cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት Ethiopian Statistics Service(ESS)

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
5 898
المشتركون
+4524 ساعات
+3037 أيام
+1 60030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ለሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ የቴክኒክ ድጋፍ ተደረገ *********ጷጉሜ 5/2016ዓ.ም ፣አዲስ አበባ******** የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት እና የዓለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት (FAO) ለሁለተኛ ጊዜ በ2017ዓ.ም ለሚካሄደው የግብርና ቆጠራ የቴክኒክና ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ የስምምነቱ ዓላማ በ2017 ዓ.ም የምናካሂደው የግብርና ቆጠራ በመስክ ስራና መረጃ ትንተና ወቅት የሚያስፈልገውን የዘርፉ ዓለም አቀፍ ቴክኒካል ድጋፍ ለማግኘት የተደረገ ስምምነት እንደሆነ ገልጸው ድርጅቱ በዚህ ታሪካዊ ጊዜ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል። ኢትዮጵያ ድርጅታችን (FAO) ከመሰረቱት ቀደምት ሀገራት አንዷ መሆኗን የገለጹት በዓለም አቀፍ የምግብና ግብርና ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ሚስ ፋራይ ዚሙድዚ ዛሬ የተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም ለምታካሂደው ሁለተኛ ዙር የግብርና ቆጠራ የሚያስፈልገው የቴክኖሎጂ፣ የሌሎች ሀገሮች ልምድ ልውውጥና የሰው ሀይል አቅም ግንባታን ማድረግ የሚያስችል ስምምነት መሆኑን በማስረዳት ተቋማቸው ቀጣይ ለሚካሄዱ ተግባራትም ድጋፋን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
إظهار الكل...
👍 79 17
በቴክኖሎጂው ዘርፍ ልዩ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው በጎ ፈቃደኛ ታዳጊዎች ለተቋሙ ሙያዊ እገዛ አደረጉ *********ጷጉሜ 1/2016ዓ.ም********** በቴክኖሎጂው ዘርፍ ልዩ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው በቁጥር 234 የሚሆኑ ሰመር ካምፕ ተሳታፊ ታዳጊዎች የኢትዮጵያ ስታቲስቲከስ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም ለሚያካሂደው የግብርና ቆጠራ የሚውሉ ታብሌቶችን የአፕሊኬሽን ፕሮቪዥኒንግ (application provisioning) እና ኢንስፔክሽን (inspection) በማድረግ ለተፈለገው አላማ እንዲውል የሚያስችል ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉ ይገኛሉ።
إظهار الكل...
👍 29 14
ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት የመሰክ ስራ ስምሪት ተሰጠ
إظهار الكل...
👍 21 7👏 1
ብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት የመሰክ ስራ ስምሪት ተሰጠ ******* ቢሾፍቱ 30/12/2016ዓ.ም******* የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት የብሔራዊ የተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት የመረጃ ሰብሳቢዎችና ተቆጣጣሪዎች ስልጠና ተጠናቆ የመስክ ስራ ስምሪት ተሰጠ፡፡ በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጲያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ ባደረጉት ንግግር ከተቀናጀ የቤተሰብ ጥናት የሚገኙ መረጃዎች በሀገራችን መንግስት በድህነት ውስጥ ያሉ ዜጎች ከድህነት ለማውጣት ለሚያቅዳቸው እቅዶች፣ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ለመቅረጽ እና የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ውስጥ ትክክለኛ ውሳኔ ለመስጠት ያላቸው ጠቀሜታ የላቀ መሆኑን በመረዳት በስልጠናው ጊዜ ያሳያችሁትን ጥሩ ስነ-ምግባር እና ትጋት በመስክ መረጃ የመሰብሰብ ስራ ላይም በመድገም ሀገራችሁ የጣለችባችሁን ታላቅ ኃላፊነት እንድትወጡ ሲሉ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ስምሪት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በበኩላቸው ተቋሙ ይህንን ያህል ወጣት ወደ ስራ ማስገባት በመቻሉ በራሱ ስራ አጥነት ከመቀነስ አንፃር ትልቅ ፋይዳ ያለው ከመሆኑም በላይ ለዚህ አይነት ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት መታጨት እድለኛነት መሆኑን አውቃችሁ ኃላፊነታችሁን በአግባቡ እንድትወጡ ሲሉ መልእክታቸውን አስተላለፈዋል። በመጨረሻም የእለቱ የክብር እንግዳ የሆኑት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ወ/ሮ ጥሩማር አባተ ምንም ባልተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ የምትሰሩ ቢሆንም እንደ ብሔራዊ ግዳጅ ወስዳችሁ ሀገር የጣለባችሁን አደራ በአግባቡ እንድትወጡ በማለት የስራ ስምሪቱን በይፋ አስጀምረዋል። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተዓማኒ የመረጃ ምንጭዎ ! Facebook:- https://www.facebook.com/essethiopia Telegram:- https://t.me/ess_statistics
إظهار الكل...
