cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የረሱል ﷺመንገድ ተከታይዎች

አሰላሙ አለይኩም የተከበራችሁ ወንድምና እህቶች የዚህ ቻናል አላማው በዋናኝነት የረሱልصلى الله عليه وسلم መንገድ ማሳየት ነው አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራን https://t.me/+jjHF3FW5JoVhNWM0

Show more
Advertising posts
348
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ተዓላ ወበረካቱሁ ሙሂቦችዬ ሰባሁል ኸይር ሁላቹም♥️ ትናንትና ተራዊህ 23 ወይስ 11? የሚለዉን የተወሠነ አይተን ነበር ዛሬም የተወሠነ የቀጠለ እንይ...! #ሊላሂ_ተዓላ✍ حَدَّثَنَا ابْنُ مَهْدِيٍّ، عَنْ دَاوُدَ بْنِ قَيْسٍ، قَالَ: «أَدْرَكْتُ النَّاسَ بِالْمَدِينَةِ فِي زَمَنِ عُمَرَ بْنِ عَبْدِ الْعَزِيزِ، وَأَبَانَ بْنِ عُثْمَانَ يُصَلُّونَ سِتًّا وَثَلَاثِينَ رَكْعَةً وَيُوتِرُونَ بِثَلَاثٍ» ከዳውድ ቢን ቀይስ እንደተዘገበው እንዲህ ብሏል «በዑመር ቢን ዐብዱልዐዚዝ እና በአባን ቢን ዑስማን ዘመን ዘመን ሰዎች (ተራዊህን) ሰላሳ ስድስት ረከዓህ ከዛም በሶስት ዊትር እያደረጉ ሲሰግዱ አግኝቻቸዋለሁ» قلتُ : وهذا أيضًا إجماع يحكيه رجل ثقة بالاتفاق واسع الاطلاع عن عمل المسلمين لمدة تقرب الربع قرن وهو أفضل قرن في الإسلام بالاتفاق . ፨ይህም ልክ እንዳሳለፍነው ታማኝ የሆነና የሙስሊሞች ተግባር ላይ ሩብ ክፍለ ዘመን ያክል ሰፊ የሆነ ጥናት ያደረገ ሰው(ሰለፍ) የዘገበው ኢጅማዕ፤ ለዚያውም ይህ ዘመን በላጭ የሆነው ክፍለ ለመሆኑ ሁሉም ሙስሊሞች የተስማሙበት ዘመን ➖➖➖➖➖ قال ابن أبي الدنيا في كتاب [فضائل رمضان ] حَدَّثَنَا شُجَاعُ بْنُ مَخْلَدٍ، قَالَ: ثنا هُشَيْمٌ، قَالَ مَنْصُورٌ: أنبا الْحَسَنُ، قَالَ: كَانُوا يُصَلُّونَ عِشْرِينَ رَكْعَةً، فَإِذَا كَانَتِ الْعَشْرُ الْأَوَاخِرُ زَادَ تَرْوِيحَةَ شَفْعَيْن ሀሰን እንደዘገቡት «(ሰለፎች) ሀያ ረከዓዎች ይሰግዱ ነበር፤ የመጨረሻው አስር ቀናትعشر الأواخر በደረሱም ግዜ ተራዊሃቸው ላይ ጥንዶች አድርገው ይጨምሩ ነበር» وقد قال أبو نعيم في [حلية الأولياء] عن الحسن أنه قال " أدركت سبعين بدريًا" فالله الله على تبديع ما كان عليه خير الناس وأفضل القرون!!. አቡ ኑዐይም በሂልየቱል አውሊያእ ኪታባቸው እንደዘገቡት ሀሰን እንዲህ ብለዋል « ሰባ የሚሆኑ የበድር ዘማች ሶሃቦችን አግኝቻለሁ» እናንተ ከ11 ረከዐህ በላይ መጨመር ቢድዓህ ነው የምትሉ ሰዎች ሆይ! እነዚያ ምርጥ ሰዎችና በላጭ ትውልዶች በስምምነት ይሰሩት የነበረን ተግባር ቢድዓ ነበር ከማለት ተጠንቀቁ እባካችሁ በሰለፎቻችናን በተግባራቸው ላይ አላህን ፍሩ ➖➖➖➖➖➖➖     ይቀጥላል...... أسلام عليكم ورحمة الله وبركاته ♥️♥️ يا محب أنبي 🎉🎉🎉🎉🎉 🎀🎀🎀🎀🎀 اللـهـمَّ صَـلِّ وَسَـــلِّـمْ  وَبَارِك ْ عـلـى  نَبِيِّنَـــا  مُحــمَّد ﷺ የቻናሉ አላማ ትክክለኛውን አቂዳ ለዑማ ማስተላለፍ ነው አላህ ያለቦታ ያለነው!!  ቻናላችንን ጆይን ሼር https://t.me/+VnwBZHzxXoU0NDFk
Show all...
