cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የሱናዋ ቆንጆ በተውሂድ ያበበች

የሀቅ ዘበኛ የቢደዓ ጥላት እውነተኛ ቆንጆ አምሳያ የሌላት አቋሟ ቀጥ ያለ እንደ ወሀ ሙላት💎💎 t.me/yesunawakonjobetwuhidyabebech

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 521
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+107 أيام
+1130 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

"ዱንያን በኪሳችን ዲኑን በቀልባችን " 📌ይህንን ፁሁፍ በተደጋጋሚ ታክሲ ላይ እመለከታለሁ ግን ግን ገርሞ ግርም የሚለኝ ሁሉም ባይባል አብዛሃኞቹ —በውሸት —በማጭበርበር —ከአንድ ስፍራ ወደሌላ ስፈራ ሲጓዙ በሙዚቃ ቅውጥ አድርገው ነው የሚንቀሳቀሱት : : አጂብ ወላሂ የኛ ነገር በጣም ይገርማል ሁለ ነገራችን “ታቤላ”ብቻ ሆኖ ቀረ ወላሂ አላህ ይዘንልን ሼይኽ,ኡስታዝ,ዳዒ, …………እየተባሉ መሞጋገስ ቀርቶ ተግባር ላይ ትኩረት ቢደርግ ስም ብቻ መኖሩ የአንድን ነገር እውነታ አየቀይረዉም እንንጠንቀቅ ጃል https://telegram.me/abutoiba https://telegram.me/abutoiba
إظهار الكل...
የሞኝ ቀልድ አትቀልድ! ~ በጩቤ፣ በዱላ፣ በመጥረቢያ፣ በመኪና፣ በጦር፣ በጠመንጃ፣ በሰይፍ፣ … ሰዎች ለማስደንገጥ ከመቀለድ፣ ከመቃጣት ተጠንቀቅ። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:– من أشار إلى أخيه بحديدة فإن الملائكة تلعنه حتى ينتهي. "ወደ ወንድሙ በመሳሪያ የጠቆመ እስከሚታቀብ ድረስ መላእክት ይረግሙታል።" [ሙስሊም] በሌላም ሐዲሥ እንዲህ ብለዋል:– لا يحل لمسلم أن يروع مسلماً. "ሙስሊም ሙስሊምን ሊያስደነግጥ አይፈቀድለትም።" አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ:– "አንድ ሰው የምሩንም ይሁን በቀልድ ወደ ወንድሙ ጠመንጃ ሊያዞር አይፈቀድለትም። መኪናም እንዲሁ (አይፈቀድም)። የከፋ ነውና።" [ሸርሑ ሶሒሒል ቡኻሪ: 9/ 502] = (ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 30/2010) የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

Photo unavailableShow in Telegram
⤵️ዛሬም ሀሳባችን መርከዝ ቢን አብ'ባስ ላይ ነው *"""""""""""""" ሌላ ዙር የዳእዋና የኒያ ፕሮግራም *** የሙሓደሯ ተጋባዥ ኡስታዞች 1⃣D/r ሰኢድ ሙሣ 2⃣ ሸይኽ አቡ አማር አወል ቢን አሕመድ 3⃣ኡስታዝ አቡ መርጃን ኸድር ቢን አሕመድ 4⃣ ኡስታዝ አብዱ ሽኩር 5⃣ ኡስታዝ አቡ ሐሳን     🔢ሌሎች ተጋባዥ ወንድሞች ይኖራሉ ተብሎ ይገመታል። 💶ፕሮግራሙን በመምራት ወንድማችሁ አቡ ኡበይዳ አብሮ ይቆያል 📣 ጅሙኣ ከ3:30🕰 በኋላ ምሽቱን ከእኛ ጋር ናችሁ። #️⃣የፕሮግራም ስርጭት ሊንክ t.me/+lmLw2jJXwF45Zjdk
إظهار الكل...
👍 3
✉️ደጋግመን ወንጀሎችን እየፈፀምን ይሰትረናል፤ ሰትሮም ሰዎች ፊት ንፁህና ውብ አድርጎ ያቆመናል ፥ አልፎም ወንጀላችንን ይምርልናል። ጌታዬ▫️
إظهار الكل...
👍 4🍓 1
በሹብሃ የወደቁ ወንድሞች የጠየቁት ጥያቄ እና መልሶች በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ(አቡ ሓቲም) https://t.me/UstazKedirAhmed/8218 https://t.me/UstazKedirAhmed/8218
إظهار الكل...
