣ ከዮርዳኖስ ዳግም ወደ ሶሪያ፣ ከዚያም ወደ ሊባኖስ፣ ከዚያም ወደ ዐረብ ኢማራት፣ በመጨረሻም ወደ ዮርዳኖስ ዐማን ተንከራተዋል።
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ሰለምቴነት ማሸማቀቂያ አይደለም! ~ አንዳንድ ሰዎች በእምነታዊ ጉዳዮች ላይ ስሜታቸውን ለመከተል፣ ከወረዱበት ለመውረድ ፈቃደኛ ያልሆላቸውን ሙስሊም ወደ ኋላ ታሪኩ በማጠንጠን “አንተ ሰለምቴ አይደለህ? ምን ታውቃለህ?” እያሉ ሊያሸማቅቁ ይጥራሉ። የተለየ አውቀው፣ የተሻሉ ሆነው ሳይሆን እንዲሁ የነሱን ስሜት ተከትሎ ስላላጨበጨበ ብቻ አንድን ሙስሊም በዚህ መልኩ ለማሸማቀቅ መሞከር ጋጠ-ወጥነት ነው። ሰለምቴነት ክብር እንጂ ነውር አይደለም። ሰለምቴነት ገድል እንጂ ማሸማቀቂያ አይደለም። በዚህ ፈተናው በበዛበት፣ የጥፋት ሃይሎች በሚርመሰመሱበት፣ ኢስላምን የሚያጠለሹ አካላት እንደ አሸን በፈሉበት፣ እጅግ ከባባድ ማደናገሪያዎች ያለ ገደብ በሚለቀቁበት ዘመን በምንም ሰበብ ቢሆን ወደ ኢስላም የሚመጡ ሰዎች ሊከበሩ እንጂ ሊነቆሩ አይገባቸውም። ድክመትም ካለባቸው መሸፈ፞ን እንጂ ማጋለጥ አይገባም። ከቻልን ሞራል እንስጥ። ይህን ማድረግ ካቃተን በማሸማቀቅ ገፍተን እንዳናስወጣቸው እንጠንቀቅ። ክርስቲያን ወይም አይሁድ የነበረ ሰውኮ ወደ ኢስላም ቢገባ በእጥፍ እንደሚመነዳ ነብዩ ﷺ ተናግረዋል። [ቡኻሪና ሙስሊም] አልኢማም አልቡኻሪ ረሒመሁላህ በሶሒሐቸው بَابُ فَضْلِ مَنْ أَسْلَمَ مِنْ أَهْلِ الكِتَابَيْنِ የሚል ርእስ እንዳሰፈሩ እናስተውል። ‘ፈድል’ ማለት ልቅና፣ ብልጫ ማለት ነው። ነብያችን ﷺ ለሮማው ንጉስ ሒረቅል በፃፉት ደብዳቤ ላይ ወደ ኢስላም ሲጠሩት ምን ነበር ያሉት? أَسْلِمْ تَسْلَمْ، يُؤْتِكَ اللَّهُ أَجْرَكَ مَرَّتَيْنِ “ስለም። ትድናለህ። አላህ ምንዳህን #ሁለት_ጊዜ ይሰጥሀል።” [ቡኻሪና ሙስሊም] ይሄ መልእክት በሒረቅል ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም። የኢብኑ ሐጀርን ማብራሪያ ይመልከቱ። [ፈትሑል ባሪ፡ 8/221] በነገራችን ላይ አንድ ካ^ፊ^ር ወደ ኢስላም ከገባ ከመስለሙ በፊት ሲፈፅማቸው የነበሩ መልካም ስራዎች ይታሰቡለታል። ሐኪም ብኑ ሒዛም ረዲየላሁ ዐንሁ “በዘመነ ጃ^ሂሊያ ስፈፅማቸው ስለነበሩት ዒባዳዎች፤ ሶደቃ፣ ባሪያ ነፃ ማውጣት፣ ዝምድናን መቀጠል በተመለከተ ንገረኝ እስኪ። ምንዳ ይኖራቸዋልን?” ብለው ነብዩን ﷺ ቢጠይቁ እንዲህ ብለው ነው የመለሱላቸዋል፡- أَسْلَمْتَ عَلَى مَا أَسْلَفْتَ مِنْ خَيْرٍ “ካሳለፍከው መልካም ስራ ጋር ነው የሰለምከው።” [ሶሒሕ ሙስሊም] ልብ በል! ሐኪም ብኑ ሒዛም ከመካ መኳንንት የነበሩ ሲሆን በድር ላይ ከቁረይሾች ጋር ተሰልፈው ጦርነቱን ተካፍለዋል። አላህ ሲያድላቸው እንደ አጋሪ ጓዶቻቸው በድር ላይ ሳይገደሉ በመትረፋቸው ኋላ ላይ ሰልመዋል። ለዚህም ነበር “የበድር ቀን ከመገደል ባተረፈኝ ጌታ ይሁንብኝ” እያሉ ይምሉ የነበሩት። ወንድሜ ሆይ! 1. እስኪ የነዚያን በጀነት የተመሰከረላቸውን ሶሐብዮች ታሪክ እናንብብ። ከነዚያ ታላላቅ የኢስላም ፈርጦች ውስጥ ቀድሞ ጣኦት አምላኪ የነበሩት'ኮ እጅግ በርካታ ናቸው። 2. እስኪ የነ ዐብደላህ ብኑ ሰላም፣ የነብያችን ﷺ ሚስት ሶፊያን ታሪክ እናገላብጥ። ከነዚያ እንቁ ሶሐብዮች ውስጥ ቀድሞ አይሁድ የነበሩት ብዙ ናቸው። 3. እስኪ የነ ሰልማኑል ፋሪሲ፣ ዐዲይ ብኑ ሓቲምና መሰል ሶሐቦችን ታሪክ እንፈትሽ። አዎ ከነዚያ ወደር የለሽ የኢስላም ጀግኖች ውስጥ ከመስለማቸው በፊት በክርስትና ውስጥ ያለፉ ነበሩ። 4. ከሶሐቦች ጊዜ ወዲህም ታሪክ የሰሩ፣ ለኢስላምና ለሙስሊሞች በዋጋ የማይተመን ውለታን የዋሉ በርካታ ሰለምቴዎች አልፈዋል። ልብ በል ወንድሜ! ልብ በይ እህቴ! ኢስላም መለኮታዊ ሃይማኖት እንጂ የማንም ግላዊ ንብረት አይደለም። ኢስላም ለሰው፣ ለጂኑ ባጠቃላይ የቀረበ አምላካዊ መድህን እንጂ ያሰኘንን የምናስገባበት፤ የደበረንን የምናስወጣበት ያ'ባታችን ግቢ አይደለም። ኢስላም ልክ ቄሶች “ውጉዝ ከመ አሪዮስ!” ብለው እንደሚያባርሩት ሸይኾችም እንዳሻቸው የሚፈርዱበት ቀልደኛ ቀኖና የለውም። ስለዚህ ወንድሜ! እስልምናን ከአባት ከአያት የወረስከው አንተ፣ በኢስላም ላይ ከሰለምቴው የተለየ የባለቤትነት መብት የለህም። ከአላህ ዘንድ ያለህ ደረጃ ከፍ የሚለው በተቅዋህ ብቻ ነው። ለሰለምቴው ኢስላምን የሰጠው የፈጠረው ጌታ እንጂ እኔ ወይም አንተ አይደለንም። እኛ ይህን የጌታ ፀጋ አከፋፋዮች አይደለንም። ምናልባት “በሰለመ በማግስቱ ፈትዋ ካልሰጠሁ ብሎ የሚገላገል ሰለምቴስ ዝም ይባል ወይ?” የሚል ሊኖር ይችላል። ይሄ ሌላ ርእስ ነው። እያወራሁ ያለሁት ሰለምቴነትን ለማነወሪያነት ስለሚጠቀሙ አካላት ነው። የነሱን ስሜት ተከትሎ ስላልፈሰሰ ብቻ “እሱ'ኮ ሰለምቴ ነው?” በማለት ለማንጓጠጥ መሞከር ምን ማለት ነው? እስኪ አስቡት! በሚያጋጥሙ አንዳንድ አለመግባባቶች የተነሳ “እሱ'ኮ መስለሙንም እንጃ!”