cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Abu Reyan~Channel

እውቀት ብርሀን ሲሆን አለማወቅ/ ጅህልና ጨለማ ነው።እንቅራ በጊዜአችን እንጠቀም ሰዎች መለወጥ ካልቻልን እራሳችን እንለውጥ።ከራሳችን ጀምረን ቤተሰባችን እንታደግ ከተለያዩ ከሱሶች;ከቢድአ ;ከሽርክ እንራቅ።ወደ ቻናላችን ለመግባት ከፈለጋቹ https://t.me/AbuRyane ኢማሙ አዙኸይብይ እንድህ አሉ እውቀት ባለህ ነገር ተናገር አልያ ችለህ ዝም በል።(አላህ ይርኸማቸው)joi@

Show more
Advertising posts
224
Subscribers
-224 hours
-47 days
-630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

********** ነጯስገጃ? ********** አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ። በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ በጣም ሩህሩህ። የአላህ ሶላትና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ ላይ ይሁን። የአላህ ባሪያዎች ሆይ! እነዚህን ሁለት ፎቶዎች ተመልከቱ። ሀገራችን ላይ መውሊድ አክባሪዎች ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም "ይመጣሉ" ብለው የሚያምኑ ሰዎች "ሀድራ" ላይ ነን ብለው በሚከተለው ሁኔታ ይቀመጣሉ ይቆማሉ። ነጯን ምንጣፍ ሰው አይቀመጥባትም። "ነብዩ ከነሶሀባዎቻቸው ሲመጡ የሚያርፉባት ናት።" ብለው ስለሚያምኑ። ሌሎች የሚሉዋቸውን አባባሎች ቁጭ ብለው ይሉና፣ የሚከተሉትን ስንኞች ሲያነቡ ይቆማሉ። 1) "መርሃባ ነቢ መርሃባ፣ መርሃባ ነቢ መርሃባ።" ትርጉሙ "ነብዩ ሆይ! እንኳን ደህና መጡ።" 2) "አርሂቡ ነቢ፣ አርሂቡ ነቢ፣ ያ ሀቢቢ።" ትርጉሙ "ነብዩ ሆይ ግቡ፣ ግቡ።" ነብዩ ይመጣሉ ብለው ያምናሉ ስንል በማስረጃ ነው። አላህ ይምራውና ስንት ሰዎችን በክህደት መንዙማው ያጠመመው ሙሐመድ አወል ሐምዛ እንዲህ ይላል "አይዟችሁ ተደሰቱ መውሊድ የመጣችሁ፣ ከነ አስሀቦቹ (ከሰሀቦችም ጭምር) ነቢ መጡላችሁ።" ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ግን እንዲህ ይላሉ "የቂያማ ቀን መጀመሪያ ቀብሪ ተከፍቶልኝ የምወጣው እኔ ነኝ።" የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ይህን ሁሉ ከሸሪአ የሚጋጩ እምነቶች እና ተግባራትን እያያችሁ አሁንም የሰይጣንን ጥሪ ተቀብላችሁ መውሊድ ታከብራላችሁ? ለነፍሳችን እንዘንላት። ነብዩ አይመጡም። ሱናቸው ግን ይሀው ፊት ለፊራችን ቀርቦልናል የህይወት ስንቅ አድርገን እንተግብረው። አላህ በነብዩ ሱና ከሚብቃቁት ያድርገን። https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
Show all...