ሹብሀት እና መልሶቻቸው.mp310.49 MB
መስከርም ሲመጣ ትዝ ከሚሉ ነገራቶች አንዱ ትምህርትና ተማሪዎች አይደሉ? እኛም ይሄን ብለን #ደብተርና #እስክርቢቶ ማቅረብ ጀምረናል።እናም እንድናደርስልዎ የሚፈልጉት ነገር ካለ ይዘዙን በተመጣጣኝ ዋጋ እናደርሳለን። ማድረስ የምችልባቸው አካባቢዎች፦ 1,እዚሁ በከተማችን ኬሚሴና አካባቢዋ 2,ሀርቡ 3,መኮይ #በዛ ያለ ነገር ካዘዙኝ ኮ/ቻ እና ደሴም ማድረስ እችላለሁ። ስትፈልጉ ከስር ባለው #ዩዘር_ኔም ግቡና ጻፉልኝ @AbuOubeida1 ማንቂያ፦በዚሁ አጋጣሚ አቅመ ደካሞችን(ለልጆች ማስተማሪያ ደብተርና እስኪርብቶ መግዛት ለሚሳናቸው ወገኖች ማገዝ የምትፈልጉ ካላችሁ በዚሁ አጋጣሚ ለርሱም በማድረስ የግል ትብብሬን እንደማደረግ ከወዲሁ ላሳውቃችሁ እወዳለሁ)። *በቅርቡ እስከ ሀይቅ የረዘመ ጉዞ ስላለኝ ብታዙኝ እሰከዛ ማድረስ እችላለሁ። አቡ ኡበይዳ t.me/AbuOubeida
إظهار الكل...
👍 1
ታላቁ የሐዲሥ ፈርጥ ከአውሮፓዊቷ አልባኒያ ምድር ~ የዘመናቸው ምሁራን አላህ በየክፍለ ዘመኑ ዲኑን እንዲያድሱ ከሚልካቸው የለውጥ ሰዎች አንዱ እንደሆኑ ያምናሉ። በሐዲሡም በፊቅሁም መስክ የነጠረ እውቀት ያካበቱ ለመሆናቸው ሁለት ሚዛናዊ ሰዎች አይወዛገቡባቸውም፣ ሸይኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አል አልባኒይ ረሒመሁላህ። ሸይኹል አልባኒይ በ1332 ዓመተ ሂጅሪያ (1914 እ.ኢ.አ) በጊዜው የአልባኒያ ዋና ከተማ በነበረችው አሽቆድራ ተወለዱ። ቤተሰባቸው ድሃ ግን ኢስላማዊ ድባብ ያከበረው ነበር። አባታቸው ሐጂ ኑሕ ከኢስታንቡል የሸሪዐ ተቋም የተመረቁ ሲሆኑ በአካባቢያቸው እውቅ የሐነፊያ መዝሀብ አስተማሪ ነበሩ። በአልባኒህ የልጅነት ዘመን ሀገራቸው አልባኒያ አሳዛኝ በሆነ ታሪካዊ ቀውስ ውስጥ ወደቀች። በጊዜው የሀገሪቱ መሪ የነበረው አህመድ ዛጉ ሀገሪቱን መርዛማ ዝገት አለበሳት። ሀገሪቱ ፅንፈኛና ለኢስላም ጥላቻን የደቀነ ምእራብ-ወለዱን የክህ .ደት ስርዓት/ሴኩላሪዝም የሀገሪቱ ስርዓት አድርጎ አወጀ። የዚህን ጊዜ ነበር የአልባኒይ አባት ሐጂ ኑሕ ከነቤተሰባቸው ኩፍርን ሸሽተው ሂጅራ ያደረጉት፣ እትብታቸው ከተቀበረበት አልባኒያ ወደ ደማስቆ ሶሪያ። ለአላህ ሲባል የተከፈለ ታላቅ መስዋእትነት! አልባኒይ ይሄንን የአባታቸውን ውለታ እንዲህ ሲሉ ደጋግመው ያነሱት ነበር። “ጌታዬ በኔ ላይ የዋለውን ፀጋ ቆጥሬ አልዘለቀውም። ምናልባትም ከዋለልኝ ፀጋዎች ሁሉ ትልልቆቹ የአባቴ ወደ ሻም መሰደድና የሰዓት ጥገና ሙያውንም ለኔ ማስተማሩ ነው።” ሸይኹል አልባኒይ በደማስቆ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በከፍተኛ ውጤት ቢያጠናቅቁም መደበኛው ትምህርት የአባታቸው ፍላጎት አልነበረምና ሳይገፉበት ቀርተዋል። ይሁን እንጂ በቁርኣን፣ በተጅዊድ፣ በነሕውና ሶርፍ እንዲሁም ፊቅህ በሐነፍያ መዝሀብ አጠናክረው ቀጠሉ። ቁርኣንን ካባታቸው ላይ የሐፈዙት ሸይኹልአልባኒይ የሰዓት ጥገና ሙያንም በሚገባ ቀስመዋል። በሙያውም ታዋቂ ከመሆናቸውም በላይ እየጨመረ ለመጣው ዲናዊ ትጋታቸው ጊዜ እንዲኖራቸው አስችሏቸዋል። የሐነፊያን መዝሀብ አጥብቀው የሚከተሉትና ከሱ ውጭ ግራ ቀኝ ማየት የማይፈልጉት የአልባኒይ አባት ልጃቸውም በዚሁ ፈለግ እንዲጓዝ ካላቸው ፍላጎት የተነሳ በሐዲሥ ጥናት ላይ እንዳይሰማሩ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ነበር። ይሁን እንጂ የአንድን መዘሀብ ጭፍን ተከታይነት በፅኑ ለሚያወግዙት አልባኒይ ይሄ ነገር ፈፅሞ የሚዋጥላቸው አልሆነም። ገና በሀያ ዐመታቸው አካባቢ ነበር የሐዲሥ ጥናታቸውን አፋፍመው የጀመሩት። ለጥናታቸው አጋዥ የሆኑ ኪታቦችን አቅማቸው በፈቀደ እየገዙ ከዚህ ባለፈም ደማስቆ ከሚገኘው “አዟሂሪያ” ቤተ መጻህፍት እየተዋሱ ይጠቀሙ ነበር። በጥናታቸው በገፉ ቁጥር ሱቃቸውን እየዘጉ ሰፊ ጊዜያቸውን በቤተ መጻህፍቱ ማሳለፉን ተያያዙት። ትጋታቸውን ያስተዋሉት የቤተ መጻህፍቱ ሀላፊዎችም ባሰኛቸው ጊዜ መጠቀም ይችሉ ዘንድ አንድ ልዩ ክፍልና የቤተ መጻህፍቱን ቁልፍ በማስረከብ ለሸይኹ ብቻ ሳይሆን ለሙስሊሙ ዐለም ባጠቃላይ ትልቅ ውለታን ጥለው አልፈዋል። ከዚህ በኋላ አልባኒይ ከሶላት ውጭ ከማለዳ እስከ ዒሻ በኋላ ቤተ መጻህፍቱን ቤታቸው አደረጉት። ጥናታቸውን አጠናክረው የቀጠሉት ሸይኹልአልባኒይ የኋላ ኋላ በሐዲሥ ጥናት መስክ ብቻ ከመቶ በላይ ኪታቦችን ለኡማው አበርክተዋል። በዘርፉ ከተሰማሩ ሌሎች ዐሊሞች ጋር ሲታዩ ሸይኹል አልባኒይ ጫፍ የደረሱ ነበሩ ማለት ይቻላል። እንዲያውም ዐሊሞች “የነኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላኒን፣ ኢብኑ ከሢርንና የሌሎችንም ሙሐዲሦች ዘመን እንደ አዲስ አመጣው” ሲሉ አወድሰዋቸዋል። የተውሒድና የሱናን ባንዲራ ሶሪያ ምድር ላይ ቀላል ለማይባል ጊዜ ያውለበለቡት ሸይኹል አልባኒይ ከተቀናቃኞቻቸው ጋር በዐቂዳ፣ በኢቲባዕ (ረሱልን ﷺ በመከተል)፣ በመዝሀብ ጭፍን ተከታይነትና በቢድዐ ዙሪያ በርካታ ውይይቶችን አድርገዋል። በሂደቱም በመዝሀብ ጭፍን ተከታዮችና በሱፊያ ሸይኾች ቀስቃሽነት ብዙ ፈተና ደርሶባቸዋል። በተመሳሳይ ጊዜ ደማስቆ ውስጥ ከሚገኙ ስመ ጥር ዓሊሞች በአቋማቸው እንዲገፉ ያላሰለሰ ማበረታቻ ከጎናቸው ነበር። ትግላቸውን አጠናክረው የዩኒቨርሲቲ አስተማሪዎች ጭምር የሚካፈሉበት ደርስ እንዲሁም ወደተለያዩ የሶሪያና የዮርዳኖስ ከተሞች እየተዘዋወሩ ወርሃዊ ደዕዋ ማድረግ ቀጠሉ። ኳታር፣ ግብጽ፣ ኩዌት፣ ዐረብ ኢማራት፣ አውስትራሊያ፣ እንግሊዝና ስፔን በተለያዩ ጊዜያት ለደዕዋ ከተጓዙባቸው ሃገራት ውስጥ ናቸው። ስራዎቻቸው ለህትመት ከበቁ ስማቸው በሰፊው ከታወቀ በኋላ በዝነኛው የመዲና ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ ሆነው ተመርጠው ለሶስት ዓመታት አገልግለዋል። ከዚህ በኋላ ሱቃቸውን ለአንድ ወንድማቸው በመተው ሙሉ ለሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ጥንታዊው የ“አዟሂሪያ” መክተባ ተመለሱ። ኢማሙል አልባኒይ ምንም እንኳ ከፖለቲካ የራቁ ቢሆኑም በተለያዩ ጊዜያት መንግስት በዐይነ ቁራኛ ይከታተላቸው