cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Warka Times

Warka Times is a multi-platform bi-lingual global online media service where credibility is a priority. We will keep you both informed and entertained. The infotainment presented on WT comes from wide variety of sources. FB 👉fb.com/warkatimesofficial

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
7 741
المشتركون
-1624 ساعات
-377 أيام
-19930 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
ሠላም ! ግንባሬን በጥይት ተመትቼ እንድገደል ቃል በቃል ውሳኔ ከተላለፈ ቆዬ። ይሄም በኢሳት(በተለይ ሲሳይ አጌና ) በመሳይ መኮንን ፤ በዘሀበሻ ፤ በስዩም ተሾመ ፤ በናትናኤል መኮንን በደረጄ ሀብተወልድ ሚዲያዎች በተደጋጋሚ ቀርቧል። ነፃ ውሳኔ ተፈፅሞ እርምጃ እንዲወሰድብን ከተጠየቀ ቆዬ። እናጠፋሃለን የሚለኝ ከቀበሌ እስከ ቤተመንግስት ያለ ሀይል ነበር። ከጠቅላይ ሚኒሰትሩ ቢሮ አዋሽ ከአዋሽ አዲስ አበባ ፖሊስ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ፌዴራል ፖሊስ፤ ከፌዴራል ፖሊስ ቦሌ ፖሊስ ከሬሳ..ከአውሬ ..ከአዕምሮ በሽተኛ ጋር በፀሃይ በውሃ በጨለማ በብርሃን ሁሉ አስረው አስፈራሩኝ። ሀሙስ ትገደላለህ ብለው አርብ ፈቱኝ። የደረሰብኝ ነገር ለመናገር የሚከብድ ነው የሚለው ቃል እራሱ አይገልፀውም። በወገናችን በቤተሰባቸን በእህት ወንድሞቻችን በእናት አባቶቻችን ላይ ከሚደርሰው ጭፍጨፋ መደፈር መገደል መረሸን የከፋ ነው ወይ የሚለወል አቋም የለኝም። አብይ አህመድና ጓደኞች የሚመሩትን ህዝብን አሳዶ የመጨፍጨፍ የፋሽት ፖለቲካ በስራዬ ብቻ ማጋለጥ መተቼት መተንተን ማስተቸት ስራዬ ነበር። ለምን ሙያዬ ስለሚያስገድድኝ ነው። ይህ ቀረሽ ነው የማይባል በደል ተፈፅሞብኛል። ፀጉረ ልውጥ ፣ የቀን ጅብ ፣ ጁንታ ፣ ሼኔ ፣ ነፍጠኛ ፣ ጃውሳ ፤ ወዘተ እያሉ አስረውኛል አሳደውኛል። ለአራት አመታት ከባንክ አገልግሎት ከቀበሌ መታወቂያ ከማንኛውም ተቋም ሰነድ እንዳላገኝ ተደርጊያለሁ። ከእጅ ስልክ ጀምሮ ያለኝን የስራ ቁሲቁ በሙሉ ዘርፈውታል። የተገነቡ ስቱዲዮዎቾን በማሸግ ለአመታት እንድከፍል እንዲፈርሱና እንድንሰቃይ አድርገዋል። በእርግጥ በዝርዝር ለመግለፅ የምችለው በዚህ አይደለም በሌላ መንገድ እንጅ ! በእስር ቤት ታምሜ ለሞት ጫፍ ደርሼ ነበር። ሙሉ ገላዬ አልቆ 49 ኪሎ ግራም ሆኜ ነበር። ሊያሳክሙኝ ቀርቶ በመትረፌ ይፀፀቱ ነበር። ፋሽቶች ስለሆኑ የሚያስደስታቸው ሞታችን እንጅ መኖራችን አይደለም። ተርፊያለሁ ፤ አምልጫለሁ ፤ ከገዛ ሀገሬ መንግስት ግድያ አምልጫለሁ !! የኔ ስደት አይባልም ከሞት ማምለጥ ነው የሚባለው። እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን !!!
إظهار الكل...
👍 29🔥 3🙏 3
በሁሉም ግንባሮች ለምትዋደቁ ፋኖዎች እንኳን አደረሳችሁ ጀግኖቻችን !!! አዲሱ አመት የድል አመት እንደሚሆን አናምናለን !!! አለን!
