cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ቱሪዝም ሚኒስቴር - Ministry of Tourism

Official Corporate Telegram of Ministry of Tourism , Ethiopia ~ For realization of Tourism’s Full Potential for Ethiopia’s Economic Growth

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 733
المشتركون
+224 ساعات
+197 أيام
+5030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የኢጋድ አባል ሀገራት በቱሪዝም ዘርፍ ያላቸውን ትስስር ያጠናክራሉ ተብለው የሚጠበቁ ኹነቶች በአዲስ አበባ ሊካሄዱ ነው፡፡ መስከረም 6 ቀን 2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ከመስከረም 7-9 በአዲስ አበባ የሚካሄደውን መርሃ-ግብር በማስመልት የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ስለሺ ግርማ ለመብዙሃን መገናኛዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ክቡር ሚንስትር ዴኤታው በመግለጫቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር የኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻዎች እና ሃብቶች ከመጠበቅ፣ ከማልማትና ማስተዋወቅ ባሻገር ቱሪዝም ለሃገራችን ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ በቅጡ ተገንዝቦ ለመተንተን እና በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ቀረጻ እና ስልታዊ የእቅድ ዝግጅትን እውን ለማድረግ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ለሃገራችን የመጀመሪያ የሆነውን የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት (TSA) መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ ይህም ኢትዮጵያን የቱሪዝም ሳተላይት አካውንትን አጠናቀው ተግባራዊ ካደረጉ ጥቂት የአፍሪካ ሃገራት ተርታ እንደሚያሰልፋት የገለፁት ክቡር ሚንስትር ዴአታው መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም. በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በሚካሄድ መርሃ ግብር ይፋ እንደሚደረግም ገልጸዋል፡፡ በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ በሚካሄደው መርሃ ግብር ላይ ይፋ የሚደረገው ሌላው ወሰኝ ኹነት ኢጋድ እና አባል ሃገራቱ በቅንጅት ያዘጋጁት የኢጋድ አባል ሀገራት ዘላቂ የቱሪዝም ማስተር ፕላን እንደሆነ የገለፁት ክቡር አቶ ስለሺ ማስተር ፕላኑ በቀጠናው ዘላቂ የቱሪዝም ልማትን እውን ያርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡ መርሃ-ግብሩ መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም የቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የኢጋድ ሴክሬታሪያት እና ዩኤን ኢሲኤ በተገኙበት እንደሚካሄድ በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡
إظهار الكل...
7👍 3
05:22
Video unavailableShow in Telegram
IMG_8175.MP428.07 MB
👍 3 2
Photo unavailableShow in Telegram
👍 5
የአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። ነሀሴ 15/2016 ዓ.ም ቱሪዝም ሚኒስትር ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስትሩና ለተጠሪ ተቋማቱ አመራሮች በፌዴራል አስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 ላይ የግማሽ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በሚኒስቴሩ አዳራሽ ተሰጠ።
إظهار الكل...
01:29
Video unavailableShow in Telegram
IMG_3143.MP416.18 MB
Photo unavailableShow in Telegram
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
👍 6
እንኳን ደስአለን! የመልካ ቁንጡሬ ባልጪት የአረኪዮሎጂ እና ፓሊዮንቶሎጂ ሥፍራ በዓለም ቅርስነት በዩኔስኮ ተመዘገበ፡፡ በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ በሚገኘው 46ኛው የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ማዕከል ዓመታዊ ጉባዔ የመልካ ቁንጡሬ ባልጪት የአረኪዮሎጂ እና ፓሊዮንቶሎጂ ሥፍራ ሶስት መስፈርቶችን በማሟላት የዓለም ቅርስ ሆነ ተመዝግቧል ሥፍራውን በዓለም ቅርስነት ያበቁት መስፈርቶች መስፈርት 3 (criterion III) ከ2.5 ሚሊየን ዓመት እስከ መጨረሻው የድንጋይ ዘመን የሰው ልጅ ይጠቀምባቸው የነበሩ የድንጋይ መገልገያዎች ይዞ የሚገኝ በመሆኑ፡፡ መስፈርት 4 (criterion Iv) እስከ 2.5 ሚሊየን ዓመት እድሜ ያላቸው የተለያዩ የሰውና የእንስሳት ቅሪተ አካሎች በብዛት የሚገኙበት በመሆኑ:: መስፈርት 5 (criterion v) የሰው ልጅ ከድንጋይ የተለያዩ መገልገያዎችን/መሳሪያዎችን ይሰራ እንደ ነበር የሚያሳዩ ስምንት የባልጩትና ሌሎች የድንጋይ መሳሪያ ማምረቻ ሥፍራዎችን ይዞ የሚገኝ በመሆኑ ነው፡፡ የቱሪዝም ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለጉባኤው በላኩት መልእክት ይህ ቅርስ የተመዘገበው ሉሲ የተገኘችበትን 50ኛ አመት በምናከብርበት ወቅት መሆኑ ለሀገራችን ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልፀዋል:: በእርግጥም ሀገራችን ምድረቀደምት መሆኗን ለአለም ተጨማሪ ማረጋገጫ የሰጠ መሆኑንም አንስተዋል:: ይህ ቅርፅ ተጠብቆ እንዲቆይም የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል:: መልካ ቁንጡሬ ባልጪት ከአዲስ አበባ ወደ ቡታጂራ በሚወስደው ጎዳና 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አዋሽ ወንዝ ዳርቻ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሀገራችን ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው ቋሚ የሚዳሰሱ ቅርሶች 12ኛው ነው፡፡
إظهار الكل...
👍 15👏 3 2
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከሀገር አቀፍ ጥናትና ማማከር ኢንስቲትዪት National Research and Consultancy Institute/ ጋር በመቀናጀት እንዲሁም በFirst Consult/Master Card Foundation አጋርነት በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኙ ባለ ኮከብ ሆቴሎች ውስጥ ለሚሰሩ በምግብ ዝግጅትና መስተንግዶ እንዲሁም በቤት አያያዝና የላውንደሪ አገልግሎት ዘርፍ የተሰማሩ  ለ362 ሴት የሆቴል ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል።
إظهار الكل...
👍 3👏 1
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.