cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Zeraf Books

Your #1 Source For Ethiopian Books Shipping Worldwide 🇺🇸🇨🇦🇩🇪🇬🇧🇰🇷🇮🇹~🌎 & Delivering Locally. Work Phone 📲 +251985333153 Inbox Your Inquiries To @Zerafb

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
9 147
المشتركون
+524 ساعات
+197 أيام
-5230 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
ጸበልተኞቹ ተጋግዘው የአባቷን አስክሬን ማሰናዳት ጀመሩ። እሷን አንዲት ሴት ከድንኳኑ ውጪ ወሰደቻት። ''አይዞሽ የኔ ቆንጆ...ስምሽ ማነው ግን? ጠየቀቻት ሴትዬዋ። ይሄኔ ቃልኪዳን ለቅሶዋን ገትታ ቀና አለች እና አይኗን በአይብሉባዋ ጠርጋ ተረጋግታ የጠየቀቻትን ሴት አይን አይኗን እያየች መለሰች። ''አኒያኑ'' ብላ መለሰች። ሴትዬዋም የቃልኪዳንን ለቅሶ ለማረሳሳት፤ ወሬውን ለመቀጠል አስባ ''ምን ማለት ነው? ሰምቼው አላውቅም ይሄንን ስም'' ብላ ድጋሚ ጠየቀቻት... ''የፀሐይ ዐይን ነው።'' መለሰች ቃልኪዳን። ''ፀሐይ ዐይነሰ አላት?'' አሁንም ጠየቀች ሴትዬዋ፤ ቃልኪዳንም ተረጋግታ መለሰች። ''አዎ! በግለት ብዛት የማይቀልጥ፤ በሙቀት የማይጠፋ፤ ብሩቱ ፅኑ ዐይን አላት ፀሐይ።'' በዚህ ጊዜ ግን ፊቷ ላይ ከቅድሙ ኀዘን የሚቃረን ብሩህነት ይነበብ ነበር።'' °°°°°°° ''የሐምራዊ ተረኮች'' ደራሲ ኤልሳ ሙሉጌታ ፣ ''ዋናተኛ ፀሐይ'' በሚል አዲስ ስራ ተመልሳለች።
إظهار الكل...
7👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
📖 ''የበደል ፍፃሜ'' ይህች መጽሐፍ የምታወሳው ስለ አንድ ባንዳ ክህደት፣ በደልና ወንጀል እንዲሁም አነሣሱና አወዳደቁ ነው። ይህንን ወንጀለኛ ተጋትሮ፣ ወንጀሉን ተከታትሎ በፍርድ ዐደባባይ ፍትሕ ስላሰፈነ ጽኑዕና ብርቱ ሰው እንዲሁም አስደናቂ ባለቤቱ ነው። ስለ "የመንገድ ዶሮ" የሚተርከው በማዋዣነት የገባው የጎንዮሽ ተረክ ያስገርማል፤ በራሱ ሌላ ዓይነት የበደል ፍጻሜን ያሳያል። "…እንደምታውቀው ስንቅ ለመንገደኛ ነው። የዚያን ጊዜ [ጣልያን ኢትዮጵያን ዳግም ከመውረሯ በፊት ባሉት ዓመታት] መኳንንቶች የሚያደርጉት እንደዚህ ነበር። በረሃ እንዳይሔዱ እግራቸው ለሰለሰ። ከዕልፍኛቸው ተቀምጠው ሲውሉ፤ ዶሮ ከማዕድቤት ተሠርቶ፣ በአገልግል ተለጉሞ፣ በበቅሎ ተጭኖ ከአሽከር ጋር በገጠር ዞሮ ይመጣላቸዋል። ያ ተፈትቶ ይበላል። ከብት የሌለው በአሽከር እንጦጦ ጋራ ደርሶ የመጣ የመንገድ ዶሮ ይበላል። ጥሩ በቅሎ ከመልካም አሽከር ጋር ያለው፣ ደግሞ ናዝሬት፣ ደሴ ደርሶ ይመለስለታል። የመኳንንቱ ጌትነት የሚለካው የመንገድ ዶሮው በሚደርስበት ርቀት ነው። በአገልግል ታፍኖ ሲውል ሲያድር እጅእጅ የሚል ምግብ የሚያስመርጥ ጥጋብ ነበር። ክፉ ቅንጦት ወርዶ ነበር። ግን ዋጋውን ከፈልነዋ!" [የ ''መንገደኛ'' ደራሲ ዮርዳኖስ አልማዝ ሰይፉ እንዳጋራው] ~ Inbox @Zerafb  To Order. Shipping Worldwide 🇺🇸🇨🇦🇫🇷🇩🇪🇮🇹 & Delivering Locally.
إظهار الكل...
የአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን መጽሐፍ ቅዱስ (81 አሐዱ) የህትመት ዘመን - 1953 ዓ.ም. *Extermely Expensive due to its rariety* °°°°°°°°° Inbox @Zerafb To Order. Shipping Worldwide 🇺🇸🇨🇦🇮🇹🇩🇪🇫🇷🇰🇷 & Delivering Worldwide.
إظهار الكل...
1
Photo unavailableShow in Telegram
1) The Iliad - Homer Translated By W.H.D. Bouse 2) American History and The Black Question A Book By R. Ivanov 3) ባለውሻዋ እመቤት - አ. ቼኾቭ 4) የአንድ ሰው እጣ - ሚከሃይል ሾሉከሆቭ ~
إظهار الكل...
የመጽሐፉ ርዕስ:- የድንቁርና ጌቶች : ሞገሱን የገፈፉት ዩንቨርሲቲ (1983-2012 ዓ.ም.) ጸሐፊና አዘጋጅ:- ብርሃኑ ደቦጭ የገፅ ብዛት:- 412 የህትመት ዘመን:- 2012 ዓ.ም. °°°°°°°°°°°°° Inbox @Zerafb or call us @ 0985333153  Order. Shipping Worldwide 🇺🇸🇨🇦🇮🇹🇩🇪🇫🇷🇰🇷 & Delivering Worldwide.
إظهار الكل...
ከማዕበል ማዶ (በደራሲ ተስፋዬ ማሞ) ጀንበር አዘቅዝቃ ነፋሻው አየር የቀኑን ወበቅ እየገፋ ቦታውን ሲረከብ፤ ሕይወት እንደ አዲስ ማንሰራራት ትጀምራለች፡፡ አሰብ ከቢር ከኋይት ሆርስ ወይም ከአልማዝ ቂጦ ቤት ጀምሮ፤ ባር ኢትዮጵያ… ባር ጆርዲኖ… ወሎ ቡና ቤት... ቀስተ ደመና… ባር ፍሎሪዳ... ባር ሜክሲኮ... ጣዕመ ቤት፤ ወይም ካምቦ ሱዳን ከፓትሪስ ሉሙምባ እስከ ድሬዳዋ ቡና ቤት... አስብ ስቂር... ብቻ ቢራ አለባቸው የሚባሉና ነፋሻማ ቡና ቤቶች፤ ደጃቸው ክብ ክብ ሠርተው የቀኑን ሙቀት በሚያራግፉ ሰዎች ሳቅና ጨዋታ ትደምቃለች...." “.....በየጎዳናው ላይ ሰው የሩጫ ያህል ወደየቤቱ ሲምዘገዘግ ሲታይ ያስፈራል፡፡ አንዳች ነገር ከኋላው የሚያባርረውና መደበቂያ ፍለጋ የሚሮጥ እንጅ ወደቤቱ የሚገባ አይመስልም፡፡ ልክ 12 ሰዓት አናቱ ላይ ሲሆን፤ በአሥመራ የብዙኃኑ የሰዓት መቁጠሪያ የሆነውና መሐል ኮምፕሽታቶ የሚገኘው የካቴድራል ሰዓት ግርማ-ሞገሳም የደወል ድምጽ ከዳር ዳር ሲያስተጋባ የአሥመራ ጎዳናዎች ከጫፍ ጫፍ ጸጥ ረጭ ይላሉ፡፡ ይህ ሁኔታ በተለይ ለእንደኔ ዓይነቱ የመሐል ሀገር ሰው፤ አልቅስ አልቅስ የሚል ስሜት የሚፈጥርና፤ በጠላት ወረዳ ውስጥ ተቆርጦ ብቻውን የቀረ ወታደር ዓይነት ስሜት እንዲሰማ የሚያደርግ ነበር። …ልብሶቹ በእኔ ልክ የተዘጋጁ እስኪመስል ድረስ ልክክ አሉብኝ:: “መቼም የእሱ ሊሆኑ አይችሉም" ስልም አሰብኩ:: እሱ ድንቡሽቡሽ ያለ ወፍራም፣ እኔ ደግሞ ቀጭን ከሚባሉት የምመደብ፣ የሰውነታችን አቋም ልዩነት የትየለሌ ነው:: "ከየት አመጣኸው?” በማለት ተገርሜ ጠየቅኩት፡፡ ልብሶቹ ፀጋዬ የሚባል የተረሸነ የአየር ኃይል ባልደረባ የነበረ ጓዳችን ልብሶች ነበሩ። ይህንን ስሰማ የተሰማኝን ስሜት በፍጹም አላውቀውም:: የተሰዋ ጓድን ልብስ መልበስ የፈጠረብኝን