cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

አል –ፈቂር ኢለሏህ ( ሷድቅ አወል) አልወራቢይ

أقــول الحــق ولو كـان مـــرا

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 335
المشتركون
-124 ساعات
-177 أيام
-5530 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

🔍የአለማቱ እዝነት ሙሐመድﷺ ያለቀሱባቸው አጋጣሚዎች...!!አጎታቸው ሐምዛ ሲገደል..!! ➋የአጎታቸው ልጅ ጀዕፈር ሲገደል፤ ከርሱም ጋር አብዱሏህ ቢን ረዋሓና ዘይድ ነበሩ...!! ➌ልጃቸው ኢብራሒም ሲሞት...!! ➍የልጃቸው(የዘይነብ) ልጅ ኡማማ ስትሞት..!! ➎የእናታቸው ቀብር የጎበኙ ግዜ...!! ➏ኢብኑ መስዑድ ሱረቱ ኒሳዕ ባነበባቸው ግዜ 41ኛው አንቀፅ ሲደርስ..!! ➐ከሱረቱል አንፋል 68ኛው አንቀጽ ሲወርድ..!!ሰዕድ ቢን ዑባዳን አሞት ለመጠየቅ በሔዱበት..!!ሷላት ሲሰግዱይህ ብዙ ግዜ ይከሰት የነበረ ሲሆን ደረታቸውም ላይ ከለቅሶው የተነሳ ድስጥ የሚፍለቀለቅ ይመስል ነበር..!!ለዑመታቸው በማዘንና በማሰብ፡ በዚህ የተሳ ጌታቸው "እኛ በዑመቶች እናስወድድሃለን! አናስከፋህም" ብሎዋቸዋል!! ➊➊ ዑስማን ቢን መዝዑን የሞተ ግዜ..!! 🖊IBNU SHAYKH @Abdul_halim_ibnu_shayk @Abdul_halim_ibnu_shayk
إظهار الكل...
👉. በኢልያስ ፈረስ የመመይዖችን መንሀጅ - በደንብ ቃኝቶ፤ የደዕዋቸውን አከሄድ - በማስረጃ አጥርቶ፤ የአቋማቸውን መውረድ - አስተውሎ አይቶ፤ የመርከዙን ሰዎች - በይፋ አውስቶ፤ ኢልያስ አህመድን - በስሙ አንስቶ፤ በሚያስገርም ወኔ - በግልፅ አውርቶ፤ ትናንት ወቅሶ ነበር - አውግዞ ተችቶ፤ ዛሬ ማውገዝ ትቷል - የሀቁን መንገድ ስቶ፤ የተምዪዕን መርፌ - (ኦቨር ዶዝ) ተወግቶ፤ ሰላሰዋን ኪኒን - በጥብጦ ጠጥቶ፤ በተመዩዕ ቫይረስ - እጅጉን ተጎድቶ፤ እልም ያለ እንቅልፍ - ለጥ ብሎ ተኝቶ፤ የትናንቱ (ገይራ) - ወኔው ሁሉ ሞቶ፤ ለመጅሊሱ ሰዎች - ትከሻውን አስፍቶ፤ ትናንት የተቻቸውን - ሙመይዖችን ትቶ፤ ሰለፊዮችን ወግቷል - ምላሱን አውጥቶ፤ የረድ ጉረኞች ብሏል - ዛሬ አፉን ከፍቶ፤ ሱሩሪዩ ጀይላን - መረቡን ዘርግቶ፤ ያሴረው ሴራ - እውን ሆነ ዘግይቶ፤ የእነ ሳዳትን - የእውቀት ልክ አይቶ፤ ሴራው እንደሚሳከ - በፊትም ገምቶ፤ ሰብሩ ይመለሳል - ይህን መንገድ ትቶ፤ ብሎ ነግሮን ነበር - እውን ሆነ ሰንብቶ፤ የሱሩሪዩ ጀይላን - ዓላማው ተሳክቶ፤ በኢልያስ ፈረስ - ዛሬ ሳዳት ወጥቶ፤ ወደ ተምዪዕ ሄደ - ቀልጦ ተንሸራትቶ፤ የትናንቱ (ገይራ) - ወኔው ሁሉ ቀርቶ፤ በሰላሰዋ ኪኒን - ኢልያስ ጎትጉቶ፤ ሳዳትን ወሰደው - እንደ በግ ጎትቶ፤ የሱሩሪዩ ጀይላን - ዓላማው ተሳክቶ፤ እሺ ብሎ ሄደ - ሳዳትም ተስማምቶ፤ ከትናንቱ መንሀጅ - ከሀቅ ቶብቶ፤ በኢልያስ ፈረስ - ዛሬ ሳዳት ወጥቶ፤ ወደ ተምዪዕ ሄደ - ሰለፊያን ትቶ፡፡            ✍️ (ኢብኑ ኑሪ) መስከረም 9/2017                        ስልጤ (ሳንኩራ) https://t.me/YusufAsselafy https://t.me/YusufAsselafy
إظهار الكل...
