cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Ethio Education 4 All

This channel provides 📌 Educational information 📌 Text Books ፣ Guides ፣ Modules ፣ Notes 📌 Exams ፣ Exercises ፣ Worksheets 📌 Research & Proposals ፣ .... 📝 Send questions, comments, or suggestions through 👇 👉 @EducConsultBot

Show more
Advertising posts
243
Subscribers
+124 hours
+27 days
+430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from N/a
Binance MoonBix (Confirmed ✅) BINANCE MOONBIX የተሰኘ የራሱን MINI APP በቴሌግራም ይዞ መጥቷል። Binance MOONBIX የራሳቸው mini-game መሆኑንም በ Official ቻናላቸው አረጋግጠዋል (👉 https://t.me/binance_announcements/6633)። Join Link - MOONBIX ❶ እንደ Blum drop games ተጫወቱ ➋ tasks ስሩ ➌ Invite አድርጉ በጊዜ ጀምሩትና ወጥራችሁ ስሩ ! 👉 Link -  https://t.me/Binance_Moonbix_bot/start?startapp=ref_564726315&startApp=ref_564726315
Show all...
Repost from N/a
ከታች ባለው ሊንክ በመግባት Vist Oromia ባዘጋጀው ውድድር ላይ በ Best Culture Photographer ዘርፍ የመጨረሻ ዙር ተወዳዳሪ ለሆነው Abenezer Yonas ድምጽ በመስጠት ትብብር ያድርጉ         👇👇👇👇   https://t.me/visit_oromia/5537    🙏🙏🙏
Show all...
Vote for the Best Cultural Photographer ! Vote for 👉 Abenezer Yonas Link - https://t.me/visit_oromia/5537 Vote for 👉 Abenezer Yonas
Show all...
Visit Oromia

Best Cultural Photographer Of 2024 1. Abenezer Yonas / 2. Samuel Melkamu / 3. Abduselam Worku

የ12ኛ ክፍል ማትሪክ ውጤት ለመመልከት ፦ 1. በዌብሳይት https://eaes.edu.et/ 2. በ 6284 - SMS 3. በቴሌግራም - @eaesbot ውጤታችሁን ለመመልከት ተከታዩን ሊንክ እንጠቀማለን ፦
https://Verify.eaes.et/temporary/FNLNMN=ID
ውጤታችሁን ለመመልከት ተከታዮቹን steps መከተል አለባችሁ ፦ Step 1፦ ተከታዩን ሊንክ Copy እናደርጋለን
https://Verify.eaes.et/temporary/
Step 2፦ Copy ካደረጋችሁት ሊንክ ቀጥሎ Capital Letter በመጠቀም የስማችሁን ቀጥሎ የአያታችሁን ከዛ የአባታችሁን ስም የመጀመሪያ ሁለት ሁለት ፊደላት ማስገባት ። ✅ FN = የራሳችሁ ስም የመጀመሪያዎቹን ሁለት ፊደላት ✅ LN = የአያታችሁ ስም የመጀመሪያው ሁለት ፊደላት ✅ MN = የአባታችሁ ስም የመጀመሪያ ሁለት ፊደላት Step 3፦ በማስከተል የ '=' ምልክት ካስገባን በኋላ የራሳችንን Registration Number እናስገባለን። ከዚህ በኋላ ሊንኩ እንደሚከተለው ይሆናል ማለት ነው፦
https://Verify.eaes.et/temporary/FNLNMN=ID
ውጤታችሁን እንዴት መመልከት እንደምትችሉ በምሳሌ እንይ ፦ ለምሳሌ የተማሪው ስም = ABEBE KEBEDE ALEMU ፤ Registration Number = 7363857 ቢሆን ፥ ከሙሉ ስሙ የመጀመሪያዎቹን ሁለት ሁለት ፊደላት ማለትም ፦ የራሱ ስም = AB የአያቱ ስም = AL የአባቱ ስም = KE Reg Number = 7363857 በመጠቀም የሚከተለውን ሊንክ ይጠቀማል ማለት ነው፦
https://Verify.eaes.et/temporary/ABALKE=7363857
ከላይ ያሉትን Steps በመከተል በቀጥታ ያለምንም ተጨማሪ Process ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ። ማሳሰቢያ፦ 1. ቅደም ተከተሉን እንዳትሳሳቱ ፥ 2. ሁሉም ፊደላት በ capital letter መሆን እንዳለበት እንዳትረሱ