إظهار الكل...
🔥 16🙏 8👍 1
ሰበር .. ከሁለት ቀናት በፊት በሱዳን ገዳሪፍ ግዛት አልፍኦ በተባለ አካባቢ ከጄኔራል መሃመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሂመቲ) ወታደሮች ጋር  ውጊያ የገጠሙት ቅጥረኛ (Mercenaries) የወያኔ ታጣቂዎች ከባድ ኪሳራን አስተናግደዋል። መረጃውን ያደረሱኝ  ምንጮቼ  በወያኔ በኩል የደረሰውን ይህንን ሽንፈት ሲገልፁልኝ  " እልቂት" ነበር ብለውታል !!! (የትግራይ ሰዎች ውሎ አድሮ መረጃውን ማግኘታቸው አይቀርም... በዚሁ መረጃ ዙሪያ ቮድካውና ፍስሃ ማንጁስ ሰሞኑን Busy ይሆናሉ - Mark my words!) @wlkayi
إظهار الكل...
👍 47 4
~ የድሉ መባቻ ወቅት እና የአገዛዙ ውጥረቶች ‼ ያሉትን እያደረጉ ነው፤ ገና ያልነገሩንን ያደርጋሉ። አገሪቱ ያላትን ብቻ ሳይሆን የሌላትን ሁሉ ወደ ጦር ሜዳ እንድታውል አገዛዙ ወስኗል። ► የአገሪቱ ካፒታል በጀት ወደ ጦርነት እየዞረ ስለመሆኑ በተለያዩ ተቋማት ያሉ ፕሮጀክቶችን መፈተሽ በቂ ነው። ► ክልሎች ይቅርና የካፒታል በጀት ሥራ የመደበኛ በጀት ደመወዝ መክፈል አቅቷቸዋል። ► ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪ ምግብ ማቅረብ ቸግሯቸው ተማሪዎቻቸውን በትነዋል። ► በየክልሉ ለመከላከያ ስንቅና ትጥቅ መዋጮ የሚጠየቁ ነጋዴዎችና ባለሀብቶች በምሬት ሤራ ንግዳቸውን መዝጋት ጀምረዋል። ► የአገራቱን ባለሀብቶች ገንዘብ አዋጡ ያለው ፋሽስቱ አብይ አሕመድ "የገንዘብ ችግር ላይ ወድቀናል" በማለታቸው  ተራ ችርቻሮ ንግድን ጨምሮ በርካታ የሥራ መስኮችን ለውጭ ባለሀብት ከፍቻለሁ ብሏል። የውጭው ባለሀብት እንኳንስ ችርቻሮ ሌላውንም ሥራ በዛሬዋ ኢትዮጵያ መሥራት አቁመው እየተሰደዱ ነው። ► የአበዳሪዎችን ገንዘብ ወደ ጦርነት ለማዋል በየፈረንጁ ቤት የሚደረገው ዙረት የረባ ነገር አላመጣም። ► የቤተመንግሥት ማስዋብና ግንባታ እንዲሁም የከተማ ማስዋብን "የተቀባይነት ጥሩ ማሳያ" ያደረገው አገዛዙ ያለውን ገንዘብ በአዲስ አበባ መንገዶች ላይ እያፈሰሰ ነው። ይሔን እያዩ ይቀበሉኛል የሚል እምነት ቢሆንም፥ አንድም ከክልል ወደከተማዋ የሚደረገውን ፍልሰት እንደሚጨምር ፥ ሁለትም  የመንገድ ማስዋብ የድሃ ሞሶብ እንደማይሞላ አገዛዙ አልተረዳም። ►  የዋጋ ግሽበት ለመከላከል ተብሎ የአገሪቱ ባንኮች ገንዘብ እንዳያበድሩ፣ የፕሮጀክቶች ክፍያ እንዲቆም በማድረግ ኢንፍሌሽንን ተቆጣጠርን ለማለት ብዙ ደክመዋል። ውጤቱ የልማት መቆም ብቻ ሳይሆን ማሽቆልቆል ነው። ☝️ እናም ስልጣኑን መጠበቅ አለበትና የተገኘው ሁሉ ወደጦር ሜዳ ተብሏል። ▪ የአማራ ኃይልን ተጠቅሞ ፋኖን የመዋጋት ጉዳይ እርሙን እያወጣ ነው። አማራን የሚጠላ አገዛዝ አማራን አሰልፎ አማራን አያሸንፍም!! ▪ የኦሮሞን ምስኪን አርሶ አደር እየሰበሰበ በማሰልጠን "ስልጣን ጠብቁ" የሚለው ልፍለፋ የት እንደሚደርስ የሚታይ ነው። ▪ መሬት የታደለው ኮሎኔልና መስመራዊ መኮንን መኮብለሉንና ፋኖን መቀላቀሉን ቀጥሏል። ኮማንዶ፣ ሪፐብሊካን ጋርድ፣ የባሕር ኃይል ... ወደ ውጊያ ያልተጣደ የለም። ▪ የቀረው የሱዳንን ግጭት ቆስቁሶ ከምዕራብ በኩል የሱዳንን ጦር ወደአማራ ማስገባት ነው። እሱንም ከሠሞኑ ወደ አል ቡርሐን መንደር አቅንቶ መሞከር ጀምሯል። ▪ አሁን በየክልሉ ያለው ነጋዴውና ባለሀብቱ የግድ ገንዘብ አዋጣ መባሉ ይቀጥላል። ▪ የአገሪቱ አንጡራ ሀብቶች በከፊልም ሆነ በሙሉ እየተሸጡ ወደውጊያ መዋላቸው አይቀርም ‼ ▪"ልጃችሁ አርጉኝ" የተባሉት ኤምሬቶች እግር ላይ ወድቆ ጥቂት ገንዘብ መለመኑም አይቀርም!! ☝️ውስጥ ውስጡን ለሶስተኛ ጊዜ የተራዘመው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ቀናትና ወራትን መቁጠሩን አላቆመም ። በአመት ትግል ንቅንቅ ያላለው ፋኖ ግን በአስደናቂ ድል ቀጥሏል። የአለምአቀፍ ተቋማት ውግዘትም ለአገዛዙ ሌላ የሽንፈት ምዕራፍ ነው። ነገር ግን ምንም ቢደረግ ሕዝብ ያሸንፋል‼ የመረረው ሕዝብ በአንድ ፋሽስት አንገት አይደፋም‼ የድል መባቻ ላይ ነን‼ ድል ለአማራ ሕዝብ‼ #AddisuDerebe
إظهار الكل...
👍 31 1🔥 1👏 1
እንዴት አደራቹህ? ወለጋ‼ ገዳዮቹ  ፈቃዳ አብዲሳ፣ጃል መሮ(ኩምሳ ዲሪባ)፣ ሽመልስ አብዲሳ፣አብይ ህመድ....... እያሉ step by step በዬ ግዜው ይቀያየራሉ ሟቹ ግን ያው አንድም ተወካይ የሌለው ወደ የትኛውም የአማራ ግዛቶች እንዳይሄድ መንገድ የተዘጋበት ጭቁኑ የአማራ ህዝብ ነው። @Bizamo
إظهار الكل...
👍 21🔥 3😡 2🙏 1
00:32
Video unavailableShow in Telegram
ጄነራል ተፈራ ማሞ እና ጓዶቹ ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረሳችሁ 🫡
إظهار الكل...
5.97 MB
👍 13 4👏 1
እንዴት አደራቹህ? ወለጋ‼ ገዳዮቹ  ፈቃዳ አብዲሳ፣ጃል መሮ(ኩምሳ ዲሪባ)፣ ሽመልስ አብዲሳ፣አብይ ህመድ....... እያሉ step by step በዬ ግዜው ይቀያየራሉ ሟቹ ግን ያው አንድም ተወካይ የሌለው ወደ የትኛውም የአማራ ግዛቶች እንዳይሄድ ምንገድ የተዘጋበት ጭቁኑ የአማራ ህዝብ ነው። @Bizamo
إظهار الكل...
