cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Walia bookstore gallery

Books

إظهار المزيد
الهند91 712الإنكليزية99 938الكتب6 158
مشاركات الإعلانات
4 171
المشتركون
-224 ساعات
-217 أيام
-5630 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
🔥 3👍 1
፨ በአጠቃላይ መጽሃፉ ብዙ፣ ብዙ የሚብራሩ ጉዳዮችን ያቀፈ ነው። በደንብ ተጠንቶ ሂስ'ም ዳሰሳ'ም ሊቀርብበት የሚገባ ነው።
إظهار الكل...
Endale Geta Kebede: የእንዳለጌታ ሃዘንተኛ ብዕር ነቢል አዱኛ እንደ መጽሃፍ- ቅዱሷ ቤርሳቤህ(260) ታሪካቸው ያልተጻፈ፣ ወይም ተነክቶ የተተወ ሰዎች፣ ስለ ‹ያልተቀበልናቸው› ማህበረሰቦች፣ ‹ማዕቀብ› ስለተጣለባቸው ህዝቦች፣ ታሪካቸው ተድበስብሶ በስርዓት ፍትህ እና ፍርድ ላላገኙ ሰዎች፣ ከመጽሃፉ መታሰቢያ ጀምሮ የት እንደገቡና፣ ‹‹የት እንደወደቁ ያልታወቁ››(129) (በዓሉ ግርማ'ን ጨምሮ) ያልታወቁ ግለሰቦች፣ ለህዝብና ለሃገር የሚኾን ሥራ ሰርተው፤ ሥራቸውን በቅጡ የሚገነዘቡላቸው አጥተው በማዕቀብ ላሉ ‹እስረኞች›፣ ‹‹የሳሎኑ መብራት በርቶ የጨለመባቸው፣ በራቸው ተከፍቶ ዝግ የመሰለባቸው፣ ፍም ተንተርክኮ ብርድ ለሰፈነባቸው››(62)፣ ልክ እንደ አቶ ሥዩም ‹‹ለግፉዓንና ምንዱባን››(20) ተቆርቋሪ፣ ተከራካሪ፣ ዘብ ቋሚና 'አለሁ' ባይ የኾነው የዶክተር እንዳለጌታ ከበደ ብዕር በ16ኛ መጽሃፉ(አንዱ የአርትዖት ነው) በሐምሌ መጨረሻ 2016፤ ‹ሲጥል› በሚል ረዥም ልብወለድ መጥቶልናል። ፨ ከመጀመሪያው ‹ከጥቁር ሰማይ ስር› ጀምሮ እስካሁኑ ‹ሲጥል› መጽሃፎቹ በተገፉ፣ ትኩረት ባልተሰጣቸው እና ባልተቀበልናቸው ማህበረሰቦች ጓዳ እየገባ በተባ ብዕሩ አንባቢን በሃዘን እየለወሰ ወስዶ ከጥቁር ሰማይ ስር እንድናስተውል ይጥለናል። (ስለዚህ ጉዳይ በሌላ ጽሁፍ እንመለስበታለን) ፨ በ‹ዛጎል› የደብረ ሰምራ፣ በ‹ምሳሌ› የለገ ኦነሲሞስ ነዋሪ ያደረገን እንዳለጌታ፣ በሲጥል የ'ዐሊይ' መንደር ማህበረሰብ ያደርገናል። ቦለቄና ባቄላ ተመጋቢ፣ የቦለቄ ሾርባ እንጂ ሌላ አልፈልግም ባይ ያደርገናል። ያየናትን ኮረዳ "አንቺ የቦለቄ ሾርባ፣                     ተሰርተሽ ሹሩባ" ብለን እናዳንቃለን። መልከመልካም ጎረምሳ ያየች እንስትም "ቡልቅልቅ እንደ ቦለቄ ብቅልቅል እንደ ባቄላ ዐየን የወንድ ዛላ!" እንዲሉ ያደርጋል። ፨ ‹ሲጥል› ሃገራዊ ኹነቶችን እያነሳ፣ በ ‹ያልተቀበልናቸው› ላይ በስፋት የተዳሰሱትን ጉዳዮች እየመለሰ፣ ማህበረሰብን እየሄሰ፣ በሱራፌል አንደበት ‹‹እንደ ተረት ተሰርታ፣ ረጅም ተረት ተርታ፣ በጊዜ ብዛት ተረታም ትውልድ መፍጠር የቻለች ሃገር!