📖
መጽሐፍ ቅዱስ ይናገር 📖
23ኛ ትምህርት
✒
የሚከተሉትን ጥቅሶች በቃልዎ ያጥኑ
1. ሰው ኃጢአቱ ይቅር እንዲባልለት ምን ሊያደርግ ያስፈልገዋል?
መልስ :- ንሰሐ መግባት፡፡
«እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም›› (ሐዋ.3፡19።)
2. ሰው ኃጢአቱን ከተናዘዘ በኋላ ምን ማድረግ ያስፈልገዋል?
መልስ ፡—ኃጢአትን መተው፡፡
«ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።›› ምሳሌ 28፡13።
3. ኃጢአታችንን ብንናዘዝ እግዚአብሔር ምን ያደርግልናል?
መልስ ፡—ይቅር ይለናል፡፡
«በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው፡፡›› (1ኛ ዮሐ. 1፡9።)
4. መንግሥተ ሰማይ ለመግባት ምን ያስፈልጋል?
መልስ ፡- ከክፉ መንገድ መመለስ።
«እንዲህም አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ካልተመለሳችሁ እንደ ሕፃናትም ካልሆናችሁ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም›› (ማቴ. 18:3።)
5. የሱስ ይህንን መለወጥ እንደምን አድርጎ ይገልጸዋል?
መልስ ፡—እንደገና በመወለድ፡፡
«ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው፡፡ ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ። ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል፥ ድምፁንም ትሰማለህ፥ ነገር ግን ከወዴት እንደ መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም፤ ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው።» (ዮሐ. 3፡ 5-8)
6. ሰው እንደገና መወለዱን በምን ያሳያል?
መልስ ፡—ኃጢአቱን በማሸነፍ እና በመተው።
ሀ. ‹ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።(1ዮሐ 5፡4።)
ለ. «ስለዚህ የዲያቢሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም፥ ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔርም ተወልዶአልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም።» (ዮሐ 3፡9።)
7. ንሰሐ ከገባን በኋላ ቀጥሎ ያለው እርምጃ ምንድነው?
መልስ ፡- መጠመቅ።
‹‹ጴጥሮስም፦ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።» ሐዋ. 2፡38።
8. ከጥምቀት በኋላ እንደምን ያለ ኑሮ ልንኖር ይገባል?
መልስ ፡- በአዲስ ሕይወት ልንኖር ይገባል።
ሀ. ‹‹ወይስ ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ የተጠመቅን ሁላችን ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ እንደ ተጠመቅን አታውቁምን?
ለ. እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን።›› (ሮሜ 6፡3፣4።)
9. ጳውሎስ እንደምን ኖረ?
መልስ ፡- በእግዚአብሔር ልጅ አምኖ ኖረ።
‹ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።›› ገላትያ 2፡20፡፡
10. የሥጋ ምኞትን ሁሉ ምን ልናደርግ ይገባል?
መልስ ፡—ልንተው ይገባል፡፡
«እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ፥ እነዚህም ዝሙትና ርኵሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው። በእነዚህም ጠንቅ የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ይመጣል። እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ፡፡ አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቍጣንና ንዴትን ክፋትንም፥ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ። እርስ በርሳችሁ ውሸት አትነጋገሩ፥ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥ የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል።›› (ቆላ. 3፡5-10)
11. ስንት ጊዜ ልንጸልይ ይገባናል?
መልስ ፡—ሁልጊዜ።
ሀ. ‹‹ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥» ሉቃ. 18፡1።
ለ. ‹‹ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።›› 1ተሰ.5፡17።
ሐ. «በማታና በጥዋት በቀትርም እናገራለሁ እጮኽማለሁ፥ ቃሌንም ይሰማኛል።›› መዝ. 55፡17።
12. ከጸሎት ጋር ምን ሊኖረን ይገባል?
መልስ ፡—እምነት፡፡
«ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ የሚጠራጠር ሰው በነፋስ የተገፋና የተነቃነቀ የባሕርን ማዕበል ይመስላልና። ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው፡፡›› (ያዕ. 1:6-7)
13. የሱስ በምን ልንኖር ይገባል አለ?
መልስ ፡ በእግዚአብሔር ቃል።
«እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው›› (ማቴ 4:4።)
14. ጳውሎስ ጢሞቴዎስን ምን ብሎ አስተማረው?
መልስ ፡—የእግዚአብሔርን ቃል ኢንዲያጠና አስተማረው፡፡
‹‹የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ፡፡» 2ጢሞ. 2:15።
15. የእግዚአብሔርን ቃል ከማጥናት ሌላ ምን ያስፈልጋል?
መልስ ፡- ቃሉን አድራጊ መሆን።
«ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል። ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ የሚጸናበት፥ ሥራንም የሚሠራ እንጂ ሰምቶ የሚረሳ ያልሆነው፥ በሥራው የተባረከ ይሆናል። ያዕ. 1፡22-25።
➡ 24ኛ ትምህርት ይቀጥላል...
@MesayD ™