cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

TUBA ISLAMIC ASSOCIATION

(عن ابي هريرة رضي الله عنه،قال قال رسولﷺ :- "بدأ الاسلام غريبا وسيعود كما بدأ غريبا فطوبى للغرباء.")

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
278
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
-830 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

ጁምዐ.. የዱዐው ሰዓት ሳያልፍብን አንድ ግዜ ሀሳባችንን ሰብስበን ዱዐ እናድርግ። የሁላችንንም ዱዐ አላህዬ ይቀበለን።
إظهار الكل...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
إظهار الكل...
ስሜ ሑርያ ይባላል። የ60 ዓመት የዕድሜ ባለ ጸጋ ነኝ።ሥራ የለኝም። ትምህርቴንም አልጨረስኩም። ቆንጆ አይደለሁም። ከዉበት መዐድ ተቆርሶ የተሰጠኝ በጣሙን ጥቂት ነው። ዕድሜዬ 30 ዓመት እስኪያልፈዉ ድረስ፡ ማንም ለጋብቻ አልጠየቀኝም። አንድ ቀን በድንገት የሰፈራችን የትዳር አገናኝ አሮጊት አናገረችኝ። ለትዳር የሚፈልግሽ ሰዉ አለ።የ33 ዓመት ወጣት ነዉ። ከዚህ በፊት አግብቶ አያዉቅም። ከአባቱ ጋር የግል ኩባንያቸዉ ዉስጥ ነው የሚሰራዉ ብላ ፎቶዉን አሳየችኝ።ሃብታም ናቸዉ። ፎቶዉን አይቼ ደነገጥኩ ።ማሻ አላህ፡ በጣም ቆንጆ ነዉ።ግን እራሴን መጠየቅ ጀመርኩ። ለምን መረጠኝ? ከሁሉም በሁሉም ነገር የበታች ነኝ። ከትምህርት ትምህርት የለምኝ። ከዉበትም ነፃ ነኝ፡ እያልኩ ሳሰላስል፡ የትዳር አገናኟ፡ አንድ ችግር ግን አለበት ብላ፡ ከነበርኩበት አነቃችኝ። ከአምስት ዓመት በፊት የማየት አቅሙን  በአደጋ ምክንያት አጥቷል። በተለያየ ግዜያት የቀዶ ህክምና ተደርጎለት አልተሳካም ስትለኝ።ወይ እዳሌ ብዬ ማማረሬን ቀጠልኩ። የትዳር አገናኟ አስቢበት ብላ ጥላኝ ሄደች። ቤተሰቦቼን አማከርኩ። ሁሉም ዝምታን መረጡ። ሴት አያቴ ግን አላህ በዚህ ማየት በተሳነዉ ሰዉ ምክንያት በደስታ ዕንባ ሊያጥለቀልቅሽ አስቦ ይሆናል ፡ እስቲ አግኚዉና አናግሪዉ፡ ከዛ በኋላ ወስኚ አለችኝ። አገኘሁት። ተነጋገርን። ተጫዋች ነው። አንደበተ ርቱዕ። በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ልቤን ተቆጣጠረዉ።በሁለት ወራት ዉስጥ ትዳር መሰረትን። በዕዉነቱ፡ መጀመርያ በብዙ ነገር ምክንያት ሰግቼ ነበረ። አንደኛዉ እራሱ ስለራሱ የዓን ብርሃኑን ከማጣቱ በፊት የነገረኝ ሁሉ በጣም አሳስቦኝ ነበር። አላፊነት ወዉሰድ እንደማይወድ፡ ምሽቱን እንዴት እንደሚያሳልፍ እንደነበረ፡ ከቆነጃጅት ጋር ስለነበረዉ ተሞኩሮ ሲነግረኝ በጣም ሰጋሁ ። ሁለተኛው የስጋት ምንጬ፡ ከሰዉ እገዛ ዉጭ ምንም ማከናወን እንደማይችልና ሸክም እንደሚሆንብኝ ሲነግረኝ ነዉ ፍርሃት ያደረብኝ። ትዳር ዓለም ዉስጥ ስንገባ ያልጠበኩትን አየሁ። እገዛ አይሻም ሁሉንም ነገር እራሱ ነው የሚፈጽመው። ይህም ብቻ ሳይሆን ሁሌም ያግዘኛል። አብረን እናበስላለን፡ አብረን እናጥባለን። ሱቅ እንኳን እንድሄድ አይፈልግም። እንዳልደክምበት።በጣም ሩህሩህ አዛኝ ባል ነው። በፍቅሩ አሳበደኝ። በአስር ዓመታት ዉስጥ 3 ልጆች ወለድን። አንድም ቀን የባልና የአባትነት ድርሻዉን ሳያጓድል አመታት እንደ ደቂቃዎች አለፉ። አንድ ነገር ብቻ ይረብሸኝ ነበር። ዓይኑን በተመለከተ ተስፋ አልቆረጠም። ሐኪም ቤት ይመላለሳል።የዓይን ብርሃኑ ከተመለሰለት ወደ ቀድሞው ባህሬዉ ሊመለስ ይችላል ።