የኦርቶዶክስ አስተምህሮዎች
በዚህ Channel ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፤ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ ትምህርቶች ይተላለፉበታል፡፡ ለአስተያየት: ጥቆማና ጥያቄ በዚህ ያግኙን ☞ @Ethiopian_Orthodox_bot Buy ads: https://telega.io/c/Ethiopian_Orthodox
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
አንድ ወንድሜ ያጫወተኝን ታሪክ እነሆ ልበላችሁ👇👇 ድሬዳዋ በምኖርበት ሰአት እናቴ የንዋየ ቅዱሳን መሸጫ ሱቅ ነበራት እናም ምትሸጥበት ቤተክርስቲያን መድሃኒያለም ቤተክርስቲያን ነው እና አንድ እናት ሁሌ መሬት መሬት እያዩ ይዞራሉ ታዲያ አንድ ቀን ከ መሬት ቆርኪ እየለቀሙ አየናቸው ጠርተን ለምን እንዲህ እንደሚያደርጉ ጠየቅናቸው መልሳቸውም አባቴ ጊዮርጊስን አረከሱት በስእሉም ተጫወቱበት ብለው እስከዛሬ የሰበሰቡትን የጊዮርጊስ ቢራ ቆርኪ አሳዩን። 😞😞😞😞😞😞😞😞😞 ልብ አድርጉልኝ ክርስቲያኖች እኚህ እናት ምን ያህል የቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕትነትና ቅድስና እንዲሁም ምልጃና በረከቱ ውስጣቸው ዘልቆ እንደገባ ። ቅዱስ ጊዮርጊስ በብዙ ተጋድሎ ያገኘውን ቅድስናና ክብር ለረከሰ ነገር ማዋላችን ምን ያህል እንደሚያስጠይቀን አታውቁምን? ለሰማዕቱ ቤተክርስቲያን ይሰሩለታል፣ ታቦት ይቀርጹለታል እንጂ ቅዱስ ስዕሉን በየቢራው ጠርሙስ ላይ እየለጠፉ እንዴት ለረከሰ ቦታና ለረከሰ ምግባር ያውሉታል? እጅግኑ የሚገርመኝ ደግሞ ተጠቃሚዎቹ እኛው አዋቂዋቹ ማህበረ ክርስቲያን መሆናችን ነው። ወዳጆቼ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለእምነታችን ታግለን ገድል ባናጽፍ እንኳን ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ይህን እኩይ ተግባር መቃወም መቻል አለብን። " ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1:10) እነሆ እኔ አንድ ብዬ ተነስቻለሁ ይህንን ጽሑፍ ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ። @Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
💠የመንፈስ ፍሬዎች💠✝️ "የመንፈስ ፍሬ ግን:ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።"ገላ 5÷22
፩.ፍቅር✞ በክርስቲያናዊ ሕይወት ከሁሉም የመንፈስ ፍሬዎች የሚቀድመውና የሚበልጠው የመንፈስ ፍሬ ፍቅር ነው።ምክንያቱም፤ ፍቅር የእግዚአብሔር ባሕርይ ስለሆነ ነው 1ዮሐ. 4:16 ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ስለሆነ ነው ሮሜ. 13.8 ማር. 12:28 ✞ የእግዚአብሔር ቃል ይህንን ሲያስረዳ እንዲህም ከሆነ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር፣ እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ከነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው ይላል 1ቆሮ.13:13፡፡ በሌላ ክፍል ፍቅርን “የፍጻሜ ማሰሪያ”ብሎታል ቆላ.3:14፡፡ ስለዚህ ክርስቲያኖች ከሁሉ የሚበልጠው ይህ የመንፈስ ፍሬ እንዲታይባቸው እግዚአብሔርንም ሰውንም ከልብ ሊያፈቅሩ ይገባቸዋል፡፡ ሌሎቹን የመንፈስ ፍሬዎች ከማሰባችን በፊት ፍቅር ሊኖረን ፍቅርን ልንከታተል ያስፈልጋል 1ቆሮ.14:1፡፡ ✞ ፍቅር የአንዱን ድካም አንዱ ሲሸከም ነው። ሰማዕትነት የሌለበት ፍቅር ፍቅር አይባልም። በአፍ ብቻ እወድሃለሁ እወድሻለሁ ማለት ውሸት ነው። ይህንንስ ባላገሩ "የአፍ ዘመድ ከገበያም አይገድ" ብሎ ተርቶበታል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐ. ፲፭፣፲፫ "ነፍሱን ስለወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም" ብሎ የፍቅርን ትርጓሜ አስተማረን። ፍቅር በአፍ የሚናገሩት ብቻ አይደለም በሕይወት የሚኖሩትም ነው እንጂ። ለዚያም ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን በቃል ከተናገረ በኋላ በተግባር ደግሞ አዳምን ለማዳን በመስቀል የተሰቀለ። መስቀል ፍቅር በተግባር የተገለጠበት አደባባይ ነው። ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት ብሎ ሊቁ የገለጠው ይህንን ነው። ፍቅር ራሱ እግዚአብሔር ነው። ፩ኛ ዮሐ.፬፣፰-፳ "ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም እግዚአብሔር ፍቅር ነውና----ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው" ይላል። ይህ የሚነግረን በፍቅር ጥላቻ እንደሌለ ነው። ፍቅር ሌላውን እንደ ራስ መውደድ ነው። ማቴ. ፯፣፲፪ "ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው" ተብሎ እንደተጻፈ ሰውን መውደድ በእኛ ሊደረግብን የማንፈልገውን በሌላውም እንዲደረግ አለመፈለግ ሲሆን እግዚአብሔርን መውደድ ደግሞ ትእዛዙን በመፈጸም ይገለጣል።ዮሐ. ፲፬፣፳፩ "ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው" እንዲል። ✞ ማቴ. ፯፣፳፩-፳፫ "በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። በዚያ ቀን ብዙዎች ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን ይሉኛል። የዚያን ጊዜም ከቶ አላወቅኋችሁም እናንተ አመፀኞች ከእኔ ራቁ ብየ እመሰክርባቸዋለሁ" እንዲል የጌታን ስም ብዙ ጊዜ ብትጠራ፣ በስሙ ተአምራትን ብታደርግ፣ በስሙ ትንቢትን ብትናገር፣ በስሙ አጋንንትን ብታወጣ ይህ የፍቅር ምልክት ተደርጎ አይያዝም። እግዚአብሔርን የመውደድ ዋናው ምልክቱ ፈቃዱን መፈጸም ነው። ፈቃዱ ምንድን ነው ከተባለ ዘጸ. ፳፣፩ ጀምሮ ያሉ አስሩን ሕግጋት መፈጸም ነው። ማቴ. ፲፱፣፲፯ "ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ" እንዳለ። ዮሐ. ፲፪፣፶ "ትእዛዙም የዘለዓለም ሕይወት እንደሆነች አውቃለሁ"እንዲል። ✞ ቅዱስ ጳውሎስ ፍቅርን ጠቅለል አድርጎ ሲያቀርበው እንዲህ ብሎታል። ፩ኛ ቆሮ. ፲፫፣፪-፰ " ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድኾችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። ፍቅር ይታገሣል፣ ቸርነትንም ያደርጋል፣ ፍቅር አይቀናም፣ ፍቅር አይመካም፣ አይታበይም፣ የማይገባውን አያደርግም፣ የራሱንም አይፈልግም፣ አይበሳጭም፣ በደልን አይቆጥርም፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለዓመፃ ደስ አይለውም። ሁሉን ይታገሣል፣ ሁሉን ያምናል፣ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣ በሁሉ ይጸናል። ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም" ብሎ ገልጾታል።
👉'ደስታ' ይቀጥላል ...........@Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
💠የመንፈስ ፍሬዎች💠✝️ "የመንፈስ ፍሬ ግን:ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።"ገላ 5÷22
፩.ፍቅር✞ በክርስቲያናዊ ሕይወት ከሁሉም የመንፈስ ፍሬዎች የሚቀድመውና የሚበልጠው የመንፈስ ፍሬ ፍቅር ነው።