🌍الله موجود بلا مكان🌎

أسلام عليكم ورحمة الله وبركاته ♥️♥️ يا محب أنبي 🎉🎉🎉🎉🎉 🎀🎀🎀🎀🎀 اللـهـمَّ صَـلِّ وَسَـــلِّـمْ  وَبَارِك ْ عـلـى  نَبِيِّنَـــا  مُحــمَّد ﷺ የቻናሉ አላማ ትክክለኛውን አቂዳ ለዑማ ማስተላለፍ ነው አላህ ያለቦታ ያለነው!! ቻናላችንን ጆይን ሼር

https://t.me/+VnwBZHzxXoU0NDFk

ሰው ዓይነት ትግል አደረጉ። ግና ሙጃሂዶቹ ዘንድ ባለው ቁርጠኛ ወኔና ጀግንነት ተቀልብሰው በገዛ መሳርያቸው ተገደሉ። ጦርነቱን ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው የመሩት ሰባቱ ጳጳሳት ተገደሉ። ሰባ ሺህ ፈረሰኞች ጳጳስ ፊላድን ጨምሮ ወደ ቀብር ተሸኙ። 25 ሺህ ጦረኞች ቆስለው ተማረኩ። በሃንጋሪ ዋና ከተማ ወታደራዊ ትርኢት ተካሄደ።  ከመካ እስከ መዲና ከእየሩሳሌም እስከ ግብፅ ለታላቁ ሡልጣን ሱለይማን የእንኳን ደስ ያለህ መልእክት ይላኩ ጀመር። የአውሮፓውያን የመስቀል ጦረኞችና የሃንጋሪ ሰራዊት እስከ አሁንም በዚህ ሽንፈት ያቃስታሉ። የመኳንንቱና የቀሳውስቱ መቃብር አሁንም ድረስ ይጎበኛል።     ሙስሊሞች የክብርና የድልን ትርጉም እንዳያውቁ፣ የዚህን ጀግና ሙጃሂድ ታሪክ እንዲሁም የጂሃድ ገድሉን እንዳይረዱ ታስቦ በተዘጋጀው ተከታታይ የሱልጣን ሀሪም ፊልም ላይ የተዛባ ታሪኩን የሚያሳዩት ሱልጣን ሱለይማን ማን እንደሆነ እናውቅ ዘንድ እንደዚህ አይነት ትክክለኛ ታሪኩንና ገድሉን እናንብብ እንማር።    በአላህ መንገድ ሲታገሉ ለተሰው ባሮቹ አላህ ምህረቱን ያጎናፅፋቸው ዘንድ እንለምነዋለን። ከላይኛው ጀነትም ያስፍራቸው። ══════════════════════ ምንጭ:              كتاب روائع من التاريخ الإسلامي   حسن حسين اليماني ╔═══════════════╗ ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት ╚═══════════════╝ ጌታዬ ሆይ! ባልሰራበት እንኳ ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8
Show all...
