cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Arqem[አርቀም]

ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ በዚያች ይበልጥ መልካም በሆነችውም (መንገድ እና ስልት) ተወያያቸው። (አል ነህል 125) ለአስተያየቶ @MezidaTemam

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
450
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ቀን 3 ሳላወራሽ .... (ፉአድ ሙና) . አንቺን የማያውቁ ጊዜው ተለወጠ፣ አሉኝ ዳግም ነጋ፣ ምንም ብርሀን የለ እንደጨለመ ነው፣ እስካሁን እኔ ጋ! አንቺ ነሽ ብርሀኔ ... አንቺ ነሽ ብርሀኔ በፊትሽ ፀዳል ነው፣ ወቅቴን የምቆጥረው፣ አይኔን ስትሞዪ ስትስቂ ስትስቂ፣ ይኸው ነጋ ‘ምለው። ልቤን ይወጋኛል .... ልቤን ይቀስፈኛል ደምኗል አየሩ፣ ጠቋቁሯል ሰማዩ፣ ውስጤ አይረጋጋም ከርታታ አይኖቼ፣ ፊትሽን ካላዩ። አመመኝ በጠና .... ከንፈርሽ ያውና ዚክር¹ አለስልሶት፣ ተቀብቶ ሙራጃ²፣ አንድዜ ብገምጠው እስከዘላለሙ፣ መራቤንም እንጃ። ቅሪልኝ³ ህመሜ ልስማሽ ስትሞጥዪ⁴፣ እንዳይጠፋሽ ሂፍዙ⁵፣ ብጮህም አልፈራም ሀጢዓት አይባልም፣ ሰው ባንቺ መያዙ!! ቅሪልኝ ግድየለም!! ተራብኩሽ አለሜ .... ተራብኩሽ በፀና፣ ጆሮዬ አኮረፈኝ፣ አለኝ ድምጿን አምጣ፣ አንደበቴ ከዳኝ፣ በወሬዬ መሀል፣ ስምሽን እያወጣ!! አወይ የኔ ጣጣ!! ናፍቀሽኛል እኮ .... ናፍቀሽኛል በጣም የሀፍረትሽ አስኳል፣ ተስሏል ከፊቴ፣ ያ ረብ እያልኩኝ ነው ታፋሽ ላይ እንድሞት፣ ቤትሽ ሆኖ ቤቴ። ተዪ ግን ራሪ .... ሲሰቃይ ለኖረ ፣ ልቡን ‘ሚሞላ አጥቶ፣ ትናንት ለሌለው፣ የኔ አይነት ማቶ፣ ራሪ አለሜ፣ ጀግና አትባዪም፣ በፍቅርሽ ሰው ሞቶ። ግን አንቺስ እንዴት ነሽ? ናፍቄሻለሁኝ? ትዝ ብዬሻለሁ፣ ትንሽ እንኳን ለአፍታ? ወይስ ብቅ አላልኩም፣ በአዕምሮሽ መሀል፣ ከቶም ለብልጭታ? ቲሽ! ምኔ ይናፈቃል? እኔ አንቺን አይደለሁ!! ናፍቆት ሲያም!! አመመኝ መናፈቅ የወትሮው ታታሪ፣ አቃተኝ መነሳት፣ አንቺን ብቻ ሳስብ፣ የዝሁርን አዛን⁶፣ ደረስኩ እስከመርሳት። አልፎኛል ጀመዓ⁷ ጣትሽን አውሺኝ፣ ስቲግፋር⁸ ላ‘ርግበት፣ ባንቺ ያረፈደ፣ ባንቺ ጣት ብቻ ነው፣ መቅቡል⁹ ‘ሚሆንለት። አስነኪኝ ግድየለም!! ጨረቃዬ .... ናፍቀሽኛል ናፍቆት ራሱ፣ እስኪያየኝ ሀዘን ለብሶ፣ እስኪል ድረስ፣ አላየሁም ያንተን ህመም፣ ሌላው ቀምሶ። ናፍቀሽኛል ውዴ!!! 20 ቀን