ሊጠላኝ ይችላል። ሲያየኝ እደብረዉ ይሆናል እያልኩ። በየግዜው ይሞክራል ግን ዉጤት የለም። የአሁን የቀዶ ህክምና ተሳክቶለት ማየት እንደሚችል ዶክተሩ መርዶዉን አብስሮኛል። ሶስቱን ልጆች ይዤ የተኛበት ክፍል ገባን።ልጆቹ አጠገቡ ቆመዋል። ራቅ ብዬ በሩ አጠገብ ተቀመጥኩ። ፋሻዉ ተነሳለት። ያያል። ማመን አብቅቶታል ። ልጆቹን እያገላበጠ ሳመ። እንዲሁም አባቱንና እናቱን። ክፍሉን መቃኘት ጀመረ። በዓይኑ ፈለገኝ። አየኝ። ጠራኝ። ነይ እንጂ ዉቧ ሙሽራዬ ብሎ ጠራኝ። ነይ እንጂ ቀረብ በይ በደንብ ልይሽ። ከገመትኩት በላይ በጣሙን ቆንጆ ነሽ አለ። እንባዬን መቆጣጠር ተሳነኝ። ስጋቴ ጨመረ።ሄድኩኝ። እጄን እፍፍ አርጎ ሳመኝ። ሰይጣን ስራውን ቀጠለ። ሰዉ ፊት ስለሆነ ነዉ። ዉሸቱን ነዉ። እያልኩኝ እራሴን በራሴ ማናገር የዕለት ተዕለት ስራዬ ሆነ ። ግና ለኔ ያለው ፍቅር እየጨመረ ሄደ አንዲት ቆንጆ ሴት ቀና ብሎ አይቶ አያዉቅም ልቡ ሁሌም ከኔ ጋር ነዉ ። አባትና እና እናቴ አረፉ አባትም እናትም ሆነኝ። ሐዘን ደጃፌ እንዳይደርስ አደረገ። እነሆ 60ኛዉን እድሜዬን ይዣለሁ። አያቴ እንዳለችዉ በደስታ ዕንባ ርሻለሁ። በራሕመቱ። ለናንተም የማይጠግባቹህን የማትጠግቡትን ይስጣቹህ። አሚን በሉ።
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
. እከሌ የእከሌ ልጅ ባንቱ ላይ ሰለዋት አውርዷል ተብሎ ስምህ የዓለማቱ ነቢይ ﷺ ፊት መነሳቱ ምነኛ ያማረ ነው…. اللهم صلِ و سلم  على سيدنا محمد ﷺ 💚 መልካም ጁማዓ 🥰 በዱአችሁ 🥰 @tubajemea
إظهار الكل...
🥰 2
Photo unavailableShow in Telegram
🌼🌼ከጁሙዓ ሱናዎች🌼🌼 ፨ሱረቱል ካህፍን መቅራት ፨ገላን መታጠብ ፨ጥሩ ልብስ መልበስ ፨ሽቶ መቀባት (ለወንዶች) ፨በጊዜ ወደ መስጅድ መሄድ ፨በነብዩ ላይ ሰለዋት ማውረድ اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ.❤️ https://t.me/tubajemea
إظهار الكل...
‏"وقل للنفسِ إن فقدَت رجاها ‏وصارَ اليأسُ يوهِنُها قواها ‏ثقي باللهِ، كم خافت نفوسٌ ‏مِن الدنيا وخالقُها كفاها ‏ستغمُرُنا السحائِب عن قريبٍ ‏بِبُشرى لا يُحاطُ بمنتهاها ‏فعاقبةُ الهمومِ إلى زوالٍ ‏عن الدنيا، إذا بلَغت مداها."
إظهار الكل...
የብዙዎች ልብ አንደበት ኑሮት ቢናገር «ደክሞኛል» ነበር የሚለው!! ቻናል:- t.me/hafugraphics
إظهار الكل...
#48 ከእሳት ለመጠበቅ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿اتَّقُوا النّارَ ولو بشِقَّةِ تَمْرَةٍ، فمَن لَمْ يَجِدْ شِقَّةَ تَمْرَةٍ فَبِكَلِمَةٍ طَيِّبَةٍ﴾ “በግማሽ ቴምርም ቢሆን የጀሃነምን እሳት ተከላከሉ። ግማሽ ቴምር ማታገኙ እንኳ ቢሆን መልካም በመናገር ተከላከሉ።” 📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 3595 ---------------- ከጃቢር ቢን አብደላህ (رضيﷲ عنه) ተይዞ:  ረሱል (ﷺ) ከመሞታቸው ሶስት ቀን በፊት እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፦  ﴿لا يموتَنَّ أحَدٌ إلّا وهو يُحسِنُ الظَّنَّ باللهِ عزَّ وجلَّ﴾ “አንዳችሁ በአላህ ላይ መልካም ጥርጣሬ አሳድሮ ቢሆን እንጂ እንዳይሞት።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 2877 @tubajemea
إظهار الكل...