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
"በጥቅሉ የዘንድሮው ውጤት ካለፉት 2 ፈተናዎች የተሻለ ነው" ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች ያለፉት 36,409 (5.4 በመቶ) ናቸው። አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 10,690 (21.4 በመቶ) በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል። በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በትግራይ ነው። በትግራይ ከቀላሚኖ ት/ቤት 675 ከ 700 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ 700 ይሄን ያህል ውጤት ሲመዘገብ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። በሀገር ደረጃ ከተፈጥሮ ሳይንስ ከካቴድራል ት/ቤት 575 ከፍተኛው ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። ከማህበራዊ ሳይንስ ከኢትዮ ፓረንትስ ትምህርት ቤት 538 ከፍተኛው ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። በተፈጥሮም በማህበራዊ ሳይንስም ከፍተኛው ውጤት የመጣው በሴቶች ነው። ዘንድሮ 1,363 ትምህርት ቤቶች ምንም አይነት ተማሪ አላሳለፉም። በኦላይን ከተፈተኑ ተማሪዎች 26.6 በመቶ የሚሆኑት አልፈዋል። Via:- tikvahethiopia
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
#NGAT ሀገር አቀፍ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ከዛሬ ከሰዓት ጀምሮ መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናውን ለመውሰድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን በፈተና ማዕከልነት ከመረጡ ተፈታኞች በስተቀር ፈተናው በመላ አገሪቱ በሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በኦንላይን እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ፈተናውን ለመውሰድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን በፈተና ማዕከልነት ለመረጡ ተፈታኞች ብቻ የፈተናው መስጫ ጊዜ መለወጡን ትምህርት ሚኒስቴር ትናንት ማሳወቁ ይታወቃል፡፡ Via:- tikvahuniversity
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የ NGAT ደንብ እና ስርዓት የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ከነገ ነሐሴ 30/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ተፈፃሚ የሚሆኑ የፈተናውን ደንብ እና ስርዓት ፦ ለተፈታኞች ► ሞባይል፣ ካልኩሌተር እና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ይዘው ፈተና ክፍል ውስጥ መግባት አይችሉም፡፡ ► ወደ መፈተኛ ክፍል ሲመጡ ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ እና Pass Card ብቻ መያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ► ፈተናው ከሚጀምርበት ሰዓት ከ30 ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት መፈተኛ ክፍል መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡ ለፈታኝ መምህራን ► ማንኛውም ፈታኝና አስተባባሪ ተንቀሳቃሽ ስልክ (ሞባይል) ይዞ ወደ መፈተኛ ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው። ► በፈተና ወቅት ተፈታኞችን ከመቆጣጠርና የፈተና አሰጣጥ ደንብ ከማስከበር ባለፈ ሌሎች ነገሮችን እንዲፈጽሙ አይፈቀድም። Via:- tikvahuniversity
Show all...