👍 13 3😁 3
ወጣቶቹ ለተቋሙ ሙያዊ ድጋፍ አደረጉ የሀገራችን የኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው የዘርፉ የነገ ተስፋዎች እና የሰመር ኮርስ ተሳታፊ ወጣቶች የኢትዮጵያ ስታቲስቲከስ አገልግሎት በ2017 ዓ.ም ለሚያካሂደው የግብርና ቆጠራ የሚውሉ ታብሌቶችን የአፕሊኬሽን ፕሮቪዥኒንግ (application provisioning) እና ኢንስፔክሽን (inspection) በማድረግ ድጋፍ አደረጉ። ወጣቶቹ ድጋፍ እየሰጡ የሚገኙት በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ሲሆን በሚቀጥሉት ቀናትም አርባ ሺ ታብሌቶችን የአፕሊኬሽን ፕሮቪዥኒንግ (application provisioning) እና ኢንስፔክሽን (inspection) ተግባራትን ያከናውናሉ። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተዓማኒ የመረጃ ምንጭዎ ! Facebook:- https://www.facebook.com/essethiopia Telegram:- https://t.me/ess_statistics
إظهار الكل...
👍 27 11
የግብርና ቆጠራ ሶስተኛ ዙር ስልጠና ሂደት ላይ ውይይት ተደረገ ******ነሐሴ 28/2016ዓ.ም******* የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት 2017ዓ.ም ለሚካሄደው የግብርና ቆጠራ ሶስተኛ ዙር ለመስክ መረጃ ሰብሳቢና ተቆጣጣሪዎች እየተሰጠ የሚገኘው የስልጠና ሂደት ላይ ውይይት ተደረገ። በውይይት መድረኩ ከነሐሴ 17/2016ዓ.ም በ45 ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከላት እየተሰጠ የሚገኘውን የስልጠና ሂደት በአስተባባሪዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን እስከአሁን ያለው የስልጠና ሂደት ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ለመረዳት ተችሏል። በውይይት መድረኩ ተገኝተው ቀጣይ አቅጣጫ የሰጡት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ እስከ አሁን የተካሄደበት ሂደት የተሻለ የሆነው በጋራ መስራት በመቻላችን ነው ሲሉ ገልፀው በቀጣይም ለቆጠራው ስኬት በእያንዳንዱ ሂደት የተሟላ ተግባቦት በመፍጠር ብዙ ሆነን እንደ አንድ መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ አቅጣጫ በመስጠት ውይይት ተጠናቋል። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ተዓማኒ የመረጃ ምንጭዎ!
إظهار الكل...
👏 27👍 16 11👎 8🥰 2
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል ጉብኝት ተደረገ ******ነሐሴ 24/2016ዓ.ም****** የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል በመገኘት የግብርና ቆጠራ መረጃ ሰብሳቢ ሰልጣኞችን ጎበኙ። ዋና ዳይሬክተሩ በዩኒቨርስቲው በመገኘት ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሀላፊ ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ሰልጣኞች በመጎብኘት በዩኒቨርስቲው ካፍቴሪያ ተገኝተው ከሰልጣኞች ጋር እራት ተመግበዋል ።
إظهار الكل...
👍 29 11
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል ጉብኝት ተደረገ ******ነሐሴ 24/2016ዓ.ም****** የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር በከር ሻሌ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል በመገኘት የግብርና ቆጠራ መረጃ ሰብሳቢ ሰልጣኞችን ጎበኙ። ዋና ዳይሬክተሩ በዩኒቨርስቲው በመገኘት ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሀላፊ ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ሰልጣኞች በመጎብኘት በዩኒቨርስቲው ካፍቴሪያ ተገኝተው ከሰልጣኞች ጋር እራት ተመግበዋል ።
إظهار الكل...
أرشيف المشاركات
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.