እኮ ብዙ ነው!! ያ ረብ ኢኒ ፈቂር!!! *** አገባባዊ ፍቺ ¹ ዚክር: – አምላክን ማወደስ ² ሙራጃ: – ቁርዓንን በቃል ሽምድዶ መለማመድ ³ ቅሪልኝ: – ቁርዓን አንብቢልኝ ⁴ ስትሞጥዪ: — ቁርዓን በቃል ስትለማመጂ ⁵ ሂፍዙ: – የተሸመደደው ቁርዓን ⁶ የዝሁር አዛን : – በቀን አካፋይ ላይ የሚሰገደው ሰላት ጥሪ ⁷ ጀመዓ: – ለስግደት መሰብሰብ ⁸ ስቲግፋር: – ምህረትን መለመን ⁹ መቅቡል: – ተቀባይነት የሚያገኘው . ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
ቀን 2 ሳላወራሽ ... (ፉአድ ሙና) . ሲያፈቅሩ ስቄያለሁ፣ ባለማወቅ ወኔ፣ ይኸው ፍቅርሽ ቀጣኝ፣ አወይ መጥኔ ለኔ፣ ምናለ ባልሳቅኩኝ? ኧረ እንኳንም ሳቅኩኝ!!! ናፍቆትሽ ጀመረኝ ... ትዝ አሉኝ ጣቶችሽ ውብ ከንፈሮችሽን ‘ምትሸፍኝባቸው፣ እንደው ስለፍቅሬ ሀራም¹ ይሆናል ወይ አንዴ ብነካቸው? ትዝ አሉኝ ጉንጮችሽ ልክ እንደ መንደሪን፣ ግመጡኝ የሚሉ፣ ሳስቅሽ ሳስቅሽ ስትሽኮረመሚ፣ በደም የሚሞሉ፣ ትዝ አሉኝ ጉንጮችሽ ምናል ብገምጣቸው፣ ምናል ብነክሳቸው? ሀራም ይሆናል ወይ? በቡርቱካን ኒያ²፣ ለሚዳብሳቸው? ናፈቅሽኝ አለሜ ተመኘሁ ባቀፍኩሽ፣ ትንፋሽሽ ቢገርፈኝ፣ በተኛሽ በእቅፌ፣ እንጃልኝ እንጃልኝ፣ ያንተ ነኝ ካላልሽኝ አልተኛም አርፌ። ትዝ አሉኝ አይኖችሽ መሬት መሬቱ ላይ የሚንከራተቱት፣ በምን ከራማ³ ነው፣ አይኔን ገረፍ አ‘ርገው፣ ልቤን የሚያዩት?? ምንድነሽ አንቺዬ? ጌታዬ በሰማይ ለደጋግ ባሮቹ፣ አልቆ ያበጀው፣ እንዳትዋሺኝ ውዴ ሁረል ዐይን⁴ ምንድነው? ምድር ተልከሽ ነው? አንቺን በዱንያ ጀባ የተባለ እድለኛ ገዳም፣ ሁረል ዐይን ቢሉት ቅንጣት ታክል ጉጉት ከልቡ አይገባም። ምን ጉድነሽ በአላህ? ናፍቀሽኛል በጣም ከካፌው ተቀምጠን የቆራረጥሽው ሶፍት ፣ አስቀናኝ በብዙ፣ እንዴት ቢታደል ነው፣ ባንቺ መነካቱ፣ በእጆችሽ መያዙ? አጅነቢ⁵ ቢሆንስ??? ትዝ አለኝ ስትስቂ ሲበራ አለሙ፣ ስትሆኚ ጨረቃ፣ ትፈካለች  ምድር፣ በውበትሽ ደምቃ፣ ራሷ ምድር እንኳን፣ ለራሷ አትበቃ። እየናፈቅሽኝ ነው ርቦኛል ድምፅሽ፣ የጆሮዬ ሩቃ⁶፣ አንቺን ሳደምጥ ነው ከግራጫ አለሜ በርግጌ ‘ምነቃ። ናፍቀሽኛል ውዴ! ሀያ ቀን እኮ ብዙ ነው!! ያረብ ኢኒ ፈቂር!! *** አገባባዊ ፍቺ ¹ ሀራም: – በእስልምና አስተምህሮ የተከለከለ ² ኒያ: – ድርጊተ–አላማ፣ ሀሳብ ³ ከራማ – ከፈጣሪ የተሰጠ ልዩ ፈቃድ ⁴ ሁረል ዐይን – ለጀነት ሰዎች የተዘጋጁ ውብ እንስቶች ⁵ አጅነቢ – ለማግባት የማይከለከል፣ ባዳ ⁶ ሩቃ – መንፈሳዊ ህክምና ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