ደረሳ ነኝ እኔ🌹🌷።

https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8

የጁዱ ቡሽራ የአለሙ ሙሽራ: ╔══════════════════╗       አንድ ዕለት ከሙጃሂዶች ጋር ╚══════════════════╝ ጌታዬ ሆይ! ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑል ወሊድ ሠይፍ የሰላ አድርግልኝ Mahi Mahisho   ይህ ከጀግንነት ከቆራጥነትና ከመስዋዕትነት አንፃር በታሪክ ውስጥ እጅግ አስገራሚው ዘመቻ ነው። በአንዳንድ የአውሮፓ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ ጥያቄን የፈጠረ! ሽንፈታቸውን መቀበል ባልፈለጉ ሰዎች ላይ አለመስማማትን ጥላቻንና መገረምን ያስከተለ ድንቅ የሙስሊሞች ገድል የተስተዋለበት። አዎ! ይህ በየትምህርት ቤቶች ልናስተምረው፣ በየአመቱ ልንዘክረው የሚገባ እውነተኛ የሙስሊሞች የድል ውሎ ነው። ጦርነት ሳይሆን እልቂት ነበር። አውሮፓ ልትረሳው ፈፅሞ አይቻላትም።      እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ1521 ዓመት ዑስማናዊው ኸሊፋ ሡልጣን ሡለይማን አል-ቃኑኒ ከኢስላማዊ  መሪ የሚጠበቅበትን ይወጣ ዘንድ ወደ ሀንጋሪው የወቅቱ ንጉስ ከኢስላም፣ ከግብር አሊያም ከፍልሚያ ሊያስመርጠው አምባሳደርን ላከ። የሱለይማን አልቃኑኒ ልዑክ ከሀንጋሪው ንጉስና ከአውሮጳው መሪ "ቪላድ ኢላላቭ 2ኛ" ጋር ለመገናኘት ወደ ግዛታቸው ዘለቀ። ሃንጋሪ በወቅቱ በአውሮፓ የመስቀል ጦርነትን ለመምራት ሽርጉድ በማለት ላይ ነበረች። ከፊት ተሰላፊ ሆና የምንጊዜውም የሙስሊሞችን ኢምፓየር ገርስሳ ዓለም ላይ መስቀልን ልታነግስ ተዘጋጅታለች። የሙስሊሞች አምባሳደር የሀገሩን መሬት እንደረገጠ በወታደሮች ተከቦ ወደ መሰቃያ ስፍራው ተወሰደ። እጅና እግሩ ተቸንክሮ በመስቀል ግንድ ላይ ተጠፍሮ ታሰረ። በጠላት ሠይፍ አካሉ እየተቆራረጠ ሰውነቱ በእሳት እየተጠበሰ በቁሙ ተሰቃይቶ ይህንን አለም ተሰናበተ።    ይህ ዜን ሡለይማን አል-ቃኑኒ ዘንድ ደረሰ። በንዴት ጦፈ። ከተቀመጠበት ዙፋን ላይ ተነሳ "እኔ በሕይወት ሳለሁ የኢስላም አምባሳደር ይገደላልን?! አውሮፓ ነገ ልኳን ታውቃለች" ሲል ተናገረ። 100,000 እግረኛ ሙጃሂዶችን 350 መድፎችና 800 የጦር መርከቦችን ያቀፈ ሠራዊት አዘጋጀ። ስለኢስላም ብሎም ስለ አንድ ልዑክ መገደል ጦሩን ሊያዘምት ቆረጠ። አዎ እርሱ ሁሉንም የመስቀል ጦረኞች ከጫፍ እስከ ጫፍ የሽንፈትን ፅዋ ያስጎነጨ ድንቅ መሪ! ተዋግቶ ያላሸነፈው ተፋልሞ ያላንበረከከው ኃይል የለም የታላቁ የኡስማኒያ ኺላፋ ጋሻ ነው።     