01:30
Video unavailableShow in Telegram
13.83 MB
እውነታው ይኸው ነው * በሰሞኑ በኦሮምያ ክልል ባሌ አካባቢ በአንድ የመንግስት ታጣቂ ፖሊስ የተደበደበችው እህት እውነታው ከቦታው በማጣራት እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ። ይህን ክስተት ያጣሩልን ወንድም ነዋሪነታቸው በሳዑድ አረቢያ የሆነ አሁን ላይ ለቤተሰብ ጥየቃ የመጡ ሸይኽ ሮቤ ይባላሉ። 1- የተደበደበችው እህት ሙስሊም እንጅ የሌላ ሀይማኖት ተከታይ አይደለችም። [ሙስሊሟን እህት በውሸት ማክ — ፈር ተገቢ ነውን?] 2- የደበደባት ፖሊስም ወደዚህ ጣቢያ ከተመደበ ገና ወራቶችን ያስቆጠረ ሙስሊም ነው። 3- ይህች ተበዳይ በዋስ ያስወጣት ሙስሊም የሀገር ሽማግሌ ነው። 4- አሁን ከቪድዮው ፖሊሱ ቀርቦ የሰጠው ምላሽ ይህች እህት ተጠርጣሪ ሆና በማየቱ በስሜት እና ተገቢ ባልሆነ መንገድ አፀያፊ ተግባር ፈፅሜያለሁ ፤ ለዚህም የርሷ እና የኔ ጉዳይ በሀገር ሽማግሌ ተይዞ የኔም የርሷም ጎሳ ቀርበው በተነጋገሩት መሰረት ክብሯን እና በደሏን የሚመልስ ነገር ባይሆንም ለመካስ ተስማምተናል ይለናል። ይህ ጉዳይ እንዳይደገም: ሀቅ እንዳይደበቅ ጊዜውን ሰጥቶ አቀራርቦ ከዚህ ደረጃ ያደረሳቸውን ሸይኽ ሮቤ አላህ ጀዛህን ይክፈልህ። እውነታው ይህ ነው ። ኢንጅነር አብዱ ሙሃመድ = ማሳሰቢያ ~ ሰሞኑን የሌላ እምነት ተከታይ የሆነች የታወቀች ሌባ ናት፣ ሌላ ጊዜ ወንድ ነው የሚሉ ቅንብሮችን አዘጋጅተው የለቀቁት ሆን ተብሎ የታሰበበት ተንኮል ነው። አላማው በተበዳይ እህታችን ሂሳብ ወንጀለኛን መደበቅ፣ አጀንዳ ማስቀየር ነው። ስንት ህዝብ በእህታችን ላይ እንደፈረደ አስቡት። ውጤቱ ግን ከዚህም የከፋ ነው። ከዚህ በኋላ እህቶቻችን ላይ የሚደርስ በደል በቂ ግፊት እንዳይገጥመው የሰውን ስነ ልቦና የሚያቀዘቅዝ፣ ለኒቃብ ጠል ሃይሎች ግብአት የሚሆን ትወና ነው ሰሞኑን የተሰራው። ከመጀመሪያም ጀምሮ አንዴ ሙስሊም ያልሆነች አመለኛ ናት፣ አንዴ ወንድ ሆኖ ተገኘ ሲባል በጣም ነው ያመመኝ። ይበልጥ ያመመኝ የሰውን ሃሳብ በማሳሳት ላይ የተሰማሩት ታዋቂ አክቲቪስቶች መሆናቸው ነው። ነገሩን በቅንነት በየዋህነት ተመልክታችሁ በነዚህ አካላት የተሸወዳችሁ ወገኖች ትምህርት ውሰዱ። ያለፈውን መመለስ ባንችል እንኳ ይህኛውን በደንብ "ሼር" በማድረግ ትንሽም ብናካካስ ደስ ይለኛል። በምትችሉት መጠን ሁሉ ሼር አድርጉት። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

የምንማርበት በቂ ጦርነት ያላየን ይመስል አሁንም በጦርነት ዜና የሚደሰቱ ወገኖችን እየተመለከትን ነው። ጦርነት ብዙ እልቂት አድርሷል እያደረሰም ነው። ለሃገርም ለወገንም የሚሻለው ሰላም ነው። ሰላም ምትክ የሌለው ምርጫ። ጦር ሜዳ የቀረ ልጇን አጥታ በሀዘን ክፉኛ የተሰበረች፣ ያለ ጧሪ የቀረችን እናት ዞሮ የማያይ ሁላ ከወላፈኑ ርቆ የጦር ነጋሪት ይጎስማል። የሶማሊያም፣ የሱዳንም ህዝብ ወገናችን ነው። ከትስስራችን ባሻገር ሰላማቸው ለኛም ትርጉም አለው። ብዙ የሃገራችን ወጣት በትምህርትም በስራም ሱዳን ውስጥ ይኖራል። በሃገር ውስጥ ያለው ጦርነት ብዙ ጉዳት አምጥቶብናል። ይሄ ለመማሪያነት አልበቃ ብሎ ከጎረቤት ጋር የሚኖርን ግጭት በጉጉት መጠበቅ ልክፍት ነው። ለሃገራችንም ለጎረቤቶቻችንም አላህ ሰላም ያምጣልን። ከራሳችንም ከጎረቤትም ጋር መግባባትን ያድለን። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