››(90) እያለ ሃገራችን ለገባችበት ማጥ፣ ህዝቦቿ ለደረሱበት መከፋፈል እያዘነ፣ በገጸ-ባህሪያቶቹ በኩል ችግራችንን እየነቀሰ፣ መፍትሄ ያለውንም እየነገረ ሲተርክ "ኋላ እመለስበታለሁ" ብለን የምናስቀምጠው አይደለም። በለመድነው ግሩም አተራረክ፣ ቴአትራዊ መልክ ባለው ቃና ሳናስበው አንድ ብለን ሁለት መቶ ሰማንያ እንላለን። ፨ መጽሃፉ ውስጥ ከምናስተውላቸውና ደጋግመን ከምንሰማቸው ድምጾች አንዱ ‹መለየት› እና ‹መለያየት› ነው። - ሲጀምር <ሀ: ጎህ ሲቀድ>... ‹‹አንድ ቀን ትቶኝ ይሄዳል›› የሚል የመለየት ስጋት ባላት ቤርሳቤህ ነው። ሲጨርስ <ኖ: ስንብት> በመለያየት ነው። መጽሃፉ ውስጥ በአንድም ኾነ በሌላም ተደጋጋሚ መለያየት'ን እናያለን። ለምሳሌ፦ የምንተስኖት እናት በሞት መለየት፤ ከቃሏ፣ ከዕምነቷ (ተገዳም ቢኾን) ከሌላ ሰው ጋር በመተኛት (በመጸነስ) መለየት(58-70)፣ የቤርሳቤህ እናት በጫት ሱስ ምክንያት ባሏንና ሁለት ልጆቿን ጥላ መለየት፣ የቤርሳቤህ (የቀድሞ) ባል ለስድስት ወራት አግብቷት በአራተኛው ወር መለየት፣ በኢዩኤል አባት የኔታ እና በወንድማቸው መሪጌታ ‹‹የሚያድናቸው እና የሚታደጋቸውን በመምረጥ››(137) በአስተሳሰብ፣ ዕምነት መለያየት፣ ኢዩኤልም አባቱ የኔታ ‹‹ውጉዝ ከመ አርዮስ›› ብለው የረገሙትን(215) የአጎቱን መንገድ በመከተል ከወላጆቹ (በኑሮም፣ በአስተሳሰብም) መለየት፣ የሱራፌል እና የፍቅረኛው መለያየት (144)፣ ከባለቤቱ ጋር ፍቺ እንዳይፈጽም በ ቢ.አ.ን (ቢገድሉንም አንሞትላቸውም ንቅናቄ) ፓርቲ በመከልከሉ፤ በመጨረሻም ከሚስቱም፣ ከውሽማውም፣ ከፓርቲውም የተለያየው ፍቺ ናፋቂ የፖለቲካ አመራር (154)፣ በገዢው ፓርቲ (በልብወለዱ) ማስፈራሪያ ኋላ ‹‹ይቅርታ አድርጌላታለሁ›› ቢልም እሷ በሰራችው ስህተት ተለያይተው የነበሩት የአቶ ሥዩም ልጅ መኩሪያ እና ፍቅረኛው (158)፣ ኤች አይ ቪ ወላጆቿን ከሷ የለየባት የ'ዐሊይ' ከተማ የስምንተኛ ቢ ክፍል ተማሪ (210)፣ የምንተስኖት በራሱ እጅ ራሱን በማጥፋት መለየት (242)፣ የረዳቱ  ሚስት ትታው በመሄድ መለየት (247)፣ የመሪጌታ በድንገት በመሰወር መለየት (247)፣... በመለያየት ስጋት ጀምሮ በመለያየት የሚያልቅ - ልብን ሃዘን ውስጥ ነክሮ፣ እንደ ገጸባህሪያቶቹ ሁሉ አንባቢውን 'ዐሊይ'ን መልቀቅ ሳይፈልግ ራሱን መጨረሻ ገጽ ላይ እንዲያገኝ የሚያደርግ ነው። ፨ ሌላው አባትነት ሰፊ ገጽ የተሰጠው ጉዳይ ነው። አባትነትን አጽንዖት ሰጥቶ ያብራራል። ገጸባህሪያቶቹ ከአባታቸው ጋር ባላቸው ግንኙነት እየተነሳ ታሪኮቹን ያዳውራል። አቶ ሥዩም ‹‹እናትነት በደንብ አልተገለጸም›› (56) ቢሉም፤ ደራሲው ግን ስለአባትነት እንጂ ስለእናትነት ብዙ ተብሏል የሚል ይመስላል። ፨ ሱራፌል አባቱ ትቶት የሄደ እና በዚህ ያዘነ፣ የተጎዳ፣ ለእናቱ ልዩ ፍቅር ያለው ነው። በቴአትር ድርሰቱ ገጸባህሪያቶቹ እንደሚነግሩን በህጻንነታቸው አባታቸው ሲመታቸውና ሲቆጣቸው ‹‹ምነው በሞተ!