የመስቀል ጦረኞች በቫቲካኑ ሊቀ ጳጳስ ትእዛዝ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ደውል የታጀበ የጦርነት ነጋሪት በመጎሰም አውሮፓን ከጫፍ እስከ ጫፍ አንቅተዋል። "ኑ ለቅዱሱ ጦርነት ተዘጋጁ" የሚለው የማንቂያ ደውል ፍሬ አፍርቶ በርከት ያለ ጦር ተሰባስቧል። ስልጠናውና የአካል ብቃት እንቅስቃሴው ቀጥሏል። የተዋቀረ የተደራጀና የተጣመረ ጦር አዋቅረዋል። ከሃያ አንድ አገሮች ወታደር ተመልምሏል። መላው አውሮፓ ለጦርነቱ በተጠንቀቅ ቆሟል። 200,000 ፈረሰኞች ከነሙሉ ትጥቃቸው፣ 35,000 ሙሉ በሙሉ ብረት ለበስ ፈረሰኞች ተዘጋጅተዋል።   የሙስሊሙ የምንጊዜውም ኃያል ንጉስ ሱለይማን አልቃኑኒ 1000 ኪሎ ሜትሮችን አቆራርጦ የኢስላምን ክብር ለማስጠበቅ የላኢላሀ ኢለላህን ባንዲር ከከፍታው ለማውለብለብ ጉዞ ጀምሯል። በመንገዱ ላይ ያሉትን ከተሞች እየከፈተ ወደፊት ገሰገሰ። ቤልግሬድንና ታዋቂውን የቱላ ወንዝ ከሠራዊቱ ጋር አቋርጦ በሞሃክ ሸለቆ በኩል አልፎ በደቡብ ሃንጋሪና በምስራቅ ሩማንያ ጉዞውን ቀጠል። በቪላድና በቫቲካን ሊቀ ጳጳስ የሚመራውን የተባበሩትን የአውሮፓ ጦር በጥቂት ሰራዊቱ ሊገጥም በመጠባበቅ ላይ ነው።     ብዙ ቁጥር ያላቸው የሮማውያንና የሃንጋሪ የመስቀል ጦረኞች በብረት ለበስ የጦር ልብሳቸው መሸፈናቸው ሱለይማንን አስጨንቆታል። እነሱን በጦር ወግቶ መግደል ከባድ መሆኑን ተረድቷል። ብረት ለበስ ናቸውና ምን አይነት መፍትሄ ያብጅ? ለሊቱን ሙሉ ሲጨነቅበትና ሲያሰላስልበት አድሯል።     ጎህ ቀዶ የሱብሂ ሰላት እንዳበቃ በወታደሮቹ ፊት ለፊት ቆመና ዙርያቸውን ቃኘ። በብረት የታሸጉትን የአውሮፓ ሰራዊቶች ተመለከተ። መጨረሻቸው አይታይም። ሰልፍ ሰርተው ቆመዋል። የትየለሌ ናቸው። የሙስሊሞች ጦር ከባድ ጦርነት እንደገጠመው ተረዳ። በለቅሶ ታጅቦ ሰራዊቱን መከረ። እያለቀሰ ተናገረ "ዛሬ እስልምና ከባድ ፈተና ተጋርጦበታል። ሙስሊሞችን ቀና ማድረግ የእኛ ኃላፍትና ሆኗል። እስከመጨረሻው የደም እንጥፍጣፊ በአላህ መንገድ ለመፋለም ተዘጋጁ" አለና ወደመሬት አቀርቅሮ አነባ። እንባውን እየጠረገ የያዘውን ብትር ጠበቅ አድርጎ "እናንተ የአላህ ባሮች ሆይ! በፅናት ተዋጉ ጠላት ሊያጠፋችሁ አሰፍስፏል አላህም ሊረዳችሁ ቃል ገብቷል"  እጁን ወደ ሰማይ ከፍ አድርጎ "አላህ ከእኛ ጋር እስካለ እኛን የሚያሸንፍ የታለ? አላሁ አክበር" አለ። ሰራዊቱ ተክቢራውን ተቀብሎ በጀመዓ አስቀጠለ። ተራሮችም የአላህን ስም ሰምተው ኖሯልና በእሱ መንገድ የተውሂድን አርማ ይዘው ለወጡ ሙጃሂዶች እኛም ብርታት እንሁናቸው በማለት ድምፃቸውን ተቀብለው አስተጋቡ።    ሁለቱ ጭፍሮች ተሰልፈዋል። ሡለይማን ሠራዊቱን በ3 ረድፎች ከፍሎታል። በ10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አስቀምጧል። ዱዓቶች ከፊት፣ ቀለል ያሉ ቁጥራቸው ያልበዛ ፈረሰኞችን በሁለተኛው ረድፍ አድርጓል። ከእነርሱ ጋር በጎ ፈቃደኞችና እግረኛ ወታደሮችን አሰልፏል። ዑለማኦች ብርቱ ጦረኞችና ራሱ ሱለይማን በመጨረሻው ረድፍ ላይ በተጠንቀቅ ቆመዋል።   