cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Ayisha Press - አይሻ ፕረስ

ይህ ሚዲያ በልጃችን በእህታችን በእናታች አይሻ ሰይድ ለአማራዊያን ስቃይ ተምሳሌት መታሰቢያ ነው። መረጃን በማስረጃ ማቅረብ መለያችን ነው!! ዓለምአቀፍ እና ሀገራዊ መረጃዎች የሚዳረሱበት፤ ፖለቲካዊ ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት የሚዲያ ተቋም ነው!! ለእውነትና ለሀቅ መቆም ግዴታችን ነው!! Ayisha‼️

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
1 127
المشتركون
+824 ساعات
+617 أيام
+33730 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የፋኖ የዋሲሁን ደረጄን መሰዋትነት ስሰማ ትግላችን ምን አክል መራር እንደሆነ ተረዳሁ። መስዋዕትነት የግድ ነው ግን ፋኖ ደረጄ በላይ በዚህ ትግል ሁለተኛ ልጁ ዋሲሁን ደረጄ መስዋቱ ነው መራራ የሚያደርገው ከሶስት ወር በፊት አንዱ ልጁ አማኑኤል ደረጄ መሰዋቱ ይታወሳል! ትግሉ መራራ ነው ዝም ብለህ ቁጭ ብለህ የምትሰድብበት የምታፌዝበት አይደለም! አርበኛ ደረጄ በቃላት የማይገለጽ መስዋዕትነት ቢሆንም እግዝአብሔር አንተንም መከረኛዋ እናታቸውንም (ያው የወታደር ሚስት 50% ወታደር ነች) ያፅናችሁ! አንተ ግን ትግሉ ዳር ደርሶ ፍሬውን ለማየት ያበቃህ። እንዲህ አይነት መራር ትግል ውስጥ ሆነን ለምን በአንድ ልብ መካሪ በአንድ አንደበት ተናጋሪ መሆን የተሳነን የአማራ ብሔርተኝነት በቅጡ መረዳትና በደማችን ስላልሰረፀ ነው። በተለይ የአማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ ነኝ የምንል አካላት ብሔርተኝነታችን የማይደግፋቸው ተግባራትን ከማድረግ እንቆጠብ። ብሔርተኛ ወንድ፣ሴት፣ሽማግሌ ፣አሮጊት፣ጀግና፣ፈሪ፣ወጣት፣ባለስልጣን፣ምንዘር እያለ አንዱን ከአንድ ለይቶ አያይም ለሁሉም ክብር አለው። የራሱ የሆነ ተቋምና መሪም ሲኖረው ለተቋሙም ለመሪውም ልይ ክብርና ጥበቃ ያደርጋል የመሪውን ቃል ሳያመነታ ይቀበላል ይተገብራል። የአማራ ብሔርተኝነት ይለምልም።
إظهار الكل...
👍 2
የፋኖ የዋሲሁን ደረጄን መሰዋትነት ስሰማ ትግላችን ምን አክል መራር እንደሆነ ተረዳሁ። መስዋዕትነት የግድ ነው ግን ፋኖ ደረጄ በላይ በዚህ ትግል ሁለተኛ ልጁ ዋሲሁን ደረጄ መስዋቱ ነው መራራ የሚያደርገው ከሶስት ወር በፊት አንዱ ልጁ አማኑኤል ደረጄ መሰዋቱ ይታወሳል! ትግሉ መራራ ነው ዝም ብለህ ቁጭ ብለህ የምትሰድብበት የምታፌዝበት አይደለም! አርበኛ ደረጄ በቃላት የማይገለጽ መስዋዕትነት ቢሆንም እግዝአብሔር አንተንም መከረኛዋ እናታቸውንም (ያው የወታደር ሚስት 50% ወታደር ነች) ያፅናችሁ! አንተ ግን ትግሉ ዳር ደርሶ ፍሬውን ለማየት ያበቃህ። እንዲህ አይነት መራር ትግል ውስጥ ሆነን ለምን በአንድ ልብ መካሪ በአንድ አንደበት ተናጋሪ መሆን የተሳነን የአማራ ብሔርተኝነት በቅጡ መረዳትና በደማችን ስላልሰረፀ ነው። በተለይ የአማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ ነኝ የምንል አካላት ብሔርተኝነታችን የማይደግፋቸው ተግባራትን ከማድረግ እንቆጠብ። ብሔርተኛ ወንድ፣ሴት፣ሽማግሌ ፣አሮጊት፣ጀግና፣ፈሪ፣ወጣት፣ባለስልጣን፣ምንዘር እያለ አንዱን ከአንድ ለይቶ አያይም ለሁሉም ክብር አለው። የራሱ የሆነ ተቋምና መሪም ሲኖረው ለተቋሙም ለመሪውም ልይ ክብርና ጥበቃ ያደርጋል የመሪውን ቃል ሳያመነታ ይቀበላል ይተገብራል። የአማራ ብሔርተኝነት ይለምልም።
إظهار الكل...