🎤 Ibn Muzayan ~ ኢብን ሙዘይን! ሁለንተናዊ ከፍታ የሚገኘው በቁርዓንና ሐዲስ ብቻ ነው።

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته ይህ ቻናል በአላህ ፍቃድ ደዕዋ ሰለፊያ ማሰራጫ ይሆናል ኢንሻ አላህ!! አላህ መልካም የሻለትን~ ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል ።

https://t.me/YusufAsselafy

ሰበር ዜና
📢 ዛሬ በአላህ ፈቃድ ከሳዑዲ በመጡት እንግዳ በዳር አስ-ሱንና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል ልዩ ሙሃዶራ አለን 
🕰 ዛሬ እለተ ሐሙስ መስከረም 9/2017 ከመግሪብ እስከ ዒሻእ ከሳዑዲ ዐረቢያ በመጡት እንግዳ የዚያራና የሙሃዶራ ፕሮግራም አላቸው፣ ላልሰማ በፍጥነት አዳርሱ!! እንግዳችን:- الشيخ الدكتور خالد بن محمد الغفيلي - حفظه الله 👉 ሸይኽ ዶ/ር ኻሊድ ቢን ሙሀመድ አል ጉፈይሊይ (ሀፊዘሁላህ) ዳር አስ-ሱንና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል አዲስ አበባ አለምባንክ አድራሻ:- አዲስ አበባ ኮ/ቀ ክ/ከተማ አለምባንክ ከኦርዶፎ ህንፃ ፊት ለፊት ባለው ቂያስ ወደ ቤተል በሚወስደው ኮብልስቶን መንገድ ከድልዲዩ በስተ ቀኝ ባለው ቂያስ እንገኛለን። ለተጨማሪ መረጃ:- +251920908031 በተጨማሪም ሎኬሽን ⤵️⤵️ https://maps.app.goo.gl/qsBKATgS8jqrJMxw9 የዳር አስ-ሱንና የቴሌግራም 👇👇 ቻናል #join በማድረግ ይቀላቀሉ https://t.me/DarASSunnah1444 https://t.me/DarASSunnah1444
إظهار الكل...
ዳር አስ-ሱንና Dar As-sunnah Channel

ይህ የዳር አስ-ሱንና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል ኦፊሻል የቴሌግራም ቻናል ነው مركز دار السنة لتعليم الشريعة الإسلامية Dar As-Sunnah Sharia Knowledge Center አድራሻ:- አዲስ አበባ ኮ/ቀ ክ/ከተማ አለምባንክ ከኦርዶፎ ህንፃ ፊት ለፊት ባለው ቂያስ ወደ ቤተል በሚወስደው ኮብልስቶን ከድልዲዩ በስተቀኝ እንገኛለን። ለተጨማሪ መረጃ:- +251920908031

👉  የኸድርና የነብዩላሂ ሙሳ ታሪክ                 ክፍል አንድ      ቁርኣን ላይ ትኩረት ከተሰጣቸው አስተማሪ ታሪኮች ውስጥ የነብዩላሂ ሙሳና የኸድር ታሪክ ነው ። በዚህ ታሪክ ውስጥ ትልቁ አስተማሪ ነገር ማንም ቢሆን በእውቀት ጥግ ደርሻለሁ ማለት እንደሌለበት አላህ ከባሮቹ ውስጥ ለሚሻው ሰው ጥበቡ ባስፈረደው የእውቀት አይነት ለየት እንደሚያደርገው ።      በዚህ ታሪክ ውስጥ ነብዩላሂ ሙሳ ረሱልና ከዛም ከፍ ባለ ደረጃ ዑሉል ዐዝም ከሚባሉት ውስጥ ናቸው ። ኸድር ደግሞ በቀደምት የኢስላም ሊቃውንቶችና እስካለንበት ዘመን ባሉ ተከታይ የኢስላም ሙሁራኖች እንደተረጋገጠው ነብይ መሆናቸው ነው ። በመሆኑም ኸድር ማለት ከነብያቶች ውስጥ አንዱ ናቸው ። ይህ ማለት በደረጃ ነብዩላሂ ሙሳ ይበልጣሉ ማለት ነው ። ምክንያቱም የረሱልነት ደረጃ ከነብይነት ደረጃ የሚበልጥ መሆኑ የተረጋገጠ ስለሆነ ። ነብዩላሂ ሙሳ ደግሞ ከረሱልም በላይ አምስቱ ዑሉል ዐዝም የተባሉት ውስጥ ናቸው ።        ነገር ግን የጥመት አንጃ የሆኑት ሱፍዮችና ሺዓዎች ይህን አስተምሮ በማስተባበል ኸድር ወልይ ነው አሉ ። እዚህ ጋር ቢቆሙ አንድ ነገር  ነበር ነገር ግን ከዚህም አልፈው ሄዱ ። ወልይ ከነብይም ከረሱልም ከዑሉል ዐዝም ይበልጣል አሉ ።‼ ለዚህህ ስህተታቸው መነሻው ደግሞ አላህ ነብዩላሂ ሙሳን ኸድር ጋር ሄደህ ተማር ማለቱ ነው ። ይህ ማለት ኸድር አላህ ዘንድ በደረጃ ከሙሳ ከፍ ያለ ስለሆነ ነው ልዩ እውቀት ሰጥቶት ከሱ ተማር ያለው አሉ ። በመሆኑም የኸድር እውቀት የውስጥ እውቀት ( ዒልመል  ባጢን) ነው የሙሳ እውቀት ደግሞ የውጭ እውቀት ( ዒልመ ዛሂር ) ነው  የሚል ፍልስፍና ውስጥ ገቡ ።          ከዚህ በመነሳት በእነርሱ እምነት የነብያት ተከታዮች የውጪውን እውቀት ነው የሚያውቁት የወልይ ተከታዮች ደግሞ የውስጡን ነው የሚያውቁት በመሆኑም የነብያት ተከታዮች የሸሪዓን ሚስጥር አያውቁም ላዩን ነው የሚከተሉት እኛ ደግሞ የሸሪዓን የውስጥ ሚስጥር ስለምናውቅ የውስጡን ነው ምንከተለው አሉ ። በዚህም ነብዩን ጨምሮ ሶሓቦችንና አጠቃላይ ቁርኣንና ሐዲስን የሚከተሉ የኢስላም ሊቃውንቶችን አላዋቂ መሀይማን አደረጉ ።      ይህ እምነታቸው ነው ዛሬ ላይ እየታየ ያለውን የኩፍርና የሽርክ ተግባር እንዲፈፅሙ ያደረጋቸው ። ምነው ሲባሉ እናንተ ስለማታውቁ ነው ኩፍር የሚመስላችሁ ነገር ግን የሙታን መንፈስ ማምለክ ፣ በቀብር ላይ ጠዋፍ ማድረግ ፣ ወደ እነርሱ የተለያዩ ቁሩባን በማቅረብ እነርሱን መለማመን ፣ እርዱኝ ፣ አክብሩኝ ፣ ድረሱልኝ ፣ አሽሩኝ … ወዘተ ማለት ተውሒድ ነው አሉ ።‼      ይህ በተሳሳተ መነሻ ላይ የተመሰረተ የተሳሳተ እምነት ነው ። የዚህ ማሳያው እንደሚከተለው ነው : – 1ኛ – ኸድር ነብይ እንጂ ወልይ አይደለም ።          የነብይነትና የወልይነት ደረጃ አይገናኝም ። የነብይነት ደረጃ በጣም የላቀ ነው ። 2ኛ – አንድ ሰው ሄደህ ከእገሌ ተማር መባሉ ያ           አካል ከሱ መብለጡን አያሳይም ። ይበልጣል ቢባልም በዛ በሚያስተምረው ጉዳይ ነው ሊሆን የሚችለው ። ይህን ወደ ታሪኩ ስንገባ በግልፅ የምናየው ይሆናል ። 3ኛ – የነብዩላሂ ኸድር እውቀት ለራሱ የተሰጠው           እንጂ ሸሪዓ ሆኖ ሊሰራበት አይደለም ። ሸሪዓ ቢሆን እንኳን ለነብዩ ተከታዮች ከዛ በፊት የነበሩ ነብያቶች ሸሪዓ ከቁርኣንና ሐዲስ ወይም ከነብዩ ሸሪዓ ጋር ከተጋጨ አይሰራበትም ሸሪዓም አይሆንም ።        ሱፍዮችና አሕባሾች እያጨማለቁት ላለው ኩፍርና ሽርክ የነብዩላሂ ሙሳና የኸድር ታሪክ በፍፁም መረጃ ሊሆን አይችልም ። ምክንያቱም በባጢል ላይ የተመሰረተ ነገር ባጢል ነውና ።       አላህ ለነብዩላሂ ሙሳ ከኸድር እንዲማሩ የፈለገው እሱ ዘንድ ካለው እውቀት ለሳቸውም ይሁን ለኸድር የተሰጠው በጣም ኢምንት መሆኑን ለማሳየት ነው ። ለዚህ ማሳያ በታሪኩ ላይ ከባህር ላይ የምትጠጣዋን ወፍ ምሳሌ እንዳደረገው ሁሉ ።         የነብዩን ሸሪዓ በፍልስፍና ውድቅ ያደረጉና ኩፍርና ሽርክ ያነገሱ ሱፍዮችና አሕባሾች ታሪኩ በእነርሱ ላይ እንጂ ለእነርሱ መረጃ አይሆናቸውምና በደንብ እንወቀው ። አላህ ካለ ሠዒድ ኢብኑ ጁበይር ከዐብዱላሂ ኢብኑ ዓባስ ዐብዱላሂ ከኡበይ ኢብኑ ካዕብ ይዘው ባስተላለፉትና ኢማሙል ቡኻሪይ በዘገቡት ሐዲስ  ላይ እንደተዘገበው ሙሉ ታሪኩን የምናይ ይሆናል ። በሱረቱል ካህፍ ላይ ይህ ታሪክ ሰፊ ሽፋን የተሰጠው ሲሆን በአቀማመጥ ሐዲሱ ላይ የመጣው ይበልጥ ቀለል ስለሚል የሐዲሱን እናያለን ።       አላህ ካለ ይቀጥላል ። http://t.me/bahruteka
إظهار الكل...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