በጌታዬ ይሁንብኝ ... መጀመሪያው አሏህን የማያስደስት የሆነ እያንዳንዱ ግንኙነት መጨረሻው አንተን ሊያስደስትህ አይችልም!!
إظهار الكل...
አንድ ቀን አመሻሹ ላይ እናት የአብራኳን ክፋዮች በማስጠናት ላይ ተጠምዳለች። አጠገባቸው ተቀምጣ የተማሩትን ታስረዳለች። ታላላቆቿን ከማስጠናት እንዳታዘናጋት ለትንሽዬዋ ልጇ የስዕል ደብተር ሰጥታታለች። በግቢያቸው ውስጥ ከዋናው መኖርያ ቤት ወጣ ብሎ ለብቻ ተገልሎ በተሰራው ክፍል ውስጥ አብረዋቸው ለሚኖሩት ለባለቤቷ አባት እራት እንዳልሰጠቻቸው በድንገት ታወሳት። ፍጥን ብላ ተነሳች። ምግብ አዘጋጅታ በሳሀን አድርጋ ወሰደችላቸው። ሌላ የሚፈልጉት ነገር ካለ እንዲጠሯት ነግራ ወደልጆቿ ተመለሰች። ህፃኗ በተሰጣት ደብተር ላይ ባማረ ውብ ገፅታ የተንቆጠቆጠ ግቢ ከነቤት ዲዛይኑ በእርሳስ መሳሏን ስትመለከት "ውዴ ምን እየሳልሽ ነው?" በማለት ጠየቀች። ጥርስ በሌለበት ምድረበዳ ምላሷ ጉበት የሚመስለው "ቱክ ቱክ" እያለ ቃል ለማምረት በሚባትል አንደበቷ "አድጌ ለወግ ማዕረግ ስበቃ የምኖርበትን ቤት ዲዛይን እየሳልኩ ነው" በማለት መለሰች። "መኝታ ክፍልሽ የታል" ህጻኗ እያንዳንዱን ክፍል አሳየቻት። ይህ መኝታ ቤት ይህ ደግሞ ወጥ ቤታችን ነው። በዚህ ክፍል ውስጥ እንግዶችን እንቀበልበታለን እያለች የቤቱን ክፍሎች ዘረዘረች። ከሳለችው ግቢ ውስጥ አንድ  ገለልተኛ ክፍልን እናት አስተዋለች። "ይህ ክፍል ከቤቱ ውጭ ከሌሎቹ ክፍሎች ለምን ተነጠለ...?" አለች። "ያንቺ ክፍል ነዋ። እማ እንደ ቅድመ አያቴ እንደ አባዬ አባት እዚህ ክፍል አኖርሻለሁ"   እናት ልጇ የተናገረችውን ማመን አቃታት። ደነገጠች። በህይወቴ መጨረሻ ቀሪ ዘመኔን የልጅ ልጆቼን ድምጽ ሳልሰማ በአራት ግድግዳዎች መካከል ብቻዬን ላሳልፍ? በማለት በትዝብት ራሷን ጠየቀች። እየተጣደፈች ከቤት ወጣች። እጅግ ውብ እና ያሸበረቀው የእንግዶች ማረፊያ ክፍል ውስጥ ያለውን እቃ አወጣች። በግቢው ውስጥ ለብቻው ተገልሎ የሚኖረውን የባሏን አባት ወደዚህ ክፍል አዘዋወረች። ባል ከስራ ሲመለስ ባየው ነገር እየተገረመ   "ደግሞ ምን ተገኘ?" በማለት ጠየቀ። ሚስት እንባዋን እየዘረገፈች መለሰች፡- "እኔና አንተ አላህ እድሜ ከሰጠን ስናረጅ የምናርፍበት ክፍል ነው" አለች። ባል ምን ለማለት እንደፈለገች ተረዳ። አባቱን በፀፀት አይኑ ሲመለከት ፈገግ እያሉ ግንባራቸውን ነቀነቁለት። ህፃኗ እየሆነ ያለውን ስትመለከት እንደመሳቅ አለች። ከላይ ያለው ጥርሷ ከአካባቢው የለም። ደብተሯን አንስታ የተገለለውን ክፍል ከቤቱ ዲዛይን ላይ እያስወገደች ዳግም ፈገግ አለች። "እንዳበደርከው ይከፈልሀል" ማለት ይህ ነው። heppymuslim2
إظهار الكل...
👍 2 1
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.