ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ግጥሞች
ይህ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርትን የምንማማርበት Channel ነው ! ወደ ቻናላችን በመቀላቀል 👇 ➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መፅሐፍትን በPDF ➲ስንክሳር ትምህርቶች ➲ መዝሙራትን ➲ ግጥሞች ➲ ፊልሞችን ➲ ጥያቄዎችን በሐይማኖት ብትኖሩ እራሳችሁን መርምሩ" ( 2ኛቆሮ -13 ፥ 5)👇 Group ገጽ👇👇 https://t.me/Orthodoxs_Tewahdo_menfeswi_group
Show more14 378
Subscribers
-6024 hours
+1507 days
+1 08230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
Photo unavailableShow in Telegram
💠የሽብሻቦ መዝሙሮች💠
💠የንስሐ መዝሙሮች💠
💠የቅዱሳን መዝሙሮች💠
💠የመላእክት መዝሙሮች💠
💠የሰማዕታት መዝሙሮች💠
💠የሃዋርያት ሙዝሙሮች💠
💠የሠርግ መዝሙሮች💠
💠የንግስ መዝሙሮች💠
💠ለወቅታዊ መዝሙሮች💠
💠ሁሉንም መዝሙሮች💠
Show all...
💕ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር
💕ኦርቶዶክሳዊ ስብከት
💕ኦርቶዶክሳዊ ዜናዎች
💕 ቃለ ስብሐት
💕 ሁ ሉ ን ም ባ ን ድ ላ ይ 💕
Photo unavailableShow in Telegram
†
† 🕊 ቅዱስ መስቀል 🕊 †
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
---------------------------------------------------
ጌታችን መርገመ ሥጋንና መርገመ ነፍስን አጥፍቶ ድኅነተ ምዕመናንን የፈጸመው በዕፀ መስቀል ላይ ነው። { ገላ ፫፥፲፫ ፣ ኤ.፪፥፲፬-፲፯ ፣ ፊል ፪፥፰ ፣ ዕብ ፲፪፥፩-፪ } ይኽም መስቀል የክርስቶስ ኃይሉ የተገለጠበትና በደሙም የከበረ ነው። { ፩ኛቆሮ. ፩፥፲፰ }
ጌታችን በዚህ መስቀል ዲያቢሎስን ድል ካደረገው በኋላ እኛም ድል እያደረግነው እንድንኖር ኃይላችን የሆነውን መስቀል አስታጥቆናል። { ኤፌ.፪፥፲፮ }
በመሆኑም እንደ ሐዋርያው እንደ ቅዱስ ጳውሎስ በመስቀሉ እንመካለን። { ገላ.፮፥፲፬ } መመካትም ብቻ ሳይሆን የጌታችን እግሮች ለድኅነተ ምዕመናን በችንካር ላይ ቆመው ለዋሉበት ለክቡር መስቀሉ እንሰግዳለን። ምክንያቱም ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በትንቢት ፦ ”እግሮቹ በሚቆሙበት ሥፍራ እንሰግዳለን" ብሎአልና፡፡ { መዝ.፩፻፴፩፥፯ }
በዚህም መሰረት ቤተ ክርስቲያን ከፍ አድርጋ በጉልላቷ ላይ የተከለችውና ዕለት ዕለትም ካህናት በክርስቶስ ስም ምዕመናንን የሚባርኩበት ቅዱስ መስቀል የሚሰብከውና የሚናገረው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
🕊
† † †
🌼 🍒 🌼
🕊
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †
[ † መስከረም ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
† 🕊 በዓለ ስዕለ አድኅኖ 🕊 †
ይህች ቀን በቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱሳት ስዕላት የሚነገርባት ክብርት ቀን ናት:: 'ስዕለ አድኅኖ' ማለት 'እግዚአብሔር በረድኤት የሚገለጥበት: አንድም በቅዱሳኑ አማካኝነት ጸጋ የሚገኝበት: የሚያድን ስዕል' ማለት ነው::
ስለዚህ ነገር አንዳንዶቹ ሊነቅፉን ይፈልጋሉ:: እኛ ግን ከማን እንደ ተማርነው እናውቃለን:: ከመነሻው እኛ ስዕልን አናመልክም:: ይልቁኑ አምልኮን እንፈጽምበታለን እንጂ:: ስዕልን ለሰው ልጆች የሰጠ ራሱ ባለቤቱ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይመሠክራል::
እንዲያውም የመጀመሪያው ሰዐሊ ራሱ አምላካችን ነው:: አዳምን እንደ መልኩ: በምሳሌው ሲፈጥረው መላእክት የእግዚአብሔርን ምስል አዳም ላይ አይተዋልና:: [ዘፍ.፩፥፳፮] (1:26) ለሙሴም ስዕለ ኪሩብን እንዲስል ያዘዘ ራሱ ነው:: [ዘጸ.፳፭፥፳፪] (25:22) በዚያም ላይ ሆኖ ሙሴና አሮንን ሲነጋገራቸው ኑሯል::