Starlinkየወደፊቱ የአለማችን የኢንተርኔት አብዮት ምንድን ነው? Starlink በኤለን መስክ ድርጅት SpaceX የተመሰረተ የሳተላይት ኢንተርኔት ፕሮጀክት ነው። የዚህ ፕሮጀክት ተቀዳሚ ተልዕኮው በዓለም ዙሪያ ላሉ የኢንተርኔት አገልግሎት ለማያገኙ ገጠራማና ሩቅ የአለም ክፍሎች ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ነው። Starlink ብዙ ቁጥር ያላቸው Low Earth Orbit (LEO) ሳተላይቶችን በጋራ በማሰማራት የፋይበር ኦፕቲክና የሞባይል ኔትዎርክ ግንኙነት የማያገኙ አካባቢዎችን አስተማማኝና ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ለማቅረብ አልሞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ዋና ዋና ባህሪያቶችGlobal Coverage: የስታርሊንክ የሳተላይት ኢንተርኔት መላው ፕላኔት የሚሸፍን ሲሆን ይህም ቀደም ሲል የኢንተርኔት ግንኙነት የማያገኙ የአለማችን ክልሎችን ተደራሽ ያደርጋል። ➋ High-Speed Internet: ስታርሊንክ ከባህላዊ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች ጋር የሚወዳደር የብሮድባንድ ፍጥነትን የሚያቀርብ ሲሆን Online Gaming, Video Conferencingና የመሳሰሉ real-time online ስራዎችን በጥሩ ፍጥነት መከወን ያስችላል። ➌ Easy Installation: StarLink ለመጠቀም በጣም ቀላል የሆነችና በቀላሉ ከታ ቦታ ማንቀሳቀስ የምትቻል Dish ሲኖረው ማንኛውም ቦታ ላይ በማስቀመጥ እራሷን ከሳተላይት ጋር ማስተካከል ትችላለች። ከዚህ በተጨማሪ LTE connection ላላቸው የሞባይል ቀፎዎች የፅሁፍና የድምጽ መልዕክት እንዲሁም የኢንተርኔት አገልግሎት ያገኛሉ ተብሏል። ➍ Constant Updates: ስታርሊንክ ተጨማሪ ሳተላይቶችን በማምጠቅ እና ሶፍትዌሩን በማዘመን ኔትወርኩን በየጊዜው እያሰፋ እና እያሻሻለ ይገኛል። አገልግሎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ ብዙ የአለም ክፍሎችን እያካለለ ነው። ❺ Disaster Response: አሁን የምንጠቀምባቸውን የኢንተርኔት አቅራቢ ድርጅቶችን infrastructure በተለያዩ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ቢወድሙ communication ይቋረጣል። የስታርሊንክ ሳተላይት ከዚህ ነገር ነጻ ሲሆኑ ለድንገተኛ አገልግሎቶች እና እርዳታ የሚፈልጉ የተጎዱ ሰዎችን በቀላሉ ማግኘት ያስችላል። በአሁኑ ሰአት በተወሰኑ የአለማችን ሃገራት ስራ የጀመረው StarLink ከአፍሪካ ሃገራት ናይጀርያ፣ ጋና፣ ሴራሊዮን፣ ማላዊ፣ ዛምብያ፣ ቦቶስዋና፣ ማዳጋስካር፣ ሩዋንዳ፣ ኬንያና ደቡብ ሱዳን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ናቸው። ይህን አገልግሎት ለመጠቀም ክፍያው ያን ያክል ውድ የሚባል አይደለም። ከሃገራት ሃገራት ልዩነት ቢኖረውም ያልተገደበ high-speed ዳታ ለመጠቀም በወር ለግለሰብ 120 ዶላር ለ Business ደግሞ ከ 140 - 5000 ዶላር መክፈል ይጠይቃል። በሀገራችን በተለይ በገጠሪቱ የሀገራችን ክፍል ብዙ ሰው የኢንተርኔት አገልግሎት አያገኝም። ይህ ነገር በሃገራችን ቢጀመር ብዙ ሰው የሚጠቀም ይመስላችኋል? ሀሳባችሁን አካፍሉን።
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የወደፊቱ የአለማችን የኢንተርኔት አብዮት Starlink ምንድን ነው? 👇👇👇👇👇
Show all...