የትኛው ይበልጥ ይደንቃቹሃል 🤔 ? 1⃣ የረሱልን ደም ድፋ ተብሎ ደሙን ጭልጥ አርጎ የጠጣውን ሶሀባ ፍቅር? 🥺 2⃣ ወይስ ሀቢቡና ለቀናት ሲለዩት ያማረ ገፅታው እና ሰውነቱ ከስቶ የጠበቃቸው ሶሀባ ፍቅር? 😍 3⃣ ነው ወይስ ሀቢቢ ከሞቱ በኋላ በህልማቸው አይቷቸው ከመጣ በኋላ አዛን ማውጣት ያቃተው ናፍቆት? 🥰 4⃣ አሊያም ደሞ እንደሞቱ ሲያረዱት ህልፈታቸውን በጉልበት ላለማመን ሰይፍ እመዛለሁ ያሉት ጥልቅ ፍቅር? 😭 5⃣ በጦር አውድማ ከቤተሰቧ ህልፈት ባሻገር የነቢ መኖር ያስደሰታትስ ቢሆን ታሪኳ የወርቅ ብእር እንጂ ሌላ አያሻውም መለክ እንጂ ሰው አይፅፈውም የተባለላት? ❤️ . ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
#ፈጅርን አለመስገድ ያለው አደጋ! እና ከዚህ አደጋ ለመዳን መጠቀም ያለባቹ መፍትሄዎች! 1) የፈጅርን ሶላት ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ ከፈጅር ሶላት መሳነፍ አደገኛ የሆነ የሙናፊቆች ምልክት ነውና!! [ቡኻሪና ሙስሊም] 2) የፈጅርን ሶላት ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ የሸይጣን መፀዳጃ አትሁን፡፡ በአንድ ወቅት ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዘንድ እስከሚነጋ ድረስ ሌሊቱን ስለሚተኛ ሰው ተወራ፡፡ ይህኔ እሳቸው እንዲህ አሉ፡- “ያ በጆሮዎቹ ውስጥ ሸይጣን ሽንቱን የሸናበት ሰው ነው!” አሉ፡፡ አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል፡፡ [ሶሒሑትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 644] 3) የፈጅርን ሶላት ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ ያለበለዚያ የሸይጣን ወጥመድ ሲሳይ ትሆናለህ፡፡ ቀንህን ሙሉ ድብርት ይጫጫንሃል፣ ንቃት ይቀልሃል፡፡ ፈጅር ላይ ተነስቶ ውዱእ አድርጎ ያልሰገደ ሰው ቆሻሻ ነፍስ ይዞ እንደሚያነጋና ስንፍና እንደሚጫጫነው ተናግረዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም] 4) ፈጅርን ስገድ ያለበለዚያ በቀብርህ ውስጥ እስከ እለተ ቂያማ የሚዘልቅ ዘግናኝ ስቃይ ትሰቃያላህ፡፡ ከነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደተላለፈው አንድ ሰው ተንጋሎ ሌላው ካጠገቡ ቋጥኝ ይዞ በመቆም እራሱን ይደቁሰዋል፡፡ ድንጋዩ ተንከባሎ ሲሄድም እሱን አምጥቶ እስከሚመለስ ድረስ እራሱ እንደነበር ይመለሳል፡፡ ከዚያም እንደ መጀመሪያው ይሰራበታል፡፡ ቂያማ እስከሚቆም ድረስም በዚሁ መልኩ ይቀጥላል፡፡ ይህን በዚህ መልኩ የሚሰቃየውን ሰውየ ምንነት ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጂብሪል ሲጠይቁት “ይሄ ቁርኣንን ይዞ ፊት የሚነሳው ከግዴታ ሶላትም የሚተኛ ነው” አላቸው፡፡ ወንድም እህቶች ሆይ! ከፈጅር ሶላት አትዘናጉ፡፡ ወቅቱን ጠብቃቹ እንድትሰግድ የሚያግዛቹሁን ብልሃትም ተጠቀሙ! 1) በጊዜ ተኛ! የምሽት ወሬ ይቅር፡፡ ነብዩ(ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከዒሻ በፊት እንቅልፍ፣ (ከዒሻ) ቡኋላ ደግሞ ወሬ ይጠሉ ነበር፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም] 2) ቀኑን በወንጀል ከማሳለፍ ተጠንቀቅ፡፡ ወንጀል ከኸይር ስራ ያቅባል፡፡ በሌላ በኩል ለኸይር ስራ ትጋ፡፡ ኢስላማዊ የመኝታ ስርኣቱን ጠብቅ፡፡ የኸይር ስራ አንድ ሽልማቱ ለሌላ ኸይር ስራ መታደል ነውና፡፡ 3) ማታ ከመተኛትህ በፊት ለፈጅር ለመነሳት ቁርጠኛ ውሳኔ አድርግ፡፡ ረጅም ጉዞ ወይም አሳሳቢ ጉዳይ ቢኖርብህ ያለ ማንም አጋዥ ምናልባትም ያለአላርም እየነቃህ ለሶላት ሲሆን መዘናጋትህ ስለእውነት ከባድ የሞራል ልሽቀት ነው፡ችዋ 4) ማንቂያ ደወል (አላርም) ተጠቀም፡፡ ምናልባት ሳይታወቅህ አጥፍቶ የመተኛት አጉል ባህሪ ካለብህ ትንሽ ራቅ አድርገህ አስቀምጠው፡፡ 5) በሰአቱ ነቅተህ ከተጫጫነህ “ትንሽ ተኛ” ለሚሉ ሸይጣን እና ነፍስያ ሸንጋይ ጉትጎታ እድል አትስጥ፡፡ መነሳትህ ያለውን ዋጋ፣ መተኛትህ ያለውን አደጋ ላፍታ አስብ፡፡ ብትነሳ 50 ዶላር ይሰጣል ቢባል የሚኖርህን ንቃት ቃኝና እራስህን ታዘብ፡፡ ፈርዱ ቀርቶ ትርፍ የሆነችዋ የፈጅር 2 ረከዐ እንኳን ከዱንያ ፀጋ ሁሉ በላጭ እንደሆነች እራስህን አስታውስ! 6) በመልካም የሚያግዝ ጓደኛ ወይም የህይወት አጋር ካለህም እሰየው! አልሀምዱሊላ ነው ይህን መልእክት ለእህት ወንድሞች በማስተላለፍ ከዚህ አደጋ ይታደጎቸው! እደተለመደው አሁኑም በከይር ስራ እንሽቀዳደም ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