🟢“ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ ” ለነሲሃ ቲቪ ተፃፈው የተባለው “በመውሊድ ስንጨፍር በካሜራ ቅረፁን” አይነት ደብዳቤ አሳዛኝም አስተማሪም ነው። 👉አሳዛኙ በሱና ማማ ከፍ ካሉ በኋላ ወድቆ ለሙብተዲዕ መሳለቂያ መሆን እጀግ ያሳዝናል። እነ አጅሬ "ነሲሃዎች" ከዚህ በፊትም በርካታ የተጠለፉባቸው ወጥመዶች በደብዳቤ የጀመሩ ናቸው። ከሱፊዮችና መሰሎቻቸው ጋር በተለያዩ የሙጃመላ መድረኮች ላይ ስለሚተዋወቁ ነው የተናቁት ። “ ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ ” እንደሚባለው ነው። በሱና ላይ የነበራቸው አቋም እንደቀለጠ ከጀይላን ጀምሮ ወዳጅም ጠላትም ነገራቸው ። ከዚህም በከፋ ጉዳይ እንደለመዱት እንተባበር ይሉ ይሆናል። 👉አስተማሪው 1️⃣አቋም በወረደ ልክ በጠላት መደፈርና ውርደት ይመጣል ።የአላህ እርዳታም ይርቃል። عَنْ ثَوْبَانَ قَالَ : قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : " يُوشِكُ الْأُمَمُ أَنْ تَدَاعَى عَلَيْكُمْ كَمَا تَدَاعَى الْأَكَلَةُ إِلَى قَصْعَتِهَا ". فَقَالَ قَائِلٌ : وَمِنْ قِلَّةٍ نَحْنُ يَوْمَئِذٍ ؟ قَالَ : " بَلْ أَنْتُمْ يَوْمَئِذٍ كَثِيرٌ، وَلَكِنَّكُمْ غُثَاءٌ كَغُثَاءِ السَّيْلِ، وَلَيَنْزِعَنَّ اللَّهُ مِنْ صُدُورِ عَدُوِّكُمُ الْمَهَابَةَ مِنْكُمْ، وَلَيَقْذِفَنَّ اللَّهُ فِي قُلُوبِكُمُ الْوَهْنَ ". فَقَالَ قَائِلٌ : يَا رَسُولَ اللَّهِ، وَمَا الْوَهْنُ ؟ قَالَ : " حُبُّ الدُّنْيَا وَكَرَاهِيَةُ الْمَوْتِ ". أخرجه أبو داود (4297) وصححه الألباني ሰውባን አሉ ፥ የአላህ መልእክተኛ (ﷺ)አሉ፦" የጥመት ህዝቦች (ለጥቃት) ሊጠራሩባችሁ ይቀርባሉ ፤ ልክ በላተኞች ተሻምተው ወደ ሚበሉት ማዕድ እንደሚጠራሩት ።" ጠያቂ እንዲህ አለ ፥ ያኔ በቁጥር አናሳ በመሆናችን ነውን ? ነቢዩ (ﷺ) አሉ ፦ " እንዲያውም የኔ ብዙ ናችሁ ፤ ነገር ግን እንደ ጎርፍ ግሳንግስ ደካማ ናችሁ ፤ አላህም በእርግጥ ከጠላቶቻችሁ ልብ ውስጥ ለእናንተ የነበራቸውን ክብር  ነቅሎ ያስወጣል ፤ አላህም በእርግጥ በልባችሁ ውስጥ ውርደትን ይጥልበታል ።" ጠያቂ እንዲህ አለ ፥ ከምን የመጣ ውርደት ነው ? ነቢዩም (ﷺ) አሉ ፦ "የዱንያ ውዴታ እና ሞትን መጥላት (አኺራን መርሳት) ።” 2️⃣ለጠላት ማባበያና ማቀራረቢያ አንዴ በር የከፈተ ዲኑን እና ክብሩን ለአደጋ አጋልጧል። ከዕብ ኢብኑ ማሊክ ከገሳን ንጉስ የመጣለትን ማባበያ ደብዳቤ ምን ነበር ያደረገው  ⁉️ ✍  ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊያ) http://t.me/Abuhemewiya
إظهار الكل...