Photo unavailableShow in Telegram
03:50
Video unavailableShow in Telegram
አጂብ የሆነ መልክት አድምጡትማ 👂👂👂ሼርም አድርጉት ለወዳጆቻቹ የ ቲክቶክ ትውልድ..........🗣🗣🗣🗣 🎙በሸይኽ ኢልያስ አህመድ (ሐፊዘሁላህ) ቴሌግራም ቻናላችንን ጆይን ይበሉ https://t.me/yeilyaswedaje
Show all...
document_5972133509483991870.mp48.78 MB
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته መውሊድን በተመለከተ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር የተዘጋጁ ከፊል ፅሁፎችን በቀላሉ እንዚህን ሊንኮች በመጫን ማንበብ ትችላላችሁ። 1, ነብዩ ﷺ መቼ ተወለዱ? https://t.me/IbnuMunewor/893 2, መውሊድን ማን ጀመረው? በመረጃ ለሚያምኑ ብቻ https://t.me/IbnuMunewor/869 3, መውሊድ ለምን አላማ እንደተጀመረ ያውቃሉ? https://t.me/IbnuMunewor/876 4, መውሊድና ነባሩ እስልምና አይተዋወቁም! {ምስክር እራሳቸው!} https://t.me/IbnuMunewor/884 5, “በአላህ እዝነት ይደሰቱ...” - ትልቁ የመውሊድ አጋፋሪዎች ምርኩዝ https://t.me/IbnuMunewor/2227 6, የሰኞ ፆም እና መውሊድ https://t.me/IbnuMunewor/2214 7, ዐቂቃ ሌላ መውሊድ ሌላ! https://t.me/IbnuMunewor/2261 8, ዓሹራን ለመውሊድ? https://t.me/IbnuMunewor/2269 9, መውሊድ ውስጥ እነዚህ አደጋዎች አሉ! https://t.me/IbnuMunewor/2294 10, በመውሊድ ላይ ስለሚፈፀመው ጭፈራ ዑለማዎች ምን እንዳሉ ታውቃለህ? https://t.me/IbnuMunewor/882 11, መውሊድን የሚፈቅዱትም አይፈቅዱትም! https://t.me/IbnuMunewor/2298 12, መውሊድ የማያከብር ሰው የሙሐመድ ﷺ ጠላት ከሆነ፣ ገና የማያከብር ሰው የዒሳ ጠላት ነው! https://t.me/IbnuMunewor/886 13, እውን የሡወይባ ታሪክ ለመውሊድ ማስረጃ ይሆናል? https://t.me/IbnuMunewor/2234 14, ሸውካኒ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት) https://t.me/IbnuMunewor/898 15, ሲዩጢ፣ የመውሊድ ደጋፊዎች ሌላኛው ምርኩዝ https://t.me/IbnuMunewor/2277 16, እውን ኢብኑ ተይሚያ መውሊድን ፈቅደዋል? https://t.me/IbnuMunewor/878 17, በሸይኹል አልባኒ እና “መውሊድ ይፈቀዳል” በሚል ሰው መካከል የተደረገ ድንቅ ቃለ-ምልልስ https://t.me/IbnuMunewor/34 18, ከ“ወሃብዮች” በፊት የነበሩ የመውሊድ ተቃዋሚዎች https://t.me/IbnuMunewor/1624 19, መውሊድ ተከሽኖ https://t.me/IbnuMunewor/2309 20, ለምንድን ነው የመውሊድ ተቃውሞ ኢኽዋኖችን ምቾት የሚነሳቸው? https://t.me/IbnuMunewor/918 21, መሷሊሐል ሙርሰላ፣ የመውሊድ አክባሪዎች የመጨረሻው ምሽግ https://t.me/IbnuMunewor/2302
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