ስሜት ልረዳው አቃተኝ:: ለአንድ አፍታ ሞትን ራሱን የለበስኩት ያህል አቅለሽላሽ ስሜት ተሰማኝ። ግን ምንም ምርጫ የለኝም። "በርቀት ከቅጥልጥል ጉብታና ተራራዎች ሥር ባለ ረባዳ ቦታ ላይ የሚትጎለጎል ጥቁር ጭስ አየሁና ሰውነቴን አንዳች ነገር ወረረኝ፡፡ አፌ እንዳመጣልኝም ወዲያው ኮሎኔሉን፤ “ኮሎኔል አደጋ አለ!" አልኳቸው:: ኮሎኔሉ ገልመጥ አድርገውኝ አሻግረው ከተመለከቱ በኋላ፤ “ኧረ በስመአብ በል! የምን አደጋ አመጣህ! ምናልባት ጫካ ነገር ተቃጥሎ ሊሆን ይችላል" አሉኝ:: እሺ አላልኳቸውም:: ፈጥኜ የፓርቲ መታወቂያ ደብተሬን ከኪሴ አውጥቼ ወደ ወንበር ስር እየወሸቅኩ፤ “እንዴ ኮሎኔል ይመልከቱ ጭሱ እኮ ጥቁር ነው... ጫካ ሊሆን አይችልም!" እያል ብሞግታቸውም አልሰሙኝም። እየተጠጋን ስንሄድ የእንጨት ወይም የጫካ ቃጠሎ ሳይሆን እኔ እንደፈራሁት ሆነ። ጥቁሩ ጭስ እየተትጎለግለ ወደ ሰማይ ይወጣል፡፡ ተደነጋገጥን......." (ከመጽሐፉ የተወሰደ)
إظهار الكل...
👍 2
Repost from Zeraf Books
BLACK LIONS: The Creative Lives of Modern Ethiopia's Literary Giants and Pioneers A Book by Reidulf Molvaer Page Count : 426 Published in 1998 * Inbox @Zerafb or call us @ 0985333153 To Order. Shipping Worldwide 🇺🇸🇨🇦🇫🇷🇩🇪🇮🇹 & Delivering locally.
إظهار الكل...
👍 1
“ከሰንጋ ተራ እስከ አምስተርዳም” "መገን ያራዳ ልጅ አይፈራም ኪሳራ፣ ጃኬቱን አሲዞ ገባ ሰንጋ ተራ፡፡" መቼስ ስለ ያ ትውልድ ብዙ ተብሏል . . . ብዙ ተጽፉል፣ 1. አሰፋ እንደሻው፣ ለአገር የተመደበ ህይዎት 2. ህይዎት ተፈራ፣ Tower in the Sky (ማማ በሰማይ) 3. ብርሃኑ አስረስ፣ ማን ይናገር የነበረ፣የታህሳሱ ግርግርና መዘዙ 4. አማረ ተግባሩ፣ ኃይሌ ፊዳና የግሌ ትዝታ 5. ካሕሳይ አብርሃ፣ የአሲምባ ፍቅር 6. በቀለ ሹሜ፣ የሰሚ ያለህ የኢትዮጵያ ህዝቦች እሪታ 7. ታደለች ኃ/ሚካኤል፣ ዳኛው ማን ነው? 8. ፍሥሀ ደስታ፣ አብዮቱና ትዝታዬ 9. ገነት አየለ፣ የኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማርያም ትዝታዎች 10. ሀብታሙ አለባቸው ፣ የሱፍ አበባ 11. እዮብዘር ዘውዴ፣ የተራማጆቹ መጨረሻ፣ የለውጥ እንቅስቃሴ በዘመናዊት ኢትዮጵያ 12. እያሱ አለማየሁ፣ የሶሻሊስቱ ጠንቋይ፣ የትውልድ እልቂት 13. አብዩ ብርሌ (ጌራ)፣ በአገር ፍቅር ጉዞ ቅጵ ፩ 15. ክፍሉ ታደሰ፣ ያ ትውልድ ቅጽ 1... 16. ፍቅረሥላሴ ወግድረስ፣ እኛና አብዮቱ «አንድ ደራሲ ስለራሱና ስለዘመኑ መፃፍ ሲችል ብቻ ነው ስለሁሉም ሰውና ስለሁሉም ጊዜ መፃፍ የሚቻለው።» ይላል ጆርጅ በርናድ ሸው። --- የመጽሀፉ ርእስ “ከሰንጋ ተራ እስከ አምስተርዳም” ይላል። ጸሐፊው ደግሞ ዶ/ር መላኩ ተገኝ ናቸው። ባለ 300 ገጽ መጽሐፍ ነው። የታተመው ሰኔ ወር 2011 ዓ.