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ2017 ዓ.ም የአዲስ የተማሪዎች ቅበላ አሰራርን በተመለከተ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጫው ተከታትሏል። ዩኒቨርስቲው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ እና ልዩ ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን አወዳድሮ እንደሚቀበል በዚሁ መግለጫ አስታውቋል። የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕረዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ፥ ራስ-ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ የተቋቋመው ዩኒቨርሲቲው ተቋማዊ ነጻነት፤ አስተዳዳሪዊ ነጻነት፤ የፋይናንስ ነጻነት እና አካዳሚክ ነጻነት ማግኘቱን ገልጸዋል። "ይህም መምህራኑን ሆነ ተማሪዎችን የመምረጥ መብት ይሰጠዋል" ሲሉ ገልጸዋል። አዲስ ይተገበራል በተባለው የቅበላ አሰራር በ2014፤ 2015 እና 2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች የሚወጣውን መስፈርት ታሳቢ አድርገው በዩኒቨርሲቲው ፖርታል https://portal.aau.edu.et መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል። መስፈርቶቹ ምንድን ናቸው ? ዶ/ር ሳሙኤል ፥ አንዱ መስፈርት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን 50 በመቶ በላይ ማምጣት እንደሆነ ገልጸዋል። ይህ ግን የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ባገናዘበ መልኩ 60 ወይም 70 በመቶ ድረስ ከፍ ሊል እንደሚችል ጠቁመዋል። በመቀጠልም ዩኒቨርስቲው በራሱ የሚያዘጋጀው የመግቢያ ፈተና (Undergraduate Admission Test) የሚኖረው ሲሆን ይህንን ፈተና ማለፍም ሌላው ዩኒቨርሲቲው ያስቀመጠው መስፈርት ነው ብለዋል። ፈተናው ምን መልክ ይኖረዋል ? በዩኒቨርስቲው መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች የሚቀርበው የፈተና ይዘት ምን መልክ አለው በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ዶ/ር ሳሙኤል ፈተናው የአፕቲቲውድ (Apptitude) መልክ የሚኖረው እንደሆነ ጠቅሰው የተማሪዎችን የቋንቋ፤ የማመዛዘን እንዲሁም የቀመር አቅማቸውን የሚለካ እንደሚሆን ጠቁመዋል። ፈተናው ከሌሎች የመግቢያ ፈተና ጋር ተመሳሳይነት ሊኖረው እንደሚችል ያነሱት ፕሬዝዳንቱ ሆኖም የሚወጣው ፈተና ሙሉ በሙሉ የዩኒቨርስቲው እንደሚሆን አስረድተዋል። የክፍያ እና የስኮላር ሺፕ ሁኔታ በተመለከተ ምን ተባለ ? በዩኒቨርስቲው ለመማር ጥያቄ የሚያቀርቡ ተማሪዎች በሁለት አይነት መንገድ እንደሚስተናገዱ ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። አንደኛው መስፈርቱን አሟልተው እና ሙሉ ክፍያ ከፍለው የሚማሩ ተማሪዎች ሲሆኑ ሌላው መንግስት ስፖንሰር ሺፕ እንዲሰጣቸው የሚጠይቁ ተማሪዎች ናቸው። ይህን በተመለከተ የተቀመጠ ኮታ እንደሌለ የገለጹት ዶ/ር ሳሙኤል እንደ እቅዳቸው ግን 50 በመቶ በመንግስት 50 በመቶ በግል ወጪያቸው የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎች ለመቀበል እንደሆነ ገልጸው ካልሆነም ቁጥሩ በተወሰነ መልኩ ልዩነት ሊኖረው እንደሚችልም ጠቁመዋል። መንግስት ከፍተኛ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለሀገር በሚፈለጉ የስልጠና መስኮች ወጪን ጭምር በመሽፈን የሚያስተናግድበት ሥርዓት እንደሚኖር እና ለሴቶች ለአካል ጉዳተኞች እና ከታዳጊ ክልል ለሚመጡ ተማሪዎች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥም ተመላክቷል። ተማሪዎች በሚያመለክቱበት ወቅት ብዙ ቅጾችን እንደሚሞሉ ፤ ስኮላርሺፕ የሚጠይቁ ተማሪዎች ከፍለው መማር እንደማይችሉ የሚያሳይ ማስረጃ ከሚመለከተው አካል ማሟላት እንደሚጠበቅባቸው እና የሚያስገቡት መረጃ ትክክለኛነቱ እንደሚጣራና ሐሰተኛ ሆኖ ከተገኘ የህግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ጭምር አንስተዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን ዩኒቨርስቲው በተከታታይ እንደሚሰጥ አረጋግጧል። Via:- TikvahEthiopia
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.