ነብዩ ﷺ መቼ ተወለዱ? ሌላ የመውሊድ ራስ ምታት ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ መውሊድ በኢስላም መሰረት እንደሌለው ከሚያመላክቱ ማስረጃዎች አንዱ ታሪክ ነው። ነብዩ ﷺ በምን ወር ተወለዱ? በስንተኛው ቀን? በስንት አመት? ለነዚህ ጥያቄዎች የሚኖረን መልስ በራሱ የመውሊድን በዓል አላስፈላጊነትና መሰረት-አልባነት ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል። 1. የተወለዱበትን አመት በተመለከተ በዝሆኑ አመት ማለትም የሐበሻው አብረሀ ከዕባን ለማፍረስ በዝሆን የታጀበ ሰራዊት ይዞ የዘመተበት አመት ነው። ይህም እ.ኤ.አ በ 570 ወይም 571 ማለት ነው። በታዋቂዎቹ የሱንና ኪታቦች ውስጥ ይህን የሚያመላክት መረጃ ባይኖርም በኢብኑ ዐባስ ስም በይሀቂ የዘገቡት ግን አለ። ግና ይህም ቢሆን ሰነዱ መጠነኛ ውዝግብ አለበት። “በዝሆኑ አመት በየትኛው ጊዜ?” የሚለው እራሱ የተለያዩ ሀሳቦች ተሰንዝረውበታል። ለምሳሌ ነብዩ ﷺ የተወለዱት፡- 1.1. በዘመቻው እለት ነው የሚል ሰነድ አልባ ዘገባ ከኢብኑ ዐባስ ተዘግቧል። 1.2. ከዝሆኑ ዘመቻ ከወር በኋላ ነው ተብሏል። 1.3. ከዝሆኑ ዘመቻ ከ40 ቀን በኋላ ነው ተብሏል። 1.4. ከዝሆኑ ዘመቻ ከ 50 ቀን በኋላ ነው ተብሏል። [አልኢስቲዓብ፡ 1/30] የዝሆኑ ዘመቻ ሙሐረም 13 እንደተካሄደ አልኸዋሪዝሚና ሌሎችም የጠቀሱ ሲሆን ሌሎች ደግሞ “የለም ረቢዑል አወል ነው” ይላሉ። የነዚህን ሀሳብ ከግምት ካስገባን 8 የተለያዩ ሃሳቦች ኖሩ ማለት ነው። በሙሐረም ከሆነ አራት፣ በረቢዑል አወል ከሆነ ደግሞ ሌላ አራት። በድምሩ ስምንት። 2. “በምን ወር ተወለዱ?” ለሚለውም ብዙ ሀሳቦች ተነስተዋል። 3.1. በሶፈር ወር ነው ያሉ አሉ። 3.2. በረመዷን ወር ነው ያሉ አሉ። ይሄ ሀሳብ ከታዋቂው የታሪክ ምሁር ዙበይር ኢብኑል በካር (256 ሂ.) እና ከሌሎችም ተላልፏል።…

እንቁጣጣሽ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 57፥3 ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ “ጳጉሜ” የሚለው ቃል “ኤፓጎሜኖይ” ἐπαγόμενοι ከሚለው ከግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ “ተጨማሪ” ወይም “የተጨመረ” ማለት ነው፥ ጳጉሜ የወር ስም ሲሆን በነባሮች 12 ወራት ላይ የተጨመረ 13ኛ ወር ነው። ይህም ወር በነሐሴ እና በመስከረም መካከል የሚገኝ የመጨረሻው ወር ነው፥ ጳጉሜ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በዘመነ ሉቃስ ስድስት ቀናት ሲኖሩር በዘመነ ዮሐንስ፣ በዘመነ ማቴዎስ እና በዘመነ ማርቆስ አምስት ቀናት ይሆናል። ልብ በሉ! ይህ ወር ከግሪክ ሄለኒዝም የተጀመረ እና ከአሌክሳንድርያ ወደ ኢትዮጵያ የገባ እንጂ በዕብራውያን አቆጣጠር ላይ ወራት 12 ብቻ ናቸው። አምላካችን አሏህ የወሮች ቁጥር በእርሱ መጽሐፍ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር እንደሆነ ነግሮናል፦ 9፥36 አላህ ዘንድ የወሮች ቁጥር በአሏህ መጽሐፍ ዉስጥ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው። إِنَّ عِدَّةَ ٱلشُّهُورِ عِندَ ٱللَّهِ ٱثْنَا عَشَرَ شَهْرًۭا فِى كِتَٰبِ ٱللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ ይህ የሚያሳየው የኢትዮጵያው ዘመን መለወጫ በልምድ ከግሪክ የመጣ ሰርጎገብ እንጂ አገር በቀል አይደለም፥ ከዚያም ባሻገር መለኮታዊ ትእዛዝ ያለው ሳይሆን ሰው ሠራሽ ቢድዓህ ነው። ዓመተ ምሕረትን ያማከለ ዘመነ ሉቃስ፣ ዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ሰው ሠራሽ ሃይማኖታዊ አስተምህሮት ነው፥ በዛ ላይ የባዕድ አምልኮ የሚፈፀምበት ቀን ነው። በጳጉሜ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ፥ በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ ጌጦች እና የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ። ይህ ቀን ሲያልቅ የቀኑ መጨረሻ ተጓግቶ ስለሚመጣ “እንቁ” ተባለ፥ የሚያመጣው ጣጣና መዘዝ ደግሞ “ጣጣሽ” ተባለ። በጥቅሉ “እንቁ ጣጣሽ” ተባለ፥ ጥንቆላና ድግምት ከትልቁ ሽርክ የሚመደቡ የአሏህን ሐቅ የሚነካ ትልቅ በደል ነው። እንቁጣጣሽን ማክበር አቆጣጠሩ አገራዊ ሳይሆን እምነታዊ መሠረት ያለው ሲሆን ከእርሱ ጋር የተያያዙት ባዕድ አምልኮ አስበን ከዚህ ሰው ሠራሽ በዓል እራሳችንን እንጠብቅ! እንግዲህ እንቁጣጣሽ ዓመታዊ በዓል ዓረማዊ እና ክርስትናን ቀላቅሎ የያዘ በዓል ነው፥ በዚህ ጊዜ "እንኳን አደረስን" ወይም "እንኳን አደረሳችሁ" ሲባል ይህንን በዓል ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ሙሥሊም ያሉት ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻ እና ብቻ ናቸው፥ እነርሱም ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦ ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 745 አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” መዲና ሲገቡ የመዲና ሠዎች የሚደሰቱባቸው ሁለት በዓላት እንዳሏቸው ዐወቁ። እርሳቸውም፦ "እነዚህ ሁለቱ ቀናት ምንድን ናቸው? በማለት ጠየቁ፥ "ሰዎችም በጃሂሊያ ጊዜ እንጫወትባቸው የነበሩ በዓላት ናቸው አሏቸው። የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ ”አሏህ ከእነርሱ የተሻሉ ሁለት ዒዶችን ሠጥቷችኋል፥ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓን አሏቸው”። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ قَدِمَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْمَدِينَةَ وَلَهُمْ يَوْمَانِ يَلْعَبُونَ فِيهِمَا فَقَالَ ‏”‏ مَا هَذَانِ الْيَوْمَانِ ‏”‏ ‏.‏ قَالُوا كُنَّا نَلْعَبُ فِيهِمَا فِي الْجَاهِلِيَّةِ ‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ إِنَّ اللَّهَ قَدْ أَبْدَلَكُمْ بِهِمَا خَيْرًا مِنْهُمَا يَوْمَ الأَضْحَى وَيَوْمَ الْفِطْرِ ‏”‏ ‏.‏ ጃምዒ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121 ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፥ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው”። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏ ጃምዒ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 91 አቡ ሰዒደል ኹድሪይ እንደተረከው፥ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” ”በሁለቱ በዓል በዒደል አደሐ እና ዒደል ፈጥር መጾም ከልክለዋል”። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، قَالَ نَهَى رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنْ صِيَامَيْنِ يَوْمِ الأَضْحَى وَيَوْمِ الْفِطْرِ ‏. “ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። ስለዚህ ከአላህ የወረዱትን ቁርኣን እና ሐዲስ ብቻ ከተከተልን ሁለት በዓል ብቻ እና ብቻ አለን፦ 7፥3 ከጌታችሁ ወደ እናንተ የተወረደውን ተከተሉ። اتَّبِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَيْكُم مِّن رَّبِّكُمْ “ተከተሉ” የሚለው ቃል “ኢተቢዑ” اتَّبِعُوا ሲሆን “ኢትባዕ” إِتْبَاع‎ ማለት እራሱ የቢድዓህ ተቃራኒ "ከአሏህ ወደ ነቢያችን”ﷺ” የተወረደውን ብቻ መከተል" ማለት ነው። "ቢድዓህ" بِدْعَة የሚለው ቃል "በደዐ" بَدَّعَ ማለትም "ፈጠረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ፈጠራ” ማለት ነው፥ ቁርኣን እና ሐዲስ ላይ የሌለ ነገር በዲን ላይ መጨመር "ቢድዓህ" ሲሆን ሙሥሊም ግን የተወረደውን ብቻ ሲከተል ሁለት ዒድ ብቻ እና ብቻ ያከብራል። ስለዚህ "እንቁጣጣሽ" ስንባል "እንኳን ደህና መጣሽ" ከማለት ይልቅ "ማን አመጣሽ?" ብለህ በታሪካዊ ዳራ እና ፍሰት እንሞግታለን። በዓሉን ባለማወቅ ለሚያከብሩ አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Show all...
ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Photo unavailableShow in Telegram
ጃዋር መሀመድ እንዲህ ይላል 👇 ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ በፍትሃዊነት የመጠቀም መብታችንን ለምግታት እንደምትዝተው ሁሉ፣ ቀጥተኛ ወታደራዊ እርምጃን መውሰድ አትችልምም፤ አትፈልግም። ይልቁንም ውሃዉን ለማልማት አቅም የሚነሱን እና ትኩርታችንን የሚበታትኑ ሶስት መሰረታዊ ስልቶችን ተጠቀማለች፡፡ እነዚህም፣ በውስጣዊ ግጭቶች መወጠር፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ማጋጨትና አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለአባይ ልማት የሚውል ገንዘብ እንዳይሰጡን ማግባባት። አሁን ላይ በራሳችን ተነሳሽነት በውስጣዊ ጦርነት እየታመስን እንዲሁም ከጎረቤት ሀገራት ጋርም አምባጓሮ ውስጥ ስለገባን ለግብጽ ሰርግና ምላሽ ሆኖላታል ማለት ይቻላል። ሰሞኑን የምታደርገው ዛቻም ከዚሁ የኢትዮጲያ ተጋላጭነት የመነጨ ነው። መፍትሄውም ዛቻውን ለማስተንፈስ ውስጣዊ ግጭቶችን በሰላም መፍታት እና ከጎረቤቶቻችን ጋር የተፈጠረውን እሰጣገባም ማርገብ ወሳኝ ይሆናል። በዚህ ጉዳይ ላይ ባለፉት አመታት በተደጋጋሚ ስጽፍና፣ ስናገር እና ምክረ-ሀሳብ ስለግስ ቆይቻለሁ። https://t.me/AbuRyane
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.