ከአስር ሰላት በኋላ ከወደ መስቀል ጦረኞች ጥቃት ተሰነዘረ። ታላቁ ሱለይማን የፊት ተሰላፊ ኃይሎች ለጥቂት ሰዓታት ጸንተው እንዲቆዩ ከዛም እንዲሸሹ አዘዘ። ሁለተኛው ረድፍ ላይ ያሉት ፈረሰኞች ከመጀመርያዎቹ ጋር ከነእግረኛ ጦሮቻቸው መስመሩን ከፍተው ወደ ኋላ ሳይሆን ወደ ጎን እንዲሸሹ አዘዘ።     በእርግጥም እነዚያ የመጀመርያ መስመር ላይ ያሉ ጀግኖች ፀንተው ጥቃቱን ተቋቋሙ። ቆሰሉ። ደሙ። በርካቶችም ሞቱ። የበዙ መሻኢኾች ተሰው። ድል የትልቅ ሰውን ደም ትፈልጋለችና እየደሙ እየሞቱ በትዕግስት ፀኑ። እስከ ሃያ ሺህ የሚገመቱ የመስቀል እግረኛ ጦረኞችን ጥዋት ተቋቁመው ሳይበገሩ በሰብር ቆሙ።   ከአይናቸው በስተቀር ሙሉ አካላቸው ከተሸፈኑ የአውሮፓውያን ብረት ለበስ 60 ሺህ የመስቀል ፈረሰኞች ጋር ተፋጠጡ። የመሸሺያው ቅፅበት ደረሰ። መስመሮች ተከፈቱ። ወደ ጎን ይሮጡ ጀመር። እግረኞችም ተከተሏቸው። ሰል መሐል ለመሐል ተሰነጠቀ።    የሙስሊሞች ጦር መሐሉ ሙሉ በሙሉ ክፍት ሆነ። የመስቀል 100,000 ሺህ ፈረሰኞች በቅፅበት ወደ ሙጃሂዶቹ ሲገሰግሱ ከሙስሊሞች መድፍ ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጡ። ከየአቅጣጫው የሚፈነዳው መድፍ በፈረሰኞቹ ላይ ያርፍ ጀመር። ሙሐመድ አልፋቲህ ቆስጠንጢኒያን ሲከፍት የተጠቀመው መድፍ ለአንድ ሰዓት ያህል ያለማቋረጥ ተተኮሰ። የአውሮጳውያን የመስቀል ጦር አብቅቶ ታሪክ ሆኖ ቀረ። በርካታ ቀሳውስት ወደ ቀብር ተሸኙ። ከነመስቀል ልብሳቸው ጳጳሳቱ ተገደሉ። ከኋላ የተሰለፉ በሺዎች የሚቆጠሩ የመስቀል ጦረኞች ወደ አል-ታውላ ወንዝ ለማምለጥ ሲሞክሩ እርስ በርሳቸው እየተረጋገጡ ብረት ለበስ ጭንብላቸውን እንዳጠለቁ ሰምጠው ይህን አለም ተሰናበቱ። የአውሮፓ ጦረኞች እጅ መስጠት ፈለጉ። ግና አውሮፓ እስከ አሁን የማትረሳውን ውሳኔ ሱለይማን አስተላለፈ "ይቅርታችን ስለበዛ መስቀለኞች ኢስላምን ለማጥፋትና ሙስሊሞችን ለማሰቃየት ተነሱ። ለሌሎችም መማርያ ይሆን ዘንድ በዚህ ጦርነት አንድም የመስቀል ጦረኛ እንዳይተርፍ። ይህ ስለኢስላም የሚከፈል መስዋዕትነት ነው" ሲል አዘዘ። በእርግጥም ተስፋ የቆረጠ
Show all...
Photo unavailable
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ ውድ የአኼራ ወንድምና እህቶቼ ዛሬ አንድ ነገር ይዤላችሁ መጥቻለው እሱም ስለደጃል ታሪኽ ነው ዱንያ ላይ እንደሱ ፊትና የለም የተባለው ፍጡር ነው ስለሱ ታሪኽ ለማግኘት ፈጥነው ይቀላቀሉ👇👇
Show all...