በመቅደሰ ሰሎሞንም ተመሳሳይ ነገርን እናገኛለን:: [፪ዜና.፯፥፲፪] (7:12) , ፩ነገ.፱፥፩] (9:1) በሐዲስ ኪዳንም ጌታ ስዕለ ኪሩብ ያለበትን መቅደስ ቤቴ [ማቴ.፳፩፥፲፫] (21:13): የአባቴ ቤት [ዮሐ.፪፥፲፮] (2:16) ሲለው: በቅዱስ ሰውነቱ ሲመስለውም [ዮሐ.፪፥፳፩] (2:21) እንመለከታለን:: ቅዱስ ዻውሎስ ለገላትያ ሰዎች ስለ ስዕለ ስቅለት ሲያስታውሳቸው [ገላ.፫፥፩] (3:1): ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ በደም የተረጨች ልብስ ብሎ ያላትን መተርጉማን ያትታሉ:: [ራዕይ.፲፱፥፲፫] (19:13)
በትውፊት ትምሕርት ደግሞ የመጀመሪያው ስዕል በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ የተሳለ ሲሆን ስዕሉም የእመቤታችን ነው:: "ሚካኤል በክነፊሁ ጾራ መንጦላዕተ ደመና ሠወራ" እንዳለ ቅዱስ ያሬድ:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአቃርዮስና ለቬሮኒካ ፲፪ [12] ዓመት ደም ይፈሳት ለነበረችው ሴት) መልክአ ገጹን ሠጥቷቸዋል::
['ቬሮኒካ' በላቲን 'ቬሮን-ኢኮን' 'እውነተኛ መልክ' እንደ ማለት ነው]
ቀጥሎም ዮሐንስ ወንጌላዊ ለጢባርዮስ ቄሣር ስዕለ ስቅለቱን ሲስልለት ቅዱስ ሉቃስ ደግም የእመቤታችን 'ምስለ ፍቁር ወልዳን' ስሏል:: ከዚያም ሲያያዝ ይሔው ከእኛ ደርሷል::
ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በከተሞች አካባቢ ቅርጾች በዝተዋልና ይሔ አላስፈላጊ መዋስ [ያውም ከመናፍቃን] ቢቀር መልካም ነው ባይ ነኝ:: ኋላ ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቁሞ ማውረድ ከባድ ነውና::
† 🕊 ጼዴንያ 🕊 †
በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው: ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር [በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል] ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት::
ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም:: ተግታ ታገለግላትም ነበር:: ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር:: [እርሱ ምን ያድርግ! እኔም ብሆን ይህንኑ ነበር የማደርገው]
ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር: በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች:: ይህቺ ክብርት ስዕለ አድኅኖ የአሁን መገኛ 4 መረጃዎች አሉ:-
፩. ያለችው ኢትዮዽያ ውስጥ [ደብረ ዘመዳ በሚባል ገዳም] ነው:: የመጣችውም ከግማደ መስቀሉ ጋር ነው::
፪. ያለችው በቀደመ ቦታዋ ነው::
፫. የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ወስደዋታል::
፬. በፈጣሪ ጥበብ ተሰውራለች::
† 🕊 ልደታ ለማርያም 🕊 †
በግብጽ ውስጥ ከሚገኙ ገዳማት በአንዱ: ማለትም በአስቄጥስ ደብረ አባ መቃርስ የእመቤታችንን ዜና ሕይወት የሚናገር ፩ [1] መጽሐፍ አለ:: መጽሐፉ እንደሚለው እመ ብርሃን ድንግል ማርያም የተጸነሰችው ታሕሳስ ፲፯ [17] ቀን ነው:: በዚህ ሒሳብ መሠረት ደግሞ እመ አምላክ የተወለደችው መስከረም 10 ቀን ነው:: ዓለማቀፍ ትውፊቱ ግን ነሐሴ ፯ [7] ተጸንሳ: ግንቦት ፩ [1] ቀን መወለዷን ያሳያል::
† 🕊 ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል 🕊 †
'ተቀጸል ጽጌ' ማለት 'መስቀል ሆይ! በአበባ አጊጥ' እንደ ማለት ሲሆን 'አጼ መስቀል' ደግሞ አጼ ገብረ መስቀልን: አንድም አፄ ዳዊት ቀዳማዊን ይመለከታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