#_አንተም_አዲስ_ነህ አዲስ ነገር ቦታውን ይይዝ ዘንድ አሮጌውና የቀድሞው ነገር ቦታ መልቀቅ ይኖርበታል። አሮጌው ጊዜ ስፍራውን ሲለቅ በአዲስ ይተካል የቀድሞው ማንነትም ሲሻርና ሲተው ብቻ የተሻለው ማንነት ይከሰታል። ያልታሰበ ስኬትና ከፍታ ኬትም ሊመጣ አይችልም። ከዚህ ቀደም ብዙ ሃሳቦች በውስጥህ ተመላልሰው ይሆናል፣ መሆን የምትፈልገውን ሰው እንዳትሆን ፍረሃት አስሮህ ስጋትም ጋርዶህ ይሆናል፣ ላይ ታች በማለትም ብዙ ለፍተህ ይሆናል። አዲስና ልዩ ባልከው ጊዜም ሃሳብህን፣ ምኞትህን፣ ህልምህን መኖር ትጀምራለህ። በትልቁ ለማሰብ፣ የተሻለውን ለመምረጥ፣ የተሻለ ቦታም ለመገኘት ግዴታ የተፈጥሮን የጊዜ ኡደትና ለውጥ መጠበቅ አይኖርብንም። ስላለን የጊዜን ሽግግር፣ የአመታትን ልውውጥ እናያለን። ከእይታችን ባሻገር ግን የለውጡ ተሳታፊ፣ የሽግግሩም ተካፋይ መሆን ይኖርብናል። ከንግርቱና ከትረካው በላይ በአዲስ ዘመን ተነሳሽነት ሙሉውን አመት በደስታና በፍቅር ማሳለፍ፣ ነገ በሚያረጀው የዛሬ አዲስ አመት የማያረጅ ዘላቂ የህይወት መሰረት ማስቀመጥ፣ የህይወት ስንቅም መሰነቅ የተሻለው አስደሳች ምርጫ ነው። አንተም አዲስ ነህ በዘመን ከፍታ ከፍ የምትል፣ በአዲስ ተፈጥሮአዊ መስተጋብር የምትደምቅ፣ የለውጥ ወዳጅ፣ እድገትን ፈላጊ ልዩነትን የምትፈጥር ብርቱ ሰው ነህ። ሃሳብህ አዲስ ነው፤ ምልከታህ፣ እይታህ አዲስ ነው። በጊዜያት መታደስ ውስጥ እራስህን አድስ፤ በዘመን ልውውጥ እራስህን ለውጥ፣ በዘመን ሽግግር ችግሮችህን፣ ፈተናዎችህን ጥለህ ተሻገር። ዘመን ብቻውን አይታደስምና በታደሰና በተሻለ ስብዕና ተቀበለው። ደስታን ተሞላበት፣ ሃሴትን አድርግበት፣ በፍካት በድምቀት ጎልተህ ታይበት። መልካምነትን ከስኬት፣ ከፍታን ከደስታ የሚያስተሳስር የድንቅ አድራጊነታችን ማሳያ የሚሆን ፣ የተረጋጋና ሰላማዊ አዲስ አመት ይሁንልን ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
ምኞት ... (ፉአድ ሙና) . ለይሉ ጁሙዓ ነው .... አንቺ አለሽ ከጎኔ፣ በአንድ እየመጠጥን የሰለዋት መቅኔ። ከከንፈርሽ ሲዘንብ የአዝካር ማር ፈሰስ፣ በሲራ ሳብሰው የናፍቆትሽ ሲደርስ፣ በለይል ሰላት ወግ ሲባረክ ድግሱ፣ በዱዓ ሲለመጥ ዱንያ ትርምስምሱ፣ ይታየኛል ቤቴ በዲን ኑር ሲያበራ፣ ኢማን ሞልቶ ሲፈስ ቁርዓኑ ሲቀራ። እንዳትቀሰቅሱኝ .... እንዳትቀሰቀሱኝ ..... እንዳትቀሰቅሱኝ ቲሽ ቀሰቀሱኝ!! ባዶ ቤት ባዶ አልጋ፣ ኢማን ያልሞላበት፣ በሀላል ያልረጋ። ብትመጪ ምናለ? ያረብ ኢኒ ፈቂር!! . ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
በ መብሩክ @ArkemMy
إظهار الكل...