መሱሁ ደጃል
አስመሳዩ ፍጡር
Photo unavailable
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ ውድ የአኼራ ወንድምና እህቶቼ ዛሬ አንድ ነገር ይዤላችሁ መጥቻለው እሱም ስለደጃል ታሪኽ ነው ዱንያ ላይ እንደሱ ፊትና የለም የተባለው ፍጡር ነው ስለሱ ታሪኽ ለማግኘት ፈጥነው ይቀላቀሉ👇👇
Show all...
መሱሁ ደጃል
አስመሳዩ ፍጡር
ሀስቢየሏሁ ወኒእመል ወኪል!! ወረኛውም ያውራ ሸይጧኑም ይሸርብ ውሻውም ይጮሃል ግመሉም ይጓዛል!! ሁሉም ለየፊናው ነው!! ይህም ብርቱ የብእር ምክር ለሙእሚኖች ተስፋን ሰነቀ!! ኡስታዝ ሂዝበሏህ!! ክፍል 1 ይህ በአይነቱ ለየት ያለ የቀልብ ዶክተር ኡስታዞች አቋም መግለጫ ፅሁፍ ነው!! እነሆ ስለኛ ሃቁን ታውቁ ዘንድ አንድ ግዜ ጥያቄዎችን ሰብስበን ምላሽ እንሰጥበት ዘንድ በኔ በወንድም ሂዝቡላህ ተጠናቅሮ የቀረበ ነው!! በቀልብ ዶክተር ኡስታዞች መታከም ትፈልጋላችሁ? እውቀትን መሸከፍ ትፈልጋላችሁ? እነሆ ከዚህ ኋላ የቀልብ ዶክተር ኡስታዞች አቋም ይህ ነው!! ይህን ሳያውቁ አበደን ወደ ህክምናችን እንዲቀላቀሉ አንሻም!! አልሃምዱሊላህ በዚህ ዘመን ዳይመንድ የሆነን እድል አግኝተናል!! አልሃምዱሊላህ ሱመ አልሃምዱሊላህ እርሶ ከኛ ጋር ተቀላቅለው እውቀት እየቀሰሙ እየታከሙም ነው!! አጅሩንም ከሚነሏህ ለማግኘት ለሌላው እያደረሱ ነው!! ይሁንና በዚህ መሃል የሸይጧን አምባሳደሮች፣ሷሂሮች፣በሩቅያህ ሰበብ የሴት እህቶቻችንን ቀሚስ ለማስወለቅ የጣሩ ጋጠወጦች፣ ብሎም እነርሱ ድነው ቤተሰቦቻቸው ታክመው ድነው ኡማው እንዳይድን እንቅፋት መሆንን ለሚሹ ደም ቀቢ የሸይጧን ጭፍሮችን ስራ ስለሚያኮላሽ የነርሱን ሴራ ስለሚያከሽፍ እርሶንም (አይ አይደለም እኔ የማውቀው ይህን ነው!!) ብለው በድፍረት ስለኛ ለመናገር እንዲረዳዎት ዘንድ እነሆ!! ከሁሉ በላይ በቅድምያ ከምንም በላይ ይህን ይወቁ (አሏህ ያድናል፣ ማንም ምንም አያድንም) !! ****የሚሰራ ሙእሚንም ይወራበታል ሂስንም ያስተናግዳል!! ታድያ በምንስ አጅር ያግኝ****** እነሆ በዚያ የሸይጧን ጭፍሮችን አንገት በሚሰላው ብርቱ ብእር በአሏህ እገዛ ላይ ተንተርሰን የማያዳግም ምላሽን ሰጠን ቢስሚሏህ!! ጥያቄ 1.እናንተ ምንድናችሁ? መልስ!! ሱብሃነላህ ወላሂ ወቢሏሂ እጅግ ከሚያስቆጣን ጥያቄ አንዱ ይህ ነው!! ሙስሊም ሆነው በላኢላሃ ኢለላህ የሚያምኑ የምንላቸው ሰዎች ቀድመው ምንድናችሁ አቂዳችሁ መንሃጃችሁ ምንድነው? ፈገግም እንላለን!! በዚያ ሸይጧን ጭንቅላታቸውን በእብሪት ለሞላላቸው ሰዎች እነሆ አሁን ዛሬ መልስ ሰጠን!! እወቁ አዋጅ አዋጅ አዋጅ፡- እኛ ሙስሊሞች ነን!!! ሙስሊምም ሆነን መሞትን መረጥን መንሃጃችን መንሃጀ ረሱል ሙሃመዱን አሚን ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ነው፡፡ አቂዳችን አቂደቱ ረሱል አል ሙስጠፋ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ነው!! ለኛ ቁርአን እና ሰሂህ ሀዲሶች ብቻ መመርያዎቻችን ናቸው!! ሰሃባዎች ኮከቦቻችን ናቸው!! ሰለፈ ሷሊሆች እነኛ ቀደምቶቹ መምህሮቻችን ናቸው!! ታቢኢኖች ታቢኢ ታቢኢኖች ሳይበረዝ ያወረዱልንን ሀቅ አንፀባራቂዎች ነን!! ---ወሀቢይ በለን ---ሱፊይ በለን ብሎም ደሞ ደስ ካለህ ---ሺኢዮች በለን!! ሁሉም እንደ አረዳዱ!! የቄሳርን ለቄሳር!! እኛ ግን ሙስሊሞች ነን ይሰማል!! --- ሙ ስ ሊ ሞ ች ነን!!--- አልሃምዱሊላህ!! አንተ/አንቺ የሰው ልጅ ብቻ ሁን አሏህ አዳኝ ነው ብሎ ለመጣ ሰው ፈፅሞ በአቂዳው በእምነቱ በአስተሳሰቡ ህክምናን አንከለክልም፡፡ ለሁሉም ህክምናን እንሰጣለን፡፡ ‹‹ሊበሏት ያሰቧትን ምን….ጅግራ ናት ይሏታል..›› ነውና ኡማውን ለመከፋፈል የሚተጉትን በዚሁ መለስን ከዚህም እንከን ፈላጊዎችን አናጣም፡፡ ግና ካልተረዱን የተረዱን እጅግም ብዙ ናቸው፡፡ ጥያቄ 2.እናንተ በጅኖች ጅንን ታወጣላችሁ ወይ? ከጅኖች ጋር ግንኙነት አላችሁ ወይ!? ይህች የሰሞነኛው የቲክታከሮች ፈትዋ እንዳትሆንብን ፈራን (፡ (፡ (፡ 👉እኛ በጅኖች ጅኖችን አናወጣም። በሲህርም ሲህርን አናክምም በፍፁም! ይህም ከሽርክ ነው!! 🤲ህክምናችን በቁርአንና በዚክር ብቻና ብቻ ነው!! የሸይጧን አምባሳደሮች ሆይ!! ሷሂሮች ሆይ!! ግዜያችሁ አበቃ!! ለኛ አሏህ ብቻ ነው ያለን!! የጅኖችንም እርዳታ አንሻም እርዳታችን ከአላህ ብቻና ብቻ ነው!! ጅኖች ውሸት ብቻ ነው ሚያወሩት ለሚሉ ባለ ቀቢፅ እውቀቶች ግን እንዲህ መልስ ሰጠን። ለዚህም ሰሂህ ሀዲሶች ብቻ መወጣጫ ሆኑን!! እወቁ አዋጅ አዋጅ አዋጅ፡- ሸይጧኖች ውሸታም ካዚቦች ናቸው!! ይህ ሀቅ ነው! ግና ሃቅን አያወሩም አውርተውም አያቁም ያለ በራሱ ካዚብ ውሸታም ነው!! ጅኖች አታላይ ብልጣ ብልጦች ናቸው! ይህም ሀቅ ነው። እውነትን አይናገሩም ያለ ግን ረሱልን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን ውሸታም ብሏል ወደ እስልምናው ይመለስ!! ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጅኖች ከዛም ባለፈ ሸይጧኖች ሳይቀሩ ሃቅ እንደሚያወሩ ግና ውሸታሞች መሆናቸውን የተነተኑበትን ሃዲሶች እነሆ!! በጉጉት ለምታነቡን ልብ ብላችሁ በፅሁፋችን እንደ ማር የጠራችን እውቀት ቅሰሙበት፡፡ አልሃምዱሊላህ አላ ኒእመቲሏህ እውነትም በመጣች ግዜ ውሸት ወደቀች እነሆ ውሸት ምንግዜም ወዳቂ ናትና!! አኢሻ መልካም ስራዋን ይውደድላትና እንዲህ አለች ‹‹ረሱል ሰለሏሂ አለይሂ ወሰለምን አንዳንድ ሰዎች ጠየቁ ስለ ሷሂሮች (የፊተኛውን ስለሚተነብዩ) ሰዎች፡፡ ረሱልም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እዲህ አሉ ‹‹ እነርሱ ማለት ምንም ማለት ናቸው!! ምንም አቅምም ሃይልም የላቸውም!!