cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የኢ/ኦ.ተዋሕዶ. መዝሙር

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምሮነ ስርአት የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ከነዜማቸው በየቀኑ ወደነንተ ያቀርባል። ይቀላቀሉ አስተያየት ሀሳብ ጥያቄዎች ከአላቸው @adiss0101 ✟✟✟✟

Show more
Advertising posts
4 061
Subscribers
No data24 hours
+1577 days
+47230 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?
Show all...
ቅዱስ ራጉኤል
ቅዱስ ገብርኤል
ቅዱስ ሚካኤል
ቅዱስ ዑራኤል
💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕 [┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ [┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ ┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓ 💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕 ┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛ 🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇 🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧
Show all...
💕መዝሙሮችን ለማዳመጥ 💓
💕ለ መ ቀ ላ ቀ ል ❣️
Photo unavailableShow in Telegram
Show all...
💠የሽብሻቦ መዝሙሮች💠
💠የንስሐ መዝሙሮች💠
💠የቅዱሳን መዝሙሮች💠
💠የመላእክት መዝሙሮች💠
💠የሰማዕታት መዝሙሮች💠
💠የሃዋርያት ሙዝሙሮች💠
💠የሠርግ መዝሙሮች💠
💠የንግስ መዝሙሮች💠
💠ለወቅታዊ መዝሙሮች💠
💠ሁሉንም መዝሙሮች💠
Show all...
💕ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር
💕ኦርቶዶክሳዊ ስብከት
💕ኦርቶዶክሳዊ ዜናዎች
💕 ቃለ ስብሐት
💕 ሁ ሉ ን ም ባ ን ድ ላ ይ 💕
💁 " ፍልሰታ " ማለት ምን ማለት ነው ❓
Show all...
ማረግ
መሻገር
መሸሽ
ሁሉም
ድንቅ አድርጎልኛል ድንቅ አድርጎልኛል የሠራዊት ጌታ 2 አልረሳኝም አምላክ አነሳኝ ከትቢያ 2
አዝ
ድንቅ አድርጎልኛል በደሌን ሳይቆጥር ድንቅ አድርጎልኛል ወደቤቱ ጠራኝ ድንቅ አድርጎልኛል እረክሼ ሳለሁ ድንቅ አድርጎልኛል ልጄ ሆይ ና አለኝ ድንቅ አድርጎልኛል በዳግም ምጻቱ ድንቅ አድርጎልኛል መንግስቱን ሊያወርሰኝ
አዝ
ድንቅ አድርጎልኛል ከአንበሳ መንጋጋ ድንቅ አድርጎልኛል ከጉድጓድ አወጣኝ ድንቅ አድርጎልኛል በጠላቶቼ ፊት ድንቅ አድርጎልኛል ግርማ ሞገስ ሰጠኝ ድንቅ አድርጎልኛል ምን እመልሳለሁ ድንቅ አድርጎልኛል እንዲህ ለወደደኝ
አዝ
ድንቅ አድርጎልኛል ጠላቶቼ ሁሉ ድንቅ አድርጎልኛል ሲጓደዱብኝ ድንቅ አድርጎልኛል ማን ይደርስለታል ድንቅ አድርጎልኛል እያሉ ሲሉኝ ድንቅ አድርጎልኛል ፈጥነህ ደረስክልኝ ድንቅ አድርጎልኛል ከሞት አዳንከኝ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ @mazmur2122 @mazmur2122 @mazmur2122
Show all...