፣ “እሱ'ኮ የሰለመ ጊዜ ቄሶች በደስታ እንኳን ሄደልን ያሉት ነው”፣ “እሱ'ኮ እንደገና ወደ ክርስትና ሳይመለስ አይቀርም”፣ “እሱ'ኮ ሶላት አይሰግድም"፣ "እሱ'ኮ ውዱእ ሲያደርግ ታይቶ አይታወቅም"፣ "እሱ'ኮ ይሰክራል …” ወዘተ በሚሉ እጅግ ሰቅጣጭና ፀያፍ ውንጀላዎች በሃሰት የሚወ፞ነጀል ሰለምቴ ምን እንደሚሰማው አስቡ። በተጨባጭ የተከሰቱ ሃሰተኛ ውንጀላዎችን ነው በምሳሌነት የጠቀስኩት። ተወንጃዮቹ ልፍስፍስ ቢሆኑ በቀላሉ ወደ ኩ^ፍ^ር ተገፍተው ከኢስላም በሸሹ ነበር። ግና ኢስላም ማለት የነዚህ ዋልጌዎች የግል ንብረት እንዳልሆነ ጠንቅቀው ማወቃቸው በጃቸው። ሰዎቹን ከማወቃቸው በፊት ኢስላምን ማወቃቸው ጠቀማቸው። እንጂ እንደዋዛ አኩርፈው በበረገጉ ነበር። ወላሂ! አንድ ስንት ስራ የሰራ ወንድም ፈፅሞ ይዋሻሉ ብለን በማንገምታቸው ሰዎች በተደጋጋሚ በመወ፞ንጀሉ የተነሳ ብዙ ሰዎች እስልምናውን እስከሚጠራጠሩት የደረሱበት ሁኔታ በተጨባጭ አውቃለሁ። መነሻው ግን የእነዚያ ታማኞች የመሰሉን ሰዎች ክፋት ነበር። በተረፈ ሰለምቴ ሆነው ስንቶችን ቁጭ አድርገው እየገሩ ያሉ ኡስታዞች አሉ?! ሰለምቴ ሆነው ለስንቶች መስለም ሰበብ የሆነ ስራ ላይ በሰፊው የዘመቱ አሉ?! ካረገዙ በኋላ በባሎቻቸው ተከድተው ብዙ ፈተና ቢደርስባቸውም ከነ ችግራቸው በኢስላማቸው ላይ እንደፀኑ ያሉ ስንት ሰለምቴዎች አሉ?! ወንድ ወይም ሴት ተከትለው ስንቶች በሚከ^ፍ^ሩበት ዘመን ለኢስላም ሲሉ ከቤተሰብ የተቆራረጡ፣ ትዳራቸውን የበተኑ ስንት ቆራጥ ሰለምቴዎች አሉ?! ነባር ሙስሊሞች በእርዳታ በቆሎ እምነታቸውን በሚቀይሩበት ምድር ለኢስላም ሲሉ ሁለ ነገራቸውን አጥተው ለእለት ጉርስ የተቸገሩ ስንት ፈተና ያልበገራቸው ሰለምቴዎች አሉ?! ደግሞም አላዋቂ ሰለምቴ እውቀት በሚጠይቁ ጉዳዮች ላይ ያላቅሙ ገብቶ ካገኘን ብቃቱ ካለን በአደብ ማስተማር እንጂ ሰለምቴነቱን ለማሸማቀቂያ መጠቀም፣ ሰለምቴነቱን እንደ ነውር በመቁጠር በየደረሱበት ማማት የለየለት ነውር ነው። መሀይም የሆነ ሰው ሰለምቴም ባይሆን ያላቅሙ እንዲያወራ የተሰጠው የተለየ ፍቃድ ወይም መብት የለውም። ስለዚህ ሰለምቴው በተለየ የሚኮነንበት ምክንያት ምንድነው? ሰለምቴ ሆኖ ከብዙዎቻችን የተሻለ ግንዛቤ ያለው ስንት ሰው አለ? ከውልደት እስከ እርጅና እድሜውን ኢስላም ውስጥ አሳልፎ አሊፍ ትቁም ትጋደም የማያውቅ እልፍ አእላፍ ህዝብስ የለም ወይ? እውቀት'ኮ በመማር እንጂ በውልደት የሚገኝ አይደለም። “ሸንበቆ አስር አመት ውሃ ውስጥ ቢቆይ አዞ አይሆንም” ይባላል። ለውጥ ከአላህ እገዛ ጋር በጥረት እንጂ በምኞትም በጉራም አይገኝም። (ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 01/2012) https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.