›› ብለው የሚጸልዩ ነበሩ። በሱራፌል እናት በኩል ሰው የሌላቸውን፣ ሰው ያጡ ሰዎችን ያስታውሰናል። ያለ ‹አለሁ› ባይ የሚኖሩትን በማስታወስ ያስተክዘናል። ‹‹ሰው ራበኝ፤ ወንድም ራበኝ፤ የሚጠብቀኝ፣ መጎዳቴንና መጎሳቆሌን የሚያውቅ ወንድም ፈለግኩ።›› (86) ትላለች። ለራሷ ወርቅ እና ልብስ እየገዛች ጎረቤቶቿን ‹‹ወንድሜ ገዛልኝ! ወንድም መከታ!›› እያለች ‹‹ብቻዬን አይደለሁም!››ን ሰፈርተኛ እንዲያውቅላት ትሻለች። ልጇንም ‹‹ሰው አይራብህ! ወንድም እህት አትጣ!›› (87) ትለዋለች። ፨ በቤርሳቤህ አባት ንጉሡ፣ ያለእናት ምንም ሳይጎድልባቸው እንዴት እንዳሳደጋቸው አባትነትን በጥቂቱ ያሳየናል። ለአባቷ ህክምና ስትልም የደህንነቱን ሰው በኮንትራት ጋብቻ ታገባዋለች። በዚህም ህይወቷ ላይ አባቷ ያለውን አሻራ ታሳየናለች። ፨ በምንተስኖት 'አባት' ተመስገን ደግሞ አባትነት'ን ፍንትው አድርጎ ይገልጻል። አቶ ተመስገን እንደማይወልዱ እያወቁ ‹‹…ተመትቻለሁ፤ ድሮ ወታደር ቤት ሳለሁ የደረሰብኝ ጉዳት አለ፤ አጉል ቦታ ተጎድቻለሁ፤ ግን ለማንም አላወራሁት፤ እናትህም አታውቅ። ማስረገዝ አይኾንልኝም፤ አልወልድም ልጄ! ይህን አውቃለሁ። ሃኪም ነግሮኛል።›› (242) ብለው ግን ሚስታቸው አርግዛ ስትወልድ ‹‹ልጁም የእርስዎ ነው›› ብላ ‹‹የምንተስኖት አባት›› እያለቻቸው ምንም ሳይመስላቸው በንጹህ ፍቅር፣ በጥልቅ አባትነት 'ልጃቸውን' አሳደጉ። ‹‹ከማን ጋር ወስልተሽ? ከየት ይዘሽ መጣሽ?!›› አላሏትም - ምክንያቱም ‹‹ምስጢሬ ታወቀብኝ›› ብላ 'ልጄን' ይዛ እንዳትጠፋብኝ ብለው ፈርተው። ከድህነት ጋር፣ ከማጣት ጋር፣ ከችግር ጋር፤ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እስኪኾን አቅፈውት እየተኙ፣ ትልቅ ልጅም ኾኖ እጁን ይዘው አስፓልት እያሻገሩ አሳደጉት። አባትነት ረቂቅ ነው ተዓምር የወጠነው የዘጠኝ ወር አይደለም የዘላለም ምጥ ነው። አባ በቃላቴ ድካምህን ላክም ሽበት እስኪውጠው የጸጉርህን ክርክም ገንዘብ አጣህ እንጂ ደሃ አልነበርክም! ውሽንፍሩ አልፏል... በእልፍኝ በሳሎንህ፣ ብዙ እንባ ጎርፏል... ከተከታይ አይንህ።   መብረቁም ስቶናል ትከሻህን ታክኮ   ካንተ ጋር መደህየት ጸጋ ነበር እኮ! የሚለውን የፈይሰል አሚን ግጥም የሚገልጽ ታሪክ፤ ደራሲው በአቶ ተመስገን ህይወት አሳይቶናል።
إظهار الكل...
👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
🥰 7👏 2
ስመጥሩው ፀሀፌ ተውኔት ውድነህ ክፍሌ: "ሲጥል" የተሰኘው መጽሐፍ የደራሲ እንዳለጌታ ከበደ /ዶ/ር/ ስንተኛ የድርሰት ልጁ ነው?  ብሎ መጠየቁ ይታወቃል:: "ፈጥነው ትክክለኛ መልስ ለመለሱ ስድስት የፌስቡክ ወዳጆቼ በእንዳለጌታ አስፈርሜ መጽሐፉን ከእሱ እጅ እንዲረከቡ አደርጋለሁ፤ ገዝቼ እሸልማለሁ።" ማለቱም አይዘነጋም:: ሆኖም በብርሀን ፍጥነት ምላሽ ከሰጡ አንባብያን መካከል 15ቱ ትክክል ሆኑ:: እናም 15ኛ መጽሐፉ ነው ያሉ ተሸለሙ:: ውድነህ ይህ ከሐምሌ 27 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ገበያ ላይ የዋለው የእንዳለጌታ " ሲ ጥ ል"ን መፅሐፍ ለ 15 አንባብያን ለመሸለም ያነሳሳው ምክንያት በፌስቡኩ ሲገልፅ: "ያለመታከት ለሙያ ለምታደርገው በጎ አሻራ እጅ ነስተናል!! እግረመንገዳችንንም እንዳለን እናመስግነው!!!! ምስጋናውን እኔ ልጀምረው "በዓሉ ግርማ - ቤርሙዳ" ቴአትርን እጽፈው ዘንዳ ጉልበት ከሆኑኝ ውስጥ አንዱ የአንተ ስራ የሆነው "በዓሉ ግርማ ህይወቱና ስራዎቹ" የተሰኘው መጽሐፍህ ነውና እንድዬ ምስጋናዬ የላቀ ነው። በቴአትሩ ዙሪያ ለነበረህ በጎ ሀሳብም ዝቅ ብያለሁ።" ብሏል:: አያይዞም " እነሆ አስራ አምስቱ ተሸላሚዎች የደራሲ እንዳለጌታ ከበደ 'ሲጥል' የተሰኘውን መጽሐፍ እንዲረከቡ ከበላይ አካል ትዕዛዝ ወርዷል¡ ወዳጄ እንዳለጌታም የተከበረ ፊርማውን አሳርፎበት አራት ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት ሽልማታችሁን ቆጥሮ አስረክቧል።" በማለት ስማቸውን እንዲህ ዘርዝሮታል:: * ህሊና በለጠ * ኤርሚያስ በጋሻው * ፍስሃ አንዳርጌ * አብርሃ ጣሰው * Kilo Bite * Ala Muler * ፋሲል አንዳርጌ * ሀብቴ Ab Vo * ሰለሞን ያረጋል * ኪዳኔ ደበበ * ማርታ ነጋሽ * ቲና ተስፋልደት * ቤዛ ኃይለየሱስ * ዮናስ ኃ/ ማርቆስ * ማርታ አዱኛ። የደራሲ እንዳለጌታ ከበደ 'ሲጥል' መጽሐፍ በየመደብሩ ይገኛል። ተሸላሚዎች ደግሞ አራት ኪሎ ኢክላሥ ሕንጻ በሚገኘው  ዋልያ መጻሕፍት መደብር ብቅ ብላችሁ 'ሲጥልን' መረከብ ትችላላችሁ። መልካም ንባብ።" --- አሳታሚው ዋልያ መፃሕፍት እንዲህ ያለውን ንባብን ለማበረታት የሚደረገውን እንቅስቃሴ እጅጉን ይደግፋል:: አሳታሚና አከፋፋይ በሆነባቸው ሌሎች መፃሕፍት ላይም ከአስር መፃሕፍት በላይ ለሚገዛ ሽያጩ ላይ ቅናሽ ያደርጋል::
إظهار الكل...