ምክንያቱም፤ ፍቅር የእግዚአብሔር ባሕርይ ስለሆነ ነው 1ዮሐ. 4:16 ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍጻሜ ስለሆነ ነው ሮሜ. 13.8 ማር. 12:28 ✞ የእግዚአብሔር ቃል ይህንን ሲያስረዳ እንዲህም ከሆነ እምነት፣ ተስፋ፣ ፍቅር፣ እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፡፡ ከነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው ይላል 1ቆሮ.13:13፡፡ በሌላ ክፍል ፍቅርን “የፍጻሜ ማሰሪያ”ብሎታል ቆላ.3:14፡፡ ስለዚህ ክርስቲያኖች ከሁሉ የሚበልጠው ይህ የመንፈስ ፍሬ እንዲታይባቸው እግዚአብሔርንም ሰውንም ከልብ ሊያፈቅሩ ይገባቸዋል፡፡ ሌሎቹን የመንፈስ ፍሬዎች ከማሰባችን በፊት ፍቅር ሊኖረን ፍቅርን ልንከታተል ያስፈልጋል 1ቆሮ.14:1፡፡ ✞ ፍቅር የአንዱን ድካም አንዱ ሲሸከም ነው። ሰማዕትነት የሌለበት ፍቅር ፍቅር አይባልም። በአፍ ብቻ እወድሃለሁ እወድሻለሁ ማለት ውሸት ነው። ይህንንስ ባላገሩ "የአፍ ዘመድ ከገበያም አይገድ" ብሎ ተርቶበታል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐ. ፲፭፣፲፫ "ነፍሱን ስለወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም" ብሎ የፍቅርን ትርጓሜ አስተማረን። ፍቅር በአፍ የሚናገሩት ብቻ አይደለም በሕይወት የሚኖሩትም ነው እንጂ። ለዚያም ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን በቃል ከተናገረ በኋላ በተግባር ደግሞ አዳምን ለማዳን በመስቀል የተሰቀለ። መስቀል ፍቅር በተግባር የተገለጠበት አደባባይ ነው። ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብጽሖ እስከ ለሞት ብሎ ሊቁ የገለጠው ይህንን ነው። ፍቅር ራሱ እግዚአብሔር ነው። ፩ኛ ዮሐ.፬፣፰-፳ "ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም እግዚአብሔር ፍቅር ነውና----ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው" ይላል። ይህ የሚነግረን በፍቅር ጥላቻ እንደሌለ ነው። ፍቅር ሌላውን እንደ ራስ መውደድ ነው። ማቴ. ፯፣፲፪ "ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው" ተብሎ እንደተጻፈ ሰውን መውደድ በእኛ ሊደረግብን የማንፈልገውን በሌላውም እንዲደረግ አለመፈለግ ሲሆን እግዚአብሔርን መውደድ ደግሞ ትእዛዙን በመፈጸም ይገለጣል።ዮሐ. ፲፬፣፳፩ "ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው" እንዲል። ✞ ማቴ. ፯፣፳፩-፳፫ "በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። በዚያ ቀን ብዙዎች ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን ይሉኛል። የዚያን ጊዜም ከቶ አላወቅኋችሁም እናንተ አመፀኞች ከእኔ ራቁ ብየ እመሰክርባቸዋለሁ" እንዲል የጌታን ስም ብዙ ጊዜ ብትጠራ፣ በስሙ ተአምራትን ብታደርግ፣ በስሙ ትንቢትን ብትናገር፣ በስሙ አጋንንትን ብታወጣ ይህ የፍቅር ምልክት ተደርጎ አይያዝም። እግዚአብሔርን የመውደድ ዋናው ምልክቱ ፈቃዱን መፈጸም ነው። ፈቃዱ ምንድን ነው ከተባለ ዘጸ. ፳፣፩ ጀምሮ ያሉ አስሩን ሕግጋት መፈጸም ነው። ማቴ. ፲፱፣፲፯ "ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ" እንዳለ። ዮሐ. ፲፪፣፶ "ትእዛዙም የዘለዓለም ሕይወት እንደሆነች አውቃለሁ"እንዲል። ✞ ቅዱስ ጳውሎስ ፍቅርን ጠቅለል አድርጎ ሲያቀርበው እንዲህ ብሎታል። ፩ኛ ቆሮ. ፲፫፣፪-፰ " ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድኾችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። ፍቅር ይታገሣል፣ ቸርነትንም ያደርጋል፣ ፍቅር አይቀናም፣ ፍቅር አይመካም፣ አይታበይም፣ የማይገባውን አያደርግም፣ የራሱንም አይፈልግም፣ አይበሳጭም፣ በደልን አይቆጥርም፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለዓመፃ ደስ አይለውም። ሁሉን ይታገሣል፣ ሁሉን ያምናል፣ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣ በሁሉ ይጸናል። ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም" ብሎ ገልጾታል።
👉'ደስታ' ይቀጥላል ...........@Ethiopian_Orthodox @Ethiopian_Orthodox
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.