cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹

@Tewahdo27 ✞ በየጊዜው አዳዲስ መንፈሳዊ † ➢ ፅሁፎች ➢ መዝሙሮች ➢ ኦርቶዶክሳዊ መልእክቶች ➢ መንፈሳዊ ነገሮችን ሁሉንም ለማግኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞ ለአስተያየቶ @Tewahdo27 ይጠቀሙ ➢ ሁሉም እንዲያነበው SHARE ያርጉ ! እናመሰግናለን !

Show more
Advertising posts
3 351
Subscribers
-224 hours
-157 days
+12530 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

️🤩 #መስከረም_10 🌹🌹 🕯 ፀደንያ ️🕯️ 🌻🌻🌹🌹🌹🌻🌻 የእመቤታችን በዓላት "33" ናቸው፣ ከእነዚህም አንዱ ወር በገባ በ "10" የሚሆን #ፀደንያ_ማርያም አንዱ ነው! . #ታሪክ 🌹 ጸዴንያ በምትባል ሀገር ማርታ የምትባል ደግ ሴት ነበረች! ይህች ደግ ሴት በቤቷ ትልቅ አዳራሽ ሰርታ እንግዶችን እንደ አባታችን አብርሃም ተቀብላ አብለታ አጠጥታ ማደሪያ ቦታም ሰጥታ ታስተናግድ ነበር! አባ ቴዎድሮስ የሚባል ኢትዮጵያዊ መነኩሴ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሔድ መሽቶበት ከማርታ ቤት በእንግድነት አድረ ጠዋት ለመሔድ ሲነሣ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚሄድ ሲነግራት የእመቤታችንን ሥዕል ገዝተህ አምጣልኝ ዋጋውን ልስጥህ አለችው! ገንዘቡን ሥዕሉ ን ሳመጣልሽ ትሰጪኛለሽ ብሏት ሄደ፡፡ 🌻 ቅዱሳት ቦታዎችን (መካናትን) ተሳልሞ ሥዕሉን ረስቶ ሳይገዛ ሲመለስ « አደራ ጥብቅ አይደለምን? ያቺ ሴት አደራ ያለችህን ለምን ረሳህ» የሚል ድምጽ ሰማ ተመልሶ ሄዶ ገዝቶ በረሃ በረሃውን መጓዝ ጀመረ! በመንገድም እየተጓዘ አንበሳ ሊበላው አየሮጠ ወደ እሱ ሲመጣበት አየ መነኩሴው አንበሳውን ከመፍራት የተነሣ ደነገጠ ተንቀጠቀጠ ደንግጦ ቁሞ ሳለ ያች ሥዕል ከአንበሳው ጩኸት ሰባት እጅ በሚበልጥ አስፈሪ ድምጽ ጩሃ ተናገረች! ያን ጊዜ አንበሳው ደንግጦ ፈጥኖ ሸሸ! መነኩሴውም መንገዱን ቀጠለ፣ በመንገዱም ከሚያስፈራ ዱር ውስጥ ወጥተው ወንበዴዎች ሊቀሙትና ሊገድሉት ከበቡት! ከሥዕለ ማርያሟም እንደ መብረቅ ያለ ታላቅ ቃል ወጣ! ወንበዴዎችም እጅግ ፈርተው ሸሽተው ከጫካው ውስጥ ገቡ፡፡ 🌻 ያም መነኩሴ እኝህን የሚያስደንቁ ተአምራት በሰማና ባየ ጊዜ በልቡ « ለእኔ ረዳት ትሆነኝ ዘንድ ወደ ሀገሬ ይዣት እሄዳለሁ እንጂ ለላከችኝ ሴት አልሰጥም» ብሎ ወደ ሀገሩ ሊሄድ በመርከብ ተሳፈረ! በባሕር ላይም ሳለ ጽኑ ነፋስ ተነስቶ መርከቡን እየገፋ ማርታ ወዳለችበት ሀገር ወደ ጼዴንያ ዳርቻ አደረሰው! ማደሪያም ስለሌለው ወደ ደጓ ሴት ወደ ማርታ ቤት ከእንግዶች ጋር አብሮ ገብቶ አደረ፡፡ 🌻 ሲነጋ ወጥቶ ሊሔድ ከደጃፍ ሲደርስ ደጃፉ ጠፍቶት ከአጥሩ ሲታገል ዋለ! ማርታም «አባቴ ያመመህ የደከመህ ትመስላለህ ዛሬ ደግሞ እዚህ እደርና ነገ ትሔዳለህ» አለችውና አደረ! በሁለኛውም ዕለት እንደ መጀመሪያው ቀን በሩን አልፎ መሄድ አቃተውና እዚያው ማርታ ቤት አደረ! በሦስተኛው ቀን መውጣት ፈልጐ ከአጥሩ ጋር ሲታገል አይታ «አባቴ የሆንከው ምንድነው እነሆ ዛሬ ሦስተኛ ቀንህ ነው» አለችው፣ መነኩሴውም «ይህችን ተአምረኛ ሥዕል አልሰጥም ብዬ ነው! እኔኮ ሥዕል ከኢየሩሳሌም ግዛልኝ ያልሽኝ መነኩሴ ነኝ» ብሎ ሥዕለ ማርያምን አውጥቶ ሰጣት፡፡ 🌻 እርሷም እጅግ በጣም ተደስታ እግዚአብሔርን አመሰገነች! በሥዕሏም ፊት ሰግዳ ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም ምስጋናን አቀረበች! ተቀብላም የተጠቀለለችበትን ልብስ ስትፈታ ፈሳሽ ወዝ ከስዕሊቱ ሲንጠፈጠፍ አገኘች! ከደስታዋም ብዛት የተነሣ የዚያን መነኩሴ እጆቹንና እግሮቹን ሳመች! ከዚህም በኋላ ያቺን ሥዕል ወደ ጸሎት ቤቷ ወስዳ በታላቅ ክብር የምትቀመጥበትን አዘጋጅታ አኖረቻት ማንም እንዳይዳስሳትም የነሐስን መስኮትን ሰራችላት! በሌሊት የሚያበሩ መቅረዞችን በፊቷ ሰቀለች! ከመቅረዞችም ውጭ የሐር መጋረጃን ጋረደች ከሥዕሊቱ እየተንጠፈጠፈ የሚወርደው የወዝ ቅባት የሚጠራቀምበት ከዕብነ በረድ የተሰራ ወጭት አኖረች! ያም መነኮስ እስከሚሞትበት ቀን ድረስ የእመቤታችንን ድንግል ማርያምን ሥዕል እያገለገለ ኖረ። 🌻 የሀገሩም ሊቀ ጳጳሳት የዚያችን ሥዕል ዜና በሰሙ ጊዜ ከኤጲስ ቆጶሳትና ከካህናት ጋር ህዝቡም ሁሉ መጡ፣ ሊቀ ጳጳሱም ይህች ስጋ የለበሰች የምትመስል ስዕለ ማርያም ወደ ማርታ ቤት የገባችበትን መስከረም "10" እለት በዓል ሁና እንድትከበር አወጀ:: 🙏 እመቤታችን በምልጃዋ ከልጇ ታሳስበን [ #አሜን ] 🤲 Oô Màryâm Lâmmà Sëbèktânï 💚@ortodox_27 💚 💛@ortodox_27 💛 ❤️@ortodox_27 ❤️ #ይቆይ//
Show all...
☞ወር በገባ በ9 ታስበው የሚወሉት አባታችን አብነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ያደረጉት ታዕምር ይህ ነው፡፡ ☞ኮሬብ በሚባል አገር ብዙ ዘመን ታሞ በአልጋ ላይ ተኝቶ የሚኖር አንድ ሰው ነበር፡፡ ለዘመዶቹ ወደ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ገዳም ውሰዱኝ ያለ እሱ የሚፈውሰኜ ኝ የለም በፍጹም ልቡናው አምኖ ይህን በተናገረ ጊዜ ተሸክመው አምጥተው ከአባታችን መቃብር ላይ አስቀመጡት ያም ታማሚ ሰው አባታችንን ከደጅህ ወደቅሁ በጸሎትህና ተማጸንኩ የተአምራትህን ኃይል በእኔ ላይ ግለጽ ኃጢአተኛ የምሆን የእኔን የባሪያህን ልመና ቸል አትበል አለ ይህን ብሎ ከአባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አጠገብ የምትፈሰ ጠበል ተጠምቆ ተኛ ሲነሳ በአባታች በአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ በጸሎቱ ኃይል ዳነ፡፡ ☞እጆቹና እግሮቹ ቀንተውለት በእግሩ ቆመ ጉልበቱም እን ጎልማሳ ሆነ ሕዝቡም የተደረገውን ተአምር አይተው እጅግ እግዚአብሔርን አመሰገኑና ይህ ጻድቅ ተአምራቱን አሳየን እኛም በጸሎቱ ኃይል ተማጽነናል እያሉ አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስን አደነቁ፡፡ ☞እኛንም አባታችን አብነ አስትንፋሰ ክርስቶስ በጸሎቱ ሀይል ከክፋ ዕለት እና ከጥፋት ሠዓት በሚመጣው ዓለም ከገሐነም እሳት ታድኑን ዘንድ እንማጸናለን፡፡ ☞(ገድለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ) ☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ ☞8-1-2017
Show all...
Show all...
TikTok · Danu Daniel

Check out Danu Daniel’s video.

🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼 ⛪️✍ #አንዱም_ለአንዱ ፦ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች አያለ ይጮህ ነበረ። ( ትን.ኢሳ ፮÷፫)❤️🙏❤️ #እንኳን_አደረሳቹሁ_የእምየ_ተዋሕዶ_ልጆች ለአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ(፯🕯) ✳️ሥላሴ፦ #ሠለሰ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን #ሦስት_አደረገ ማለት ነው፡፡ #ሥላሴ ማለት ሦስትነት ማለት ነው። ✳️እግዚአብሔር #አንድ_ሲሆን_ሦስት ሦስት ሲሆን አንድ ነው፡፡ ✳️ እግዚአብሔር #የአብ_የወልድ_የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት መጠሪያ ስማቸው ነው:: ✳️የእግዚአብሔር አንድነት በመለኮት፣ #በሕልውና_በአገዛዝ_በባሕርይ፣ !#በመፍጠር_በሥልጣን፣ በፈቃድ በመሳሰሉት ነው፡፡ ( ዘፍ፩፥፲፩ ) (መዝ፻፩፥፳፭) ( ዮሐ፲፥፴ ) (ዮሐ ፲፬፥፲ ) ✳️የእግዚአብሔር ሦስትነት #በስም_በአካል፣ #በግብር ነው፡፡ ✳️የስም ሦስትነት፦ #አብ_ወልድ_መንፈስ ቅዱስ። (ማቴ.፳፰፥፲፱) ✳️የአካል ሦስትነት፦-ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ #ለእያንዳንዳቸው_ፍጹም መልክዕ ገጽ፣ አካል አላቸው፡፡ (ማቴ.፫፥፲፮) ✳️የግብር ሦስትነት፡- #አብ_ወላዲ_አስራጺ፣ #ወልድ_ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራጺ ከአብ የሰረጸ። (ዮሐ፲፭፥፳፮)🙏❤️🙏 ✳️#ሦስቱም በባሕርይ #መለያየት፥ በአካል #መቀላቀል ሳይኖርባቸው ስማቸውና ግብራቸው ሳይፋለስ በአንድነት በሦስትነት ጸንተው ለዘላለም ይኖራሉ፡፡ ✳️አንድነትና ሦስትነት በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን ነገ እንመለከታለ ወስበሐት ለእግዚያብሔር 🤲 🤲 🤲 #አሜን......... 🧡 ......... #አሜን ⊹ #አሜን🙏³ @ortodox_27 🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼
Show all...
🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼 ⛪️✍ #አንዱም_ለአንዱ ፦ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች አያለ ይጮህ ነበረ። ( ትን.ኢሳ ፮÷፫)❤️🙏❤️ #እንኳን_አደረሳቹሁ_የእምየ_ተዋሕዶ_ልጆች ለአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ(፯🕯) ✳️ሥላሴ፦ #ሠለሰ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን #ሦስት_አደረገ ማለት ነው፡፡ #ሥላሴ ማለት ሦስትነት ማለት ነው። ✳️እግዚአብሔር #አንድ_ሲሆን_ሦስት ሦስት ሲሆን አንድ ነው፡፡ ✳️ እግዚአብሔር #የአብ_የወልድ_የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት መጠሪያ ስማቸው ነው:: ✳️የእግዚአብሔር አንድነት በመለኮት፣ #በሕልውና_በአገዛዝ_በባሕርይ፣ !#በመፍጠር_በሥልጣን፣ በፈቃድ በመሳሰሉት ነው፡፡ ( ዘፍ፩፥፲፩ ) (መዝ፻፩፥፳፭) ( ዮሐ፲፥፴ ) (ዮሐ ፲፬፥፲ ) ✳️የእግዚአብሔር ሦስትነት #በስም_በአካል፣ #በግብር ነው፡፡ ✳️የስም ሦስትነት፦ #አብ_ወልድ_መንፈስ ቅዱስ። (ማቴ.፳፰፥፲፱) ✳️የአካል ሦስትነት፦-ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ #ለእያንዳንዳቸው_ፍጹም መልክዕ ገጽ፣ አካል አላቸው፡፡ (ማቴ.፫፥፲፮) ✳️የግብር ሦስትነት፡- #አብ_ወላዲ_አስራጺ፣ #ወልድ_ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራጺ ከአብ የሰረጸ። (ዮሐ፲፭፥፳፮)🙏❤️🙏 ✳️#ሦስቱም በባሕርይ #መለያየት፥ በአካል #መቀላቀል ሳይኖርባቸው ስማቸውና ግብራቸው ሳይፋለስ በአንድነት በሦስትነት ጸንተው ለዘላለም ይኖራሉ፡፡ ✳️አንድነትና ሦስትነት በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን ነገ እንመለከታለ ወስበሐት ለእግዚያብሔር 🤲 🤲 🤲 #አሜን......... 🧡 ......... #አሜን ⊹ #አሜን🙏³ @ortodox_27 🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼🕯🌼
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.