#ሰበር ኤርትራ የኢሳያስ አፈወርቄ ሀገር የኤርትራ ሰራዊት ዛላንበሳ ከተማን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ።ከአዲግራት ከ40 km ቅርብ በሆነ ቦታም ሰራዊቱ ኬላ መዘርጋቱ ታውቋል። የውስጥ አንበሳ የውጭ እሬሳ የሆነው የአብይ አህመድ አስተዳደር ነሀሴ  20 ቀን 2016 ከተማውን ለቆ መውጣቱን ተለትሎ እንደሆነ ነው የሻአቢያ ሰራዊት ከተማውን ሊቆጣጠር የቻለው ሲሉ የአካባቢው ምንጮች የገለፁት። በአሁኑ ሰዓት ከኤርትራ ከፍተኛ የሆነ የጦር ሀይል እየተጠጋ ይገኛል።
إظهار الكل...
#ሹክሹክታ‼️ የአገዛዙ ሀይል ከ1 ወር በፊት በደስታና በፌስታ የኢንተርኔት አገልግሎትን በአማራ ክልል በይፋ መልቀቁን እና ያዋጣኛል ያለውን ሴራ ለማራገብ በሳይበር ሰዎቹ የአማራ ፋኖ አንድነትን መንኮላሸትን ሰበብ አድርጎ ትግሉ ይኮላሻል የሚል እምነቱን ከወደ ሰሞኑ እንደከሸፈ በደህንነቶቹ በኩል የደረሰው አገዛዙ በልዩ ኦፕሬሽን ሰራዊቱን ወደ አማራ ክልል እያስገባ ኔቶርክና የኢንተርኔት አገልግሎቱን በአንዳንድ አካባቢ እያቋረጠ መሆኑ ተጠቅሷል። ከወደ ሰሞኑ የረገበ የመሰለው አገዛዙ በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች የመከላከያ ሀይሉን በከፍተኛ እያንቀሳቀሰ ይገኛል። የአማራ ፋኖ አባላቶች ከወትሮው በተለዬ መዘጋጀት ጥንቃቄ ማድረግ አይለያችሁ። የድሮንና የጀት ድብደባ ለማድረግ እቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ልብ ያሉት የመረጃ ምንጮች ፋኖዎች አንደኛ አመት መታሰቢያ እና ህዝባዊ ንቅናቄ በሚል በግላጭ የመሰብሰብን አባዜ ቢቀንሱ ይመረጣል ተብሏል።
إظهار الكل...
👍 9
#ሰበር_ዜና‼️ አመሻሹን መርጦ ለማርያም የሚገኘው የሰባ አንደኛ ክፍለጦር አመራሮች በአማራ ፋኖ በጎጃም በዘጠነኛ ክፍለ ጦር አባይ ሸለቆ ብርጌድ ተደመሰሱ። አባይ ሸለቆ ብርጌድ ባደረገው ማጥቃት ከሰማኒያ በላይ የወራሪው አባላት ሲደመሰሱ የሰባ አንደኛ ክፍለጦር አመራሮች ተደምስሰዋል። ከአመራሮቹ የቀረው ከክፍለጦሩ አዛዥ ኮሎኔል አዱኛ የተባለ የወራሪው መሪ ብቻ መሆኑ ተረጋግጧል ።
إظهار الكل...