👍 9 6👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
የደራሲ እንዳለጌታ ከበደ አዲስ ልብወልድ መፅሐፍን "ሲጥል" ከታች በተጠቀሱት መጻሕፍት ቤቶች ማግኘት ትችላላቹሁ። #4ኪሎ ለሚቀርባቹሁ ዋልያ መፅሐፍ እነሆ መፅሐፍ ጃፈር መፅሐፍ ዳንያል መፅሐፍ ሀሁ መፅሐፍ አበራ መፅሐፍ ቡክ ሳይት ሽታሁን መፅሐፍ ፀጋዬ  መፅሐፍ #ፒ ያሳ ለሚቀርባቹሁ ሸምሱ መፅሐፍ #ካሳንቺስ ለሚቀርባቹሁ ጦቢያ መፅሐፍ #ሜክሲኮ ለሚቀርባቹሁ ጃፈር መፅሐፍ ኮሜርስ መፅሐፍ አይናለም መፅሐፍ ሀሁ መፅሐፍ ጃፈር መፅሐፍ ቁጥር 2 /ደብረወርቅ ህንፃ/ #ሳርቤት ለሚቀርባቹሁ ፍሬው መፅሐፍ #አውቶብስ ተራ ለሚቀርባችሁ አስቻለው መፅሐፍ #መርካቶ ለሚቀርባችሁ አሞዛ መፅሐፍት ሶሎሞን መፅሐፍት #ሳሪስ ለሚቀርባችሁ ጃፈር መፅሐፍ #መገናኛ ለሚቀርባቹሁ ኤደን መፅሐፍ #22 ለሚቀርባችሁ     አብዱ መፅሐፍ #ጉርድ ሾላ  ለሚቀርባቹሁ መዝገቡ መፅሐፍ #በተጨማሪም በተለያዩ አዙዋሪዎች እጅ ላይ ያገኙታል
إظهار الكل...
👍 18👏 1
የደራሲ እንዳለጌታ ከበደ አዲስ ልብወልድ መፅሐፍን "ሲጥል" ከታች በተጠቀሱት መጻሕፍት ቤቶች ማግኘት ትችላላቹሁ። #4ኪሎ ለሚቀርባቹሁ ዋልያ መፅሐፍ እነሆ መፅሐፍ ጃፈር መፅሐፍ ዳንያል መፅሐፍ ሀሁ መፅሐፍ አበራ መፅሐፍ ቡክ ሳይት ሽታሁን መፅሐፍ ፀጋዬ መፅሐፍ #ፒ ያሳ ለሚቀርባቹሁ ሸምሱ መፅሐፍ #ካሳንቺስ ለሚቀርባቹሁ ጦቢያ መፅሐፍ #ሜክሲኮ ለሚቀርባቹሁ ጃፈር መፅሐፍ ኮሜርስ መፅሐፍ አይናለም መፅሐፍ ሀሁ መፅሐፍ ጃፈር መፅሐፍ ቁጥር 2 /ደብረወርቅ ህንፃ/ #ሳርቤት ለሚቀርባቹሁ ፍሬው መፅሐፍ #አውቶብስ ተራ ለሚቀርባችሁ አስቻለው መፅሐፍ #መርካቶ ለሚቀርባችሁ አሞዛ መፅሐፍት ሶሎሞን መፅሐፍት #ሳሪስ ለሚቀርባችሁ ጃፈር መፅሐፍ #መገናኛ ለሚቀርባቹሁ ኤደን መፅሐፍ #22 ለሚቀርባችሁ አብዱ መፅሐፍ #ጉርድ ሾላ ለሚቀርባቹሁ መዝገቡ መፅሐፍ #በተጨማሪም በተለያዩ አዙዋሪዎች እጅ ላይ ያገኙታል
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
#ሁላችሁም_ተጋብዛችኋል።  (በነጻ) ----- ልዩ መርሐግብር:-  ከደራስያን ጋር የመጨዋወት እና  መጽሐፍ የማስፈረም ልዩ ሥነ-ስርዓት:: የዕለቱ የክብር እንግዳ:- ደራሲ አለማየሁ ደመቅ የዕለቱ ፕሮግራም አወያይ :- ደራሲ እና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ የተመረጠው መጽሐፍ: ዮቶር የመርሐግብሩ አሰናጅ:- ዋልያ መጻሕፍት:: ቦታ:- አራት ኪሎ: ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ:  ኢክላስ ህንጻ ዋልያ መጻሕፍት:: ቀን:- ቅዳሜ: ሐምሌ 27 2016 ዓ. ም : ምሽት ከ10:00 እስከ 12:30 ድረስ:: ማስታወሻ:: 1) እንዲህ ዓይነቱ ፕሮግራም ቀጣይነት   ያለው ነው:: 2) ከዚህ ቀደም የተደረጉ መሰል ፕሮግራሞችን ለመከታተል በዋልያ ቡክ ስቶር ቻናል ያገኙናል። ( https://m.youtube.com/channel/UCT2s8ZltG5kIS6Q1n7NGGxw
إظهار الكل...
👍 5 4
Photo unavailableShow in Telegram
👏 7
Photo unavailableShow in Telegram
20👏 5👍 2
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.