በሃገራችን ኢትዮዽያ የነገረ መስቀሉ ትምሕርት ከመጣ ጀምሮ መስቀል ይከበራል:: በአደበባባይ ግን እንዲከበር ያደረጉት የቅዱስ ካሌብ ልጅ አፄ ገብረ መስቀል ናቸው:: በወቅቱ ንጉሡ: ሠራዊቱ: ዻዻሱና ሕዝቡ በተገኙበት ቅዱስ ያሬድ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር-መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው: ከጠላትም ያድነናል" እያለ ይዘምር ነበር::
የአበባ ጉንጉንም ለመስቀሉና ለንጉሡ ይቀርብ ነበር:: ከ፰፻ [800] ዓመታት በሁዋላም አፄ ዳዊት ግማደ መስቀሉን ባስመጡ ጊዜ መስከረም ቀን ተተክሎ ታላቅ በዓልም ሆኖ ተከብሯል::
† 🕊 ንግሥተ ሳባ 🕊 †
ይሕቺ ደግ ኢትዮዽያዊት ከ፫ [3] ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት:: በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች::
ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች:: ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ምኒልክን ወልዳለች:: ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች:: [ማቴ.፲፪፥፵፪] (12:42) በስምም "ሳባ: አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች:: ዛሬ ዕለተ ዕረፍቷ ነው::
እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን: ጸጋ በረከቷን: ከስዕሏም ረድኤት ትክፈለን:: የቅዱሳኑም ክብር አይለየን::
🕊
[ † መስከረም ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም
፪. በዓለ ስዕለ አድኅኖ
፫. ቅዱስ እፀ መስቀል [ተቀጸል ጽጌ]
፬. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
፭. ቅድስት ማርታ ዘጼዴንያ
፮. ቅድስት ዮዲት ጥበበኛዋ
፯. ንግስተ ሳባ / ማክዳ / አዜብ
፰. ቅድስት መጥሮንያ ሰማዕት
፱. አፄ ዳዊት ንጉሥ
፲. ቅድስት አትናስያና ፫ [3] ልጆቿ
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሜራ
፫. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፬. ቅድስት እሌኒ ንግስት
፭. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
" የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ! በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተስሎ ነበር:: ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው ? " [ገላ.፫፥፩] (3:1)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍 1
🤑💵 🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 𝗧𝗿𝗮𝗱𝗶𝗻𝗴 መማር የምትፈልጉ የሚገርም የ Forex ቻናል ያውቃሉ❓
💶 𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 💶
@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር የምትፈልጉ አናግሯቸው እስከ 𝟰𝟬% Discount የሚደርስ ቅናሽ አድርገዋል !
☎️ +251977338586 🇪🇹
☎️ +251977338586 🇪🇹
ይህን ይጫኑት ይህን ይጫኑት ይህን ይጫኑት
👇👇 ይህን ተጭነው መመዝገብ ይችላሉ !👇👇
❎█▓▒░ ►OPEN◄░►OPEN ▒▓█❎
❎█▓▒░ ►OPEN◄░►OPEN ▒▓█❎
❎█▓▒░ ►OPEN◄░►OPEN ▒▓█❎
❎█▓▒░ ►OPEN◄░►OPEN ▒▓█❎
💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸💸
👆 ይህን ይጫኑት ይህን ይጫኑት ይህን ይጫኑት 👆
🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬
🇫 🇴 🇷 🇪 🇽 🇹 🇷 🇦 🇩 🇮 🇳 🇬
🎯 𝗔𝗱𝗱 𝗬𝗼𝘂𝗿 𝗖𝗵𝗮𝗻𝗻𝗲𝗹 ➕
👇 ምርጥ ምርጥ ቻናሎችን ከፈረጉ ከስር ያለውን ይጫኑ 👇
👆 ምርጥ ምርጥ የ Telegram ቻናሎች 👈
❤️ መንፈሳዊ የ Telegram ቻናል ስብስብ ❤️
Free FaceSwap🤖
Free UndressBot🙈
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.