👏 4
አሳዛኝ መረጃ‼️ በጣም አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ የኦነግ ብልጽግና በተቆጣጠረባቸው አካባቢዎች #የሚደፈሩ የአማራ ሴቶችና ህፃናት ከፍተኛ የአካልና የስነልቦና ጫና እየደረሰባቸው ይገኛል:: ከዛም ባለፈ በርካታዎቹ በሚደርስባቸው ጥቃት  #እያረገዙ እና #የተላላፊ_በሽታ ሰለባ እየሆኑ ይገኛሉ:: የአማራን ሴቶችና ህፃናት መድፈር ታቅዶና ተጠንቶ በኦሮሙማው ብልጽግና እየተደረገ ያለ አውሬነት ነው:: እናት ፣ እህት ፣ ሚስት ፣ ልጅ ያለው ወንድም ይሁን ሴት አማራ እንደ ህዝብ ተነስቶ በአስቸኳይ ይህን የአውሬ ስብስብ ከቀዬው ማፅዳቱ ግድ ነው! ወራሪው መንጋ ከሚጠላን በላይ ጠላትን ጠልተን ፣ አፅድተን ትግሉ #በአጭር መቋጨት ይኖርበታል‼️
إظهار الكل...
ባህርዳር ጥንቃቄ ‼️ በባህርዳር ከተማ የአገዛዙ ሀይል በጅምር ፎቆችና በትላላቅ  ህፃዎች   ስናይፐር ተኳሾች እንዲቀመጡ  በተጠቀቅ    መመሪያ መውረዱ ተሰምቷል ሆኖም ህዝባችንና የፋኖ አባላቶች እጅግ ጥንቃቄ ይደረግ።
إظهار الكل...
🔥 2
#ሰበር_ዜና የደፈጣ ጥቃት በመሀል ሳይንት‼️ ዛሬ በ09 01/2017 ዓ ም የአማራ ፋኖ በወሎ አምሓራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ክንፍ የሆነው በመሀል ሳይንት ወረዳ የሚንቀሳቀሰውና በፋኖ ጎሹ ሳይንቴው የሚመራው የአትሮንስ ብርጌድ ፋኖዎች ቀይዋሻ በተባለ አካባቢ የአገዛዙ ስልጣን ጠባቂ ሠራዊት በሚንቀሳቀሱበት ሰአት ከቀኑ 7 ሰአት አካባቢ ባደረጉት የደፈጣ ጥቃት ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የአገዛዙ ጥምር ጦር ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። በተያያዘ ዜና በዚሁ አካባቢ ከአገዛዙ ጋር በጥምረት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 6 ሚሊሻዎች በሰላም እጃቸውን ሰጥተዋል።   ሌሎችም ከወንድሞቻቸው በመማር እጃቸውን በሰላም እንድሰጡ የብርጌዱ አዛዥ ተናግሯል። #ድል_ለአማራ_ህዝብ #ድል_ለፋኖ
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
አንድነት ሀይል ነው ! የአማራ ፋኖ በጎንደር የአድዋ ክፍለ ጦር አመራሮች የአሰራር እና የትግል ተሞክሮ ልውውጥ ከአማራ ፋኖ በጎጃም የቢተወደድ አያሌው መኮነን ብርጌድ አመራሮች እና የብርጌዱ የየደረጃው አመራሮች በተገኙበት ተሞክሮ ተለዋውጠዋል ። ድል ለአማራ ፋኖ !
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰበር አርቲስት አዜብ ወርቁ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ አርቲስቷ በ3ኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደምትገኝ  ተገልጸዋል። አርቲስቷ ሰሞኑን "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት!" የሚል ጽሁፍ በማህበራዊ ሚዲያዎች ካጋራች በኋላ ጽሁፉ መነጋገሪያ ሆኖ እንደነበርና በኋላም ከማህበራዊ ገጿ ጽሁፉን ማንሳቷን ማስታወቋ አይዘነጋም።
إظهار الكل...
👍 3 1
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.