ም ላይ ሲሆን አሳታሚውም “ሊትማን መጻሕፍት” ነው፡፡ ℹ️በመጽሐፉ ሽፋን ላይ ከርዕሱ በላይ የትንሹ መላኩ ፎቶግራፍ ይታያል፡፡ ℹ️ከርዕሱ በታች ደግሞ ‘ከታኅሣሥ ግርግር በፊት የተወለደ የአንድ ያዲሳ’ባ ልጅ ግለ ታሪክ’ የሚል ሃረግ አለ፡፡ ℹ️ወረድ ብሎ ደግሞ የብሔራዊ ቴአትር አካባቢና አምስተርዳም ውስጥ የሚገኙ ሁለት ህንፃዎች ፎተግራፍ አለ፡፡ ℹ️ከመጽሐፉ ሽፋን ጀርባ ደግሞ የዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ባለቤት የወ/ሮ ፍቅርተ ገ/ማሪያም፣ የዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይና የወጣቱ መላኩ ተገኝ በአውሮፓ ስዊዘርላንድ ውስጥ በ1973 የተነሱት ፎቶግራፍ ይታያል፡፡ ℹ️የመጽሐፉ አበርክቶት፡ “ለኢህአፓዬ” ይላል ℹ️መጽሐፉ አራት ምዕራፎችና 300 ገጾች አሉት፡፡ ℹ️መጨረሻ ላይ ማለትም ገጽ 300 ላይ ምዕራፍ 4.5 የምትል ግማሽ ገጽ የማትሞላ ወቀሳ መሰል የግጥምና የዝርዝር ፅሁፍ አለች፡፡ ℹ️መጽሐፉ ከሽፋኑ ጀምሮ እስከ መግቢያው ድረስ ያሉት ፅሁፎችና ምስሎች የአንባቢን ቀልብ የሚስቡ በመሆናቸው ለመጽሐፉ ተነባቢነት የራሳቸውን አስተዋፅዖ አድርገዋል፡፡ ℹ️የገጽ ቅንብሩና የሽፋን ቀለሙም ማራኪ ናቸው፡፡ ℹ️በውስጥ ርዕስ ገፅ ላይ የሰፈረችው ግጥም መጽሐፉ ቁም ነገር ብቻ ሳይሆን አዝናኝ ፅሁፍም እንደያዘች የሚያመለክት ይመስላል መገን ያራዳ ልጅ አይፈራም ኪሳራ፣ ጃኬቱን አሲዞ ገባ ሰንጋ ተራ፡፡ (መገን ያራዳ ልጅ…)፡፡ ℹ️በመጽሐፉ ገጽ 8 ላይ የሰፈረው አጭር መግቢያ መጽሐፉ እንዴት መነበብ እንዳለበት ማሳሰቢያ ቢጤ (disclaimer) ያዘለ ነው፡፡ ℹ️ መጽሐፉ “ትውስታ እንጂ የግል ታሪክ አይደለም” ይሉናል ዶ/ር መላኩ፡፡ ℹ️ በ “ትውስታ” እና በ “ግለ-ታሪክ” መካከል ያለውን ልዩነት ባይነግሩንም “ትውስታ” በእንግሊዘኛ memoir ሲባል ግለ-ታሪክ ደግሞ auto-biography ይባላል፡፡ ሌላ ሰው ሲፅፈው ደግሞ biography ይባላል፡፡ በትውስታና በግለ-ታሪክ መካከል የመጠን ልዩነት ካልሆነ በስተቀር “ይህ ይካተት፣ ያኛው አይካተት” የሚል የተፃፈ ህግ ያለ አይመስለኝም፡፡ ዶ/ር መላኩ ኢሕአፓን ተንተርሶ ስለ ግል ሕይወቱ መጻፍ ታሪካዊ ተገቢነቱም ሆነ መብቱም እንደሌላቸው ይግለጻሉ፣ ነገር ግን ይህን ከማድረግ የሚከለክላቸው ሃይል ወይም የተፃፈ ህግ ያለ አይመስለኝም፡፡ በኢሕአፓ ዙሪያ ብዙ ባይባልም በርከት ያሉ መጻሕፍት ተፅፈዋል፤ ከእንግዲህም ብዙ የሚፃፍ ይመስለኝል፡፡ ብዙዎቹ ስለኢሕአፓ ሲፅፉ ስለ ግል ህይወታቸውም ሆነ ስለ ድርጅቱ በስፋት ዘግበዋል፡፡ ስለዚህ የታሪክ ብዥታን ከማጥራት ውጭ ምንም የሚያስነውር ነገር አልፈፀሙም፡፡ ዶ/ር መላኩ ከዚህ በፊት በአማርኛም ሆነ በእንግሊዘኛ የፃፋቸውን ፅሁፎች አበርክተዋል ፡፡ በሁለቱም ቋንቋዎች በተመሳሳይ ብቃትና ጥራት ብሎም ጥልቅ ትንተና የሚፅፍ ድንቅ ፀሐፊ ናቸው፡፡ (© መሐመድ አወል)
إظهار الكل...
👍 3 1
Photo unavailableShow in Telegram
👍 2
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.