🎤 ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ) ✍

የጠራ እውቀት ከተቃና አቐምና ተግባር ጋር የተረዘቀ ታድሏል !!

Photo unavailableShow in Telegram
🎤 ታላቅ የዳዕዋ እና የንያ ፕሮግራም ጥሪ↩️ ✅ በአይነቱ ለየት ያለ የዳዕዋ እና የንያ ፕሮግራም በውላውላ የሰለፍዮች መስጂድ ገቢ ማሰባሰቢያ ግሩፕ ላይ በቀጥታ ስርጭት (online) ተዘጋጂቷል። የፕሮግራሙ አዘጋጆች፦      ✅ የውላውላ  ሰለፍያ  ጀምዓዎች 🪑 የእለቱ ተጋባዠ እንግችን ፦↩️ 🎙ኡስታዝ ኢልያስ አወል ( አቡ ሷሊህ አልኡሰይሚን) ሀፊዘሁ አሏህ    ዕርስ፦ በእለቱ ይነገራል 🟢 ኢንሻአላህ ሌላም ተጋባዥ እንግዳ ይኖራል 🗓 ፕሮግራሙ የፊታችን ጁመአ  ከምሸቱ 3፡00 ሰአት ቡሀላ ይጀመራል ቀደማችሁ በመገኘት የፕሮግራሙ ተካፋይ ይሁኑ!!! ♻️ ፕሮግራሙን ለመከታተል ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ። ✍በቻናል እና በግሩፓች ሼር በማድረግ ሀላፍትናችንን እንወጣ ➷➷➷➷➷➷➷➷➷ https://t.me/YweIaweIa_Groups https://t.me/YweIaweIa_Groups 🌐 ሸር በማድረግ ሀላፊነታችንን እንወጣ
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
አድራሻውን ማወቅ አልቻልነም ብላችህ ማስተወቂያ ይሰራለት ብለችህ ለተጨነቀችህ ማስተወቂያው ይህ ነው። 👇👇 ✍السلام عليكم ورحمة الله وبركاتهውድ እና የተከበራችህ የመድረሰቱ አል-ወሰጢያ ደርስ ተከተታዮች በሙሉ የነገው እሁድ ደርስ ሰዓቱ እንደተጠበቀ ነው። የሚሰጡ ደርሶች 1  📚ሪያዱ አስ-ሳሊሂን የኢማሙ ነወውይ ከ3:00 -4:00 ድረስ 2  📚ኢርሻድ ዒላ ሰሂሂል እዕቲቃድ የሸይኽ ፈውዛን ከ4:00- 5:00 3 📚ጣሃዊይ የአቢል ኢዝ ከ5:00- 6:00 የመድረሳችን አድራሻ አዲስ አበባ በተለምዶ ስልጤ ሰፈር የሚባለው ሰፈር ከሸምሱ ሬስቶራንት በለችው ቂያስ 25 ሜትር ገባ ብሎ የለው ነው። https://t.me/AbraribnAwal
إظهار الكل...