የናፍቆት ደብዳቤ .m4a3.28 MB
ለዉብ ምሽታችን 💚💚💚 በተሳሳተ መንገድ ለረዥም ጊዜ ፣ ብዙ ርቀት ብትጓዝም በማንኛውም ጊዜ ፣ በየትኛውም ቦታ ትክክለኛ ነው ወደምትለው መንገድ መግባት ትችላለህ በል ዛሬውኑ የልብህን እውነት ፣ ህልምህን ተከተል…………………… ------------------------------------------------ ሀገር የልጅ ብድር እንጂ ያባቶች ስጦታ አይደለም። ንባብን አፍቅር፤ ራስህን በንባብ ቅበር… . የመፅሃፍ ቁጥር እየጠራህ አትፎካከር… ያነበብከውን ማብላላትህን ገምግም፡፡ የምታነበውን ሞግት፤ እንዲሁ አትቀበል፤ ወይም አንብበህ ለመጨረስ አትሩጥ፡፡ ጥሩ መነሻ እንዲሆነን!! ምሁር ወይም አንባቢ የሚባሉ ግለሰቦች በወር ምን ያህል የሚያነቡ ይመስልሃል? አስር ሀያ ልትል ትችላለህ፤ እውነቱ ግን በወር ሁለት መጽሃፍት ቢያነቡ ነው፡፡ ባጭሩ በቀን 20 ገፅ ማለት ነው፡፡ ያ ደግሞ ምናልባት ከአንድ ሰዓት ንባብ አይበልጥም፡፡ ስለዚህ ማስተዋልን የተመረኮዘ የንባብ ባህል አዳብር፤ አንዳንዱ በዘጋቢ ፊልም፤ በፊቸር ሲኒማ፣ በኦዲዮ ቪዢዋል ወይም የሚዲያ መረጃዎች ላይ ራሱን ያጥራል፤ ይህ ግን ጥቂት እንጂ ብዙ ፋይዳ አይኖረውም፡፡ በንባብና ኦዲዮ ቪዚዋል መሀል ሰፊ ልዩነት አለ፤ ንባብ ውስጥ አእምሮህ የሚቀርበውን መረጃ እያሰላሰለ ምናቡን እንዲያሳድግ ይጥራል፤ በምታየው ምስል ግን በሰከንዶች አይተህ ስለምታልፈው ለምናብ አቅም ጥቅም አታገኝበትም፡፡ በአንድ የቪዲዮ መረጃ አንድን ተራራ በአንድ ሰከንድ አሳይቶህ ያልፋል፤ በመፅሃፍ ቢሆን ግን ስዕሉን ወደ አእምሮህ ለማምጣት ታስባለህ… እናም የምናብ ስፋትህ ይዳብራል፡፡ በምንም መልኩ ማናችንም ከመፅሃፍ ንባብ ጋር የጠበቀ ቁርኝትን ልናስቀድም የተገባ ነው፤ ከሚዲያ እውቀት በላቀ ጥልቀት ራስን መጠየቅና ማስገኘት የሚያስችሉ እውቀቶች የምንዝቀው የተመረጡ ጥራዞች ውስጥ ነው፡፡ ምርጥ መጽሃፍትን እንዴት እንምረጥ? የሚለውንና እንዴት የንባብ አቅማችንን እናሳድግ ስለሚለው ቀስ በቀስ የምለው ይኖራል፤ ((( ቡርሃን አዲስ ))) ------------------------------------------------ ሸጊቲ ምሽት!!!
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
የየነ
إظهار الكل...
✅ ለኸይር ሰበብ እንሁን!! 📣📣📣📣📣📣📣📣 💎እንደሚታወቀው ከነገ ወዲያ የአሹራ ቀን ነው። ይህን ቀን መፃም የአንድ አመት ወንጀል ያስምራል። በተለይ ደሞ የነገውን ዘጠነኛው ቀን ከተጨመረበት ምንዳው የተነባበረ ይሆናል። ✅ ነገር ግን የነዚህ ቀን ትልቅ ትሩፋት የማያውቁ፣ የተዘናጉና የረሱ ሰዎች ስለሚኖሩ እናት አባቶቻችን፣ ወንድም እህቶቻችን፣ ጓደኞቻችን፣ የቅርብ ዘመዶቻችንም ሆነ ማንኛውም ለምናውቀው ሙስሊም ሁሉ በማስታወስ የኸይር ሰበብ እንሁን።‼️ 【አመላካች የሰሪውን አጅር ያገኛል ♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ @ArkemMy @ArkemMy
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.