ነበር። ሁለት ጊዜም ለእስራት ተዳርገዋል። በሁለተኛ እስራታቸው ከታላላቅ ዐሊሞች ጋር የተገናኙ ሲሆን በእስራት ላይ እያሉም የሙንዚሪን “ሙኽተሶሩ ሶሒሕ ሙስሊም ‘ተሕቂቅ' አድርገዋል። ለሐቅ ባላቸው ፅኑ አቋምና ለለውጥ ባላቸው የማይታጠፍ ተጋድሎ የሚታወቁት ሸይኹል አልባኒይ ውጫዊ የአመለካከት ወረራዎችን ብቻ ሳይሆን የኢስላምን ውበት ያደበዘዙ ውስጣዊ ወረራዎችንም በመዋጋት ፋና ወጊ ነበሩ። አልባኒይ ለተስፊያና ተርቢያ ማለትም ኢስላምን ከቢድዐ፣ ከሺርኪያት፣ ከደካማ ማስረጃዎችና ሰርጎ-ገብ አመለካከቶች ማፅዳት እንዲሁም ትውልድን ቁርኣንና ሶሒሕ ሱና ላይ በተመሰረተው ንፁሁ ኢስላም ላይ ኮትኩቶ የማውጣት አካሄድ ልዩ ትኩረት ይሰጡ ነበር። ከግማሽ ክፍለ-ዘመን በላይ የተጓዙበትን ይህን አካሄዳቸውን በርካቶች እንዲያጤኑበትና እንዲሄዱበት ያላሰለሰ ጥረት አድርገዋል። ለኡማው አንድነት እጅግ የሚጨነቁት አልባኒይ ለአንድነት የሚደርገው ጥረት ፍሬ ያፈራ ዘንድ ግን ከባዶ የ”አንድ እንሁን” ጩኸት ባለፈ የግድ ወደ ቁርኣንና ሱና መመለስ እንደሚያስፈልግ በፅኑ ያሳስባሉ። እዚህ ላይ በአንድ ወቅት ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡትን መልስ ብናነሳ አይከፋም። ጥያቄ፡- “ትክክለኛ ነገር ካልያዝን ብለን ከምንበታተን በስህተት ላይ ሆነን ብንሰባሰብ ይሻላል። መክንያቱም ሐቅ ሁሉ ትክክል አይደለምና። እንዲሁም ባጢል (ውድቅ ነገር) ሁሉም ስህተት አይደለምና!” አልባኒይ፡- “ይሄ ምናባዊና ቅዠታዊ ንግግር ነው። በስህተት ላይ ከሆንን መሰባሰባችን ምንድን ነው ፋይዳው? ከፊላችን በስህተት ላይ ከፊላችን ደግሞ በሐቅ ላይ ከሆንን ብንለያይ ምንድን ነው ጉዳቱ? አሸናፊና የላቀው ጌታችን እንዲህ ይላል:- {ከሐቅ በኋላ ጥመት እንጂ ምን አለ?} ሸይኹል አልባኒይ በጠንካራ የሰለፊያ አቋማቸው የተነሳ ብዙ ሰቃይና እንግልት ደርሶባቸዋል። ለኢስላም ሲባል ከአልባኒያ የተጀመረው ስደት ደማስቆን መጨረሻው አላደረገም። በተለያዩ ጫናዎች ምክንያት ከሶሪያ ወደ ዮርዳኖስ፣ ከዮርዳኖስ ዳግም ወደ ሶሪያ፣ ከዚያም ወደ ሊባኖስ፣ ከዚያም ወደ ዐረብ ኢማራት፣ በመጨረሻም ወደ ዮርዳኖስ ዐማን ተንከራተዋል።
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

👍 1
በሀይቅ ከተማ ቢላል መስጂድ የተደረገ አዲስ ሙሓደራ ስለ ሽርክ እና መውሊድ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሸይኽ አወል ኬሚሴ
إظهار الكل...
ሸይኽ_አወል_አልከሚሴ_ሺርክ_እና_መውሊድ.m4a46.51 MB
🔴 አሁን ቀጥታ ስርጭት 📚 رياض الصالحين ክፍል - 76 (22) باب فضل ضعفة المسلمين والفقراء رقم الحديث 257 🎙በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም ሼር በማድረግ ሌሎችንም ተጠቃሚ ያድርጉ የላይቩ ሊንክ t.me/SheikhMuhammedZainAdam?livestream
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.