የአገዛዙ የፀጥታ አመራሮች ስብሰባን የተመለከተ ጄኔራል ተፈራ ማሞ ፋኖን መቀላቀሉን ተከትሎ የአገዛዙ የክልል ጸጥታ አመራሮች ስብሰባ የተቀመጡ ቢሆንም ስብሰባው እንደታሰበው እንዳልሄደ ባህርዳር ዊክሊክስ ከምንጮቿ ያገኘችው መረጃ ያስረዳል። በስብሰባዎቹ ከተነሱት አንኳር ነጥቦች መካከል የሚከተሉትን እንጥቀስ፦ 1. በስብሰባው "የፋኖ ትግል አመራሮችን ዒላማ አድርገን ስለተንቀሳቀስን ብቻ ትግሉ ሊቆም የሚችል አይደለም፤ ይልቅ የተሻለ መፍትሔ ማምጣት ያስፈልጋል" የሚል ሃሳብ ተነስቷል። 2. ሌላው በስብሰባው ከተነሱት ውስጥ ወሳኙ ነጥብ… አገዛዙ አሁን አድማ ብተናን ሊያምን የማይችልበት ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑ "ትጥቅ ከማስፈታት ይልቅ የተተኳሽ እጥረት አለ በማለት የሚይዙትን ተተኳሽ መገደብ ያስፍልጋል፤ ትጥቅ ማስፍታቱ ሌላ ቀውስ በእራስ ላይ መጋበዝ ነው" የሚል ሃሳቦችም በመድረኩ ተንሸራሽሯል። 3. "የስብሰባው ውጤት ያላማራቸው አመራሮች ሚሊሻው በስውር እንዲደራጅ እና ከአድማ ብተናው እኩል እንዲታጠቅ በማድረግ በሁለቱ ኃይሎች መካከል መተማመን እንዳይኖር ይደረግ" የሚል ውሳኔ መወሰኑንም የምንጫችን መረጃ ያስረዳል። 4. ሌላውና አስቂኙ ነገር ደግሞ የአበል መቀነስ ላይ ያለው የእርስበርስ እሰጣገባ ነበር፤ ህዝብ ለሚጨፈጭፉበትና ለኦሮሞ ብልጽግና የፈረስነት ሚናቸው አበል እንዳይቀነስ ከባድ ሙግት እንደነበርም ተሰምቷል። ከዚህ ጋር ባልተያያዘ ዜና ደግሞ ነገ በአዲስ አበባ በሰላም ሚኒስቴር አስተባባሪነት "ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም" የሚል የሩጫ ውድድር መዘጋጀቱን ሰምተናል። "ለስልጣን መጠበቂያነት ከመጠቀም ይልቅ የፀጥታ ተቋማቶቻችሁን በማዘዝ ህግ አስከብሩ፣ ሰላም አስፍኑ… የሴራ ፖለቲካችሁን ተው" ብለን ከ2010 እስከ 2015 ለምነናል… አሁን በሩጫ ልታመልጡ ትችሉ ካልሆነ በቀል፣ የሚመጣ ሰላም ወይም የሚፀና ስልጣን የለም። ለሞተ ስርዓት ይህ ሁሉ መንከላወስ 😃
إظهار الكل...
👍 25 3
ደፈጣ - ጎንደር በዛሬው ዕለት በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከወገራ ወደ ችንፋዝ በመጓዝ ላይ የነበረ የአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት በክንደ ነበልባሎቹ ለወሬ ነጋሪ እንኳን ሳይተርፍ በደፈጣ ጥቃት መዳጡ ታውቋል። ለእገዛ የተንቀሳቀሰ ተጨማሪ የአገዛዙ ኃይልም ከምድር በታች መሆኑ ተነግሯል። ሁለቱ ጥቃቶች በርካታ አራዊት ሰራዊት ቀንሰዋል። ከሰሞኑን በተለይ በደቡባዊ ጎንደር በርካታ ውጤታማ ኦፕሬሽኖች መፈፀማቸውም ታውቋል።
إظهار الكل...
👍 6
"3 ክላሽ የያዙ ፋኖዎች" የመፈንቅለ መንግሥት ስጋት ፈጥረውብህ ካስቃዡህና ሱሪህን ካራሱት፣ በምን መልኩ ልናግዝ እንችላለን? የዚህ ጨቅላ ከብት ችግር ግን ከአማኑኤል ሆስፒታልም በላይ ነው።
إظهار الكل...
👍 12
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.