አስደሳች ዜና ታላቅ የሙሓዶራ ፕሮግራም የፊታችን እሑድ በቀን 12/1/2017 ታላቅ የሙሓዶራ ፕሮግራም በአል- ወሰጢያህ መድረሳ  ከወትሮው ለየት ባለና ባማረ ሁኔታ ስለተዘጋጀ ይህ እድል እንዳያመልጠዎት ስንል እርሰዎን  ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር  በአክብሮት ጋብዘንዎታል።     🪑 ተጋባዥ እንግዶች   1️⃣1⃣ኛ.  ዶር. ሸይኽ ሑሰይን ሙሐመድ አስ-ሲልጢይ ሐፊዘሁሏህ 2️⃣2⃣ኛ.  ኡስታዝ አቡል ቡኻሪ ሙባረህ ኢብራሂም ሐፊዘሁሏህ 3⃣3⃣ኛ አቡ ኡበይዳ አብራር አወል ሐፊዘሁሏህ ሁሉም ርዕሶች በሰዓቱ ይገለፃሉ!!!! ልብ ይበሉ ⤵️ ↪️ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!!! አድራሻ፡- አዲስ አበባ ስልጤ ሰፈር አል-ወሰጢያህ መድረሳ እለተ፡-  እሑድ 12/1/2017 ሰዓት፡- ከጠዋቱ 3: 00 ጀምሮ 🌷ለሴቶችም በቂና ምቹ ቦታ ተዘጋጅቷል!!!!   ጥብቅ ማሳሰቢያ : – 👉 ይህንን በአይነቱ ልዩ የሆነ ፕሮግራም እንዳያመልጥዎ ፕሮግራሞትን ከወዲሁ በማመቻቸት ከቤተሰብዎ፣ ከጓደኛዎ፣ ከስራ ባልደረባዎ ጋር ለመታደም ቁጥር 1️⃣ ፕሮግራምዎ አድርገው ይያዙ።   👉 ጥሪን ማክበር ኢስላማዊ ስነ-ምግባር ነው!!!   ✍️አዘጋጅ፡- አል- ወሰጢያህ መድረሳ https://t.me/AbraribnAwal https://t.me/AbraribnAwal
إظهار الكل...
ሐያእ (አይናፋርነት) ለሴት ልጅ ትልቁ ሀብቷና ውበቷ ነው!! ————— ሐያእ በመሰረቱ ወንዱም ሴቱም ጋር ሊኖር የሚገባው ተወዳጅ ምርጥ ባህሪ ነው። በተለየ መልኩ ግን ሴቶች ዘንድ ወሳኝነት አለው። ይሁን እንጂ ሐያእ (አይናፋርነት) የሚባለው ነገር አላህ ካዘነላቸው ጥቂት እንስቶች በስተቀር "ብን!" ብሎ የጠፋ ይመስላል። ሴት ልጅ አይናፋርነት ከሌላት እንዲሁ ባህሪዋ ለባሏ እንኳ አይማርከውም፣ ምክንያቱም አይናፋርነት ለሴት ልጅ ከፈጣሪዋ ከአላህ የተሰጣት ልዩ ውበትና ግርማ ሞገሷ፣ ተፈጥሯአዊ የሆነ ስጦታዋ ነውና። ሀያእ (አይናፋርነት) የሚባለው ነገር ከብዙ ሴቶች ልብ ድራሹ ጠፍቶ በስመ ስልጣኔ ጋጠ-ወጥ ሴቶች አስባልቱን ከሞሉት ሰነባብቷል። እንዲያውም አንዳንዴ በተቃራኒው ሀያእ የሚባለው ነገር ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ዘንድ ይስተዋላል። በተለያዩ ዝግጅቶች፣በተለይ በሰርግና የተለያዩ የሺርክ ስንኞች የተሞሉበት መንዙማና ነሺዳ በሚደለቅበት መውሊድ ላይ ከወንዶች ጋር ለመዝለልና ለዚና ሀያእ የሚባል ነገር አሽቀንጥረው ጥለውት ይወጣሉ። " እህቴ ሆይ! ቁርኣን አንድን ነገር ሲጠቅስ ያለ ምክንያት አይደለም!። ይልቅ ከእኛ መተገበሩ ወይም መጠንቀቁ ተፈልጓል ማለት ነው። ለምሳሌ አላህ ስለ ነቢዩላህ ሙሳ (ዐለይሂ ሰላም) ስደት ላይ ሆነው የገጠማቸውን ሲተርክ እንዲህ በማለት የአንዲትን እንስት አካሄድ አውስቷል:- فَجَاءَتْهُ إِحْدَاهُمَا تَمْشِي عَلَى اسْتِحْيَاءٍ «ከሁለቱ አንደኛይቱም ከሐፍረት ጋር የምትሄድ ሆና መጣችው፡፡» አል-ቀሰስ 25 ሸይኽ ናሲሩ ሰዕዲ (ረሂመሁላህ) ይህን አንቀፅ ሲያብራሩ ተፍሲራቸው ላይ እንዲህ አሉ:- “ይህ የሚያመላክተው የመልካም ስነ-ምግባር ባለቤት መሆኗን ነው፣ ምክንያቱም አይናፋርነት በላጭ ከሆነው ከመልካም ስነ-ምግባር ነው!