ዘማሪ_ቀሲስ_ምንዳዬ_ብርሃኑ_Mendaye_Birhanu_ድንቅ_አድርጎልኛል_Denk_Adrgolgna.m4a5.30 MB
👍 7🥰 3
🕊 †  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን  † [  † መስከረም 7 [ ፯ ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  †  ] እንኩዋን ለቅድስት ኤልሳቤጥ: ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ሊቅ እና አባ ሳዊርያኖስ ክቡር ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ [  †  🕊 ቅድስት ኤልሳቤጥ  🕊  †  ] በወንጌላዊው አንደበት የተመሰገነች እናታችን ቅድስት ኤልሳቤጥ ትውልዷ ከነገደ ሌዊ ነው:: ሐረገ ሙላዷም ከቅዱስ አሮን ካህን ወገን ይመዘዛል:: ከአሮን በቴክታና በጥሪቃ ወርዶ ሔርሜላ ላይ ይደርሳል:: ይህቺ ሔርሜላ የምትባል ደግ ሴት ማጣት ["ጣ" ጠብቆ ይነበብ] የሚባል የተባረከ ሰው አግብታ ፫ [3] ቡሩካት ልጆችን ወለደች:: የመጀመሪያዋን 'ማርያም' አሏት:: እርሷ ቅድስት ሰሎሜን ወለደች:: ሁለተኛዋን 'ሶፍያ' አሏት:: እርሷ ደግሞ ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች:: ሦስተኛዋ ግን የተለየች ናት:: 'ሐና' ብለው ሰየሟት:: እርሷም የሰማይና የምድር ንግሥት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ወለደች:: በዚህም መሠረት ድንግል ማርያም: ቅድስት ኤልሳቤጥና ቅድስት ሰሎሜ የእህትማማች ልጆች ናቸው:: ቅድስት ኤልሳቤጥ እድሜዋ በደረሰ ጊዜ ስም አጠራሩ የከበረ: ደግ ካህን ለሆነ: ለቅዱስ ዘካርያስ አጋቧት:: እርሷ የሊቀ ካህናቱ ሚስት ናትና ክብሯ ከፍ ያለ ነበር:: ምንም ልጅ ባይኖራትም ዘወትር በጸሎትና በጾም: ምጽዋትንም በማዘውተር: ነዳያንንም በማሰብ የምትኖር እናትም ነበረች:: ቅዱስ ወንጌል ላይ ከእመቤታችን ቀጥሎ የነዘካርያስን ቤተሰብ ያህል ክብሩ የተገለጠለት ፍጡር ይኖራል ብሎ መናገሩ ይከብዳል:: ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጀመረው በዚህ ቅዱስ ቤተሰብ ነውና መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ሲል አጽፎታል:: "ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል:: [ሉቃ.፩፥፮] (1:6) የሰውን እንተወውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ መኖር ምን ይረቅ? ለዚህ አንክሮ [አድናቆት] ይገባል! እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ ፺ [90] የዘካርያስ ፻ [100] ደግሞ ደርሶ ነበር:: ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ ግን በስተ እርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው:: ቅድስቲቷ መስከረም ፳፮ [26] ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: ድንግል እመቤታችን ወደ እርሷ መጥታ 'ሰላም' ባለቻት ጊዜ ምንም ያሳደገቻት ልጇ ማለት ብትሆን: መንፈስ ቅዱስ ስለ ሞላባት እመ ብርሃንን አመስግናታለች:: ቡርክት: ብጽእት: ከፍጥረተ ዓለሙ የከበረች መሆኗንም መስክራለች:: በማሕጸኗ ያለ የ፮ [6] ወር ጽንስም የእመ አምላክን ድምጽ ቢሰማ በደስታ ዘሏል:: ለፈጣሪውም ስግደተ-ስባሔ አቅርቧል:: ቅድስት ኤልሳቤጥ አክላም "ወምንትኑ አነ ከመ ትምጽኢ ኀቤየ እሙ ለእግዚእየ-የጌታየ እናቱ ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እንዴት ይገባኛል?" ስትል በትኅትና ተናግራለች:: ከጌታ እናት ጋር ለ፫ [3] ወራት በአንድ ቤት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ ፪ [2] ዓመት ከ፮ [6] ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና እሱንም ግደል" አሉ:: እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑን ዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል:: አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ፫ [3] ፭ (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ ፭ [5] ፯ (7) ዓመት ሲሞላው ግን እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት:: ኤልሳቤጥ ማለት 'እግዚአብሔር መሐላየ ነው': አንድም 'የጌታ አገልጋይ' ማለት ነው:: [ † 🕊 ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ሊቅ  🕊 †  ] ይህ አባት የተዋሕዶ ሃይማኖታችን ምሰሶ ነው:: በ፭ [5] ኛው መቶ ክ/ዘመን በግብጽ ተወልዶ አድጐ: በልጅነቱ መጻሕፍትን ተምሮ: የምናኔ ሕይወትን መርጧል:: ቆይቶም የታላቁ ሊቅ ቅዱስ ቄርሎስ ረድእ ሆኖ ተምሯል: አገልግሎታል:: በጉባኤ ኤፌሶን ጊዜም ቅዱስ ቄርሎስን ተከትሎ ሒዶ ተሳትፏል:: በ፬፻፵፬ [444] ዓ/ም ታላቁን ሊቅ ተክቶ የእስክንድርያ ፳፭ [25] ኛ ፓትርያርክ ሆኖ ተሹሟል:: ለ፯ [7] ዓመታትም መጽሐፈ ቅዳሴውን [እምቅድመ ዓለምን] ጨምሮ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል:: በመልካም እረኝነትም ሕዝቡን ጠብቇል:: ዘመነ ሰማዕታትን ተከትሎ የመጣው የመናፍቃን ዘመን ሲሆን ለ፻፶ [150] ዓመታት ያህል መናፍቃን እንደ አሸን ፈልተዋል:: በዚያው ልክ ከዋክብት ቅዱሳን ሊቃውንት ነበሩና በየጊዜው ጉባኤያትን እየሠሩ: መናፍቃንን አሳፍረዋል:: ምዕመናንንም አጽንተዋል:: በ፬፻፶፩ [451] ዓ/ም የተፈጸመው ድርጊት ግን ዛሬም ድረስ ጠባሳው የሚለቅ አልሃነም:: ንጉሡ መርቅያንና ዻዻሱ ልዮን የንስጥሮስን ትምሕርት አለባብሰው ሊያስተምሩ ሲሞክሩ ግጭት በመፈጠሩ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ፪ [2] ተከፈለች:: በጉባኤው የነበሩ ፮፻፴፮ [636] ዻዻሳት ስቃይና ሞትን ፈርተው በኑፋቄ መጽሐፍ ላይ በመፈረማቸው "መለካውያን" [ከእግዚአብሔር ይልቅ ለንጉሥ የሚታዘዙ] ተባሉ:: ጉባኤውም "ጉባኤ ከለባት" [የውሾች ስብሰባ]: "ጉባኤ አብዳን" [የሰነፎች ጉባኤ] ተብሏል:: ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ግን "በኑፋቄው ላይ አልፈርምም" ከማለቱ አልፎ መናፍቃኑን አወገዛቸው:: በዚህ ምክንያት ወደ ጋግራ ደሴት ከ፯ [7] ደቀ መዛሙርቱ ጋር አሳደዱት:: በዚያም ለ፫ [3] ዓመታት ቆይቶ በ፬፻፶፬ [454] ዓ/ም ዐረፈ:: ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከማረፉ በፊት በተሰደደባት ደሴተ ጋግራ ለ፫ [3] ዓመታት ብዙ መከራ ከመናፍቃን ደርሶበታል:: እርሱ ግን በትእግስቱና በትምሕርቱ ብዙዎችን ወደ ሃይማኖት መልሷል:: ቤተ ክርስቲያን እርሱን 'አበ ተዋሕዶ' [የተዋሕዶ እምነት አባትና አርበኛ] ትለዋለች:: የተነጨ ጺሙ: የረገፉ ጥርሶቹና የፈሰሰ ደሙ ዛሬም ድረስ ትልቅ ምስክርና የሃይማኖት ፍሬ ነውና:: "ያስተጻንዕ ህየ እለ ኀለዉ ደቂቀ: ዘተነጽየ እምነ ጽሕሙ ወእም አስናኒሁ ዘወድቀ: ፍሬ ሃይማኖቱ ፈነወ ብሔረ ርሑቀ" እንዲል:: [  † 🕊 ታላቁ አባ ሳዊርያኖስ  🕊 †  ] የዚህን ቅዱስ ሰው ስም የሚጠራ አፍ ክቡር ነው:: ጣዕመ ሕይወቱ ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም:: እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የበቀለ: ፴ ፡ ፷ : ፻ [30: 60: 100] ፍሬዎችን ያፈራ የመንፈስ ቅዱስ ተክል ነው:: በትውልድ ሮማዊ ሲሆን የተወለደው በ፫፻፱ [309] ዓ/ም ነው:: ወላጆቹ በዚህ የንጉሥ ዘመዶች: በዚያ ደግሞ ባለጠጐች ነበሩ:: እነርሱ ለልጃቸው ጥበብን መርጠዋልና የግሪክን ፍልስፍና: የዮናናውያንን ጥበብ ሁሉ ተማረ:: ከዚያ በአንድ ልቡ ብሉይን: ሐዲስን ተምሮ ሲጠነቅቅ ወላጆቹ ዐረፉ:: ቅዱሱ ሳዊርያኖስም "የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር መስጠት አለብኝ" ብሎ ቀን ቀን ያለፈውን: ያገደመውን ሁሉ ሲያበላ: ሲያጠጣ: ነዳያንን ሲጐበኝ ይውላል:: ምሽት ሲል ደግሞ ወደ ቅዱሱ ንጉሥ [አኖሬዎስ] ቤተ መንግስት ገብቶ: ወገቡን ታጥቆ ከንጉሡ ጋር ሲጸልይና ሲሰግድ ያድራል::
Show all...