›› ጠያቂዎችም ጥያቄያቸውን አስከተሉ እንዲህም አሉ ‹‹አንቱ የአሏህ መልእክተኛ ሆይ አንዳንዴ እኮ የሚነግሩን ነገሮች እውነት ይሆናሉ!!›› ሲሉ የአሏህ መልእክተኛም እንዲህ አሉ ‹‹ ጅን እኮ እውነታውን ሃቁን በ ሷሂሩ ጆሮ ስር (በጓደኛው ጆሮ ስር) ያስቀምጣል፡፡ ልክ አንድ ሰው አንድ ሰው ብልቃጥ አልያም ጠርሙስ ውስጥ አንዳችን ነገር እንደሚያስቀምጥ ነገር፡፡ ያም ይህ ሷሂር (የፊተኛውን ተንባይ) ያቺን እውነት (የጅኑን ቃል) ይዞ በብዙ ውሸት ውስጥ ያንከላውሰዋል ያደባልቀዋል፡፡›› መፅሃፍ 71 ሃዲስ ቁጥር 657 ወገኔ ሰሂህ ሀዲሶች ብቻ በቁን ስንል እኮ ከልባችን ነው!! ረሱልም ሃቅ ተናገሩ!! ጅኑ አልዋሸም ያ ጠንቋይ ቢዋሽ እንጂ፡፡ ጅኑም እውነቱን ለእኩይ ነገር ተጠቀመበት፡፡ ከሀዲሱ ምን እንማራለን? ይህን ለናንተ ለአንባብያን ልንተው ፈለግን ግና የሸይጧን ባለሟሎች እንከንን ፈላጊ ናቸውና እንደ ሷሂሩ እውነታውን ከብዙ ውሸቶች ጋር ከመቀላቀላቸው በፊት እናብራራላችሁ፡፡ ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንደተናገሩት አይሻ እንደሰማችው ጅኑ እውነት ይናገራል ተናግሮም ሳሂሩ ግን ከውሸት ጋር ይደባልቀዋል!! ውሸቱን ግን የሚቀላቅለው ይህ ሷሂር ነው፡፡ አሏሁ አክበር እነሆ የሸይጧን አምባሳደሮች እውነትን ከብዙ ውሸት ጋር የሚቀላቀሉት በዚህች ሰአት ተዋረዱ!! ሌላም ሃዲሶች አሉን ይቀጥላሉ…. እውቀትን ለፈለገ እውቀትን እስከ አፍንጫው እናስታጥቃለን፡፡ እኛ አጥፊዎች ወንጀለኞች እና ደካማ የአላህ ባሮች!! ዝም ስንል ሃቁን ማውራት አቅቶን ሳይሆን ክርክርን ለአሏህ ስንል ለመራቅ ነው፡፡ ይህን ግን እውቀትን ብቻ ለመስጠት ተጠቀምነው!! ወደ ቀጣዩ ሃዲስ እናምራ!! እነሆ በደምብ እውቀትን ቅሰሙ!! ይቀጥላል!! https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8 https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8
Show all...
ደረሳ ነኝ እኔ🌹🌷።

https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8

ከሸዕባን ወር ትሩፋቶች... https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8
Show all...
ከሸዕባን ወር ትሩፋቶች.mp38.56 MB
00:23
Video unavailable
رحم الله شيخنا الإمام المحدث الشيخ عبد الله الهرري رحمة واسعة وجزاه عنا خير الجزاء. غاب الجسد وبقي النهج https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8 https://t.me/+g-H-DJ4TBOsyNjA8
Show all...
2.17 MB
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.