፣ በተለይ በሴቶች ላይ።” [ተፍሲሩ ሰዕዲ] "ከሀፍረት ጋር የምትሄድ ሆነ…" በማለት አካሄዷን አውስቷል፣ አላህ ይህን አካሄድ አንቺም ከቤት የሚያስወጣሽ አስገዳጅ ነገር ሲኖር ተግባራዊ እንድታደርጊው ፈልጓል ማለት ነው። አለባበስሽ ሸሪዐው የሚፈልገው አይነት ሆኖ በጅልባብና ኒቃብ የተሰተርሽ ሆነሽ ብትወጪ እንኳን ይህ አይናፋርነት ፈፅሞ ሊለይሽ አይገባም!። ምክንያቱም ሀያእ ከፈጣሪሽ ዘንድ የተቸረሽ ትልቁ ሀብትሽና ውበትሽ ነው!። " ነቢዩ እንዲህ ብለዋል:- “ኢማን ከሰባ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፣ ሐያእ ከኢማን ቅርንጫፍ ነው።” ቡኻሪይ ዘግበውታል " የነዚያ ጋጠ-ወጦች ጩሃት ሸንግሎሽ በስመ-ስልጣኔና ግልፀኝነት ሀያእሽን አትልቀቂው የአንቺ የሙስሊሟ እንስት የፈጣሪዋ ትልቅ ችሮታ ነው!!። ሀያእ የሚባለውን የተፈጥሮ ስጦታሽንና ሀብትሽን ለማቆየት ምናምንቴዎችን ትተሽ ጓደኝነትሽን ሀያእ ካላቸው እህቶችሽ ጋር አድርጊው!። ጓደኛሽ ሀያእ ከሌላት ሙተነቂብ መሆኗ አለያም ከአንቺ በላይ እውቀት ስላላት አትሸንግልሽ!፣ ከቻልሽ ሀያእ እንዲኖራት ምከሪያት! ካልተስተካከለች ግን ራቂያትና ሀያእ ያላቸውንና ዲናቸው ጠንካራ የሆኑ እህቶችሽን ጓደኛ አድርጊ!። " ወንድሜ ሆይ! ልታገባ ስታስብ ሀያእ ያላትን ሴት መምረጥ እንዳለብህ አትዘንጋ!። ልታገባት ያሰብካት ሴት ምናልባት ማሻ አላህ አለባበሷ ሸሪዐዊ የዲን እውቀቷም እንደዛው ሊሆን ይችላል፣ ግን ሀያእዋ እንዴት ነው?!። ምክንያቱም ሀያእ ትልቅ ዋጋ አለው! በዚህ አስቸጋሪ ማህበረሰብ በበዛበት ዘመን ሀያእ የሌላት እንስት ከራሷ የባሰ ሀያእ የሌለውን ትውልድ ቢሆን እንጂ ሀያእ ያለውን ትውልድ ልታፈራ አትችልም!!። ሀያእ እየጠፋ የመጣ የሙስሊም እንስቶች ትልቅ ሀብት ነው!! እህቴ ሆይ! ትልቁን ሀብትሽን ውበትሽን፣ የፈጣሪሽን ስጦታ ፈልገሽ አጥብቀሽ ያዢው!! ✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa) #join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
إظهار الكل...
[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]

Photo unavailableShow in Telegram
"ገርሞ ገርሞ ይገርማል" ኣለ ኡስታዝ ባህሩ ተካ ጉዳቸውን ተመልከቱ!!! ከወረዱ አይቀር ውርድርድ ነው እንጂ?!
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.