የአዋጅ ነጋሪ ቃል የአዋጅ ነጋሪው ቃል በበረሃ አየለ የእግዚአብሔርን መንገድ አስተካክሉ እያለ ምስክርነቱን ዮሐንስ ካስረዳ ልባችን ለጌታ መልካም መንገድ ይሁን የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም አውደ አመቱን ባርኪልን ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም ሀገራችንን ባርኪልን ድንግል ማርያም ተራራው ዝቅ ይበል ጠማማውም ይቅና ካልተስተካከለ መንገድ የለምና የእግዚአብሔርን መንግስት እንመስርት ሁላችን ማረፊያ እንዲሆነን ለመጪው ሃብታችን የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም አውደ አመቱን ባርኪልን ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም ቤተክርስቲያን ጠብቂ ድንግል ማርያም ክፋትና ተንኮል ከልባችን ይጥፋ ጽድቅና ርህራሄ በኛ ላይ ይስፋፋ ሥጋና ደምህን በክብር አግኝተናል ህይወት እንዲሆነን አምላክ ተማጽነናል የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም አውደ አመቱን ባርኪልን ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም ሀገራችንን ጠብቂ ድንግል ማርያም ሁለት ልብሶች ያሉት ከማብዛት ልብስን ለሌለው ያድለው  ሁለተኛውን ከበደላችንም አንጻን አደራህን በክፉ እንዳንጠፋ እኛ ባህሮችህ የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም አውደ አመቱን ባርኪልን ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም ሀገራችንን ጠብቂ ድንግል ማርያም ክፋትና ተንኮል ከልባችን ይጥፋ ጽድቅና ርህራሄ በኛ ላይ ይስፋፋ ሥጋና ደምህን በክብር አግኝተናል ህይወት እንዲሆነን አምላክ ተማጽነናል የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም ቤተክርስቲያንን ጠብቂ ድንግል ማርያም የደናግል መመኪያ የነቢያት ገዳም አውደ አመቱን ባርኪልን ድንግል ማርያም ዘማሪት ፀዳለ ጎበዜ @mazmur2122 @mazmur2122 @mazmur2122
Show all...
የአዋጅ_ነጋሪው_ቃል_ዘማሪት_ፀዳለ_ጎበዜ.m4a11.75 MB
2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
፤ አቤቱ፥ አንተን ታመንሁ፤ ለዘላለም አልፈር። ፤ በጽድቅህ አስጥለኝ ታደገኝም፤ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል አድነኝም። ፤ በጠንካራ ቦታ ታድነኝ ዘንድ አምላክና መሸሸጊያ ሁነኝ፤ ኃይሌ መጠጊያዬ አንተ ነህና። ፤ አምላኬ፥ ከኃጢአተኛ እጅ፥ ከዓመፀኛና ከግፈኛም እጅ አድነኝ። ፤ አቤቱ፥ አንተ ተስፋዬ ነህና፥ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከታናሽነቴ ጀምረህ መታመኛዬ ነህና። ፤ ከማኅፀን ጀምሮ በአንተ ተደገፍሁ፥ ከእናቴም ሆድ ጀምሮ አንተ መሸሸጊያዬ ነህ፤ ሁልጊዜም ዝማሬዬ ለአንተ ነው። ፤ ለብዙዎች መደነቂያ ሆንሁ፤ አንተ ግን ብርቱ መጠጊያዬ ነህ። ፤ አፌን ምስጋና ምላ ሁልጊዜ ክብርህንና ግርማህን እዘምር ዘንድ። ፤ በእርጅናዬ ዘመን አትጣለኝ፥ ጕልበቴም ባለቀ ጊዜ አትተወኝ። ፤ ጠላቶቹ በላዬ ተናግረዋልና፤ ነፍሴንም የሚሹአት በአንድነት ተማክረዋልና፥ እንዲህም አሉ። ፤ እግዚአብሔር ትቶታል፤ የሚያድነው የለምና ተከትላችሁ ያዙት። ፤ አምላክ ሆይ፥ ከእኔ አትራቅ፤ አምላኬ ሆይ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን። መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 71 ቁ1-12  #መልካም_ዕለተ_ሰንበት🙏 @mazmur2122 @mazmur2122 @mazmur2122
Show all...
4👍 1
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.