1 017
Subscribers
+124 hours
+357 days
+15730 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የነፍስ ምግብ እንጅ
አንዳንድ ሰዎች እንደሚያስቡት ጾም የሥጋ ሥቃይ ሰማዕትነት ወይም መስቀል አይደለም ሥጋ ከነፍስ ጋር የሚተባበርበት ደረጃ ላይ ለመድረስ ከፍ ከፍ የሚልበት እንጂ። ስንጾም የመጾማችን ዕቅድ ሥጋችንን ለማንገላታት አይደለም ጠባዩን ለመግራት እንጂ። ይህ በመሆኑም አንድ የሚጾም ሰው መንፈሳዊ እንጂ ሥጋዊ ሰው አይሆንም ማለት ነው ።
ጾም መናኝ ነፍስ ስለሆነ በምናኔ ውስጥ ያለ ባልንጀራ ሥጋውን ይዞ ይጓዛል እንጂ ብቻውን አይጓዝም። ጾም ማለት የተራበ ሥጋ ማለት አይደለም የመነነ ሥጋ እንጂ። ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የሥጋ ልዕልና እና ንጽህና እንጂ ለመብላት የሚናፍቅ የሚራብ ሰውነት ያለበት ሁኔታ ማለትም አይደለም፤ መብላት ዋጋውን የሚያጣበትና ሰውነት ለመብላት ካለው ፍላጎት ራሱን የሚያላቅቅበት ሁኔታ እንጂ።
ጾም ነፍስ ከፍ ብላ ሥጋን ከእርስዋ ጋር ከፍ የምታደርግበት ጊዜ ነው። ይህ ጊዜ ሥጋ ጓዙንና ሸክሙን የሚያራግፍበት ጊዜ ስለሆነ እግዚአብሔር ያለ ምንም እገዳ ለመንፈሳዊ ዘላለማዊነት ደስታ የሚሠራበት ጊዜ ይሆናል። ጾም ማለት ነፍስና ሥጋ በኀብረት መንፈሳዊ ተግባር ለማከናውን የሚጠቀሙበት ጊዜ ነው። በጾም ወቅት ነፍስና ሥጋ የነፍስን ሥራ ለመሥራት ይተባበራሉ። ይህም ማለት ለጸሎት ለተመስጦ ለክብርና ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆን ሕይወትን ለመጋራት ይተባበራሉ ማለት ነው።
ብጹዕነታቸው አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
ጾም እጅግ ግሩም የሆነ ነገር ነው፡፡ ኃጢአታችንን እንደማይጠቅም አረም ከውስጣችን ይነቅለዋል፡፡ እውነተኛው የጽድቅ ተክልም በውስጣችን ልክ እንደ አበባ እንዲያብብ ይረዳዋል፡፡ (ቅዱስ ባስልዮስ)
ከምግባራት ሁሉ ታላቁ ጸሎት ነው ነገር ግን የእርሱ መሠረቱ ጾም ነው፡፡ የምንጾምበት ምክንያት ርኩስ የሆነውን የሰይጣንን መንፈስ በነፍሳችን ውስጥ እንዳያድር ለመጠበቅ ነው፡፡ ሥጋችንን ለጾም ባስገዛነው ጊዜ ነፍሳችን ነፃነትን፤ ጥንካሬን ሰላምን፣ ንጽሕናን እንዲሁም እውቀትን ለመለየት እንድትበቃ ትሆናለች፡፡ (ጻድቁ ዮሐንስ ዘክሮስታንድ)
“ማግባት ስትፈልግ አስቀድመህ ጸልይ፤ አሳብህን ለእግዚአብሔር ንገረው፡፡ እግዚአብሔር መርጦ እንዲሰጥህ ለምነው፡፡ ጭንቀትህን ኹሉ በእርሱ ላይ ጣለው፡፡ አንተ እንደዚህ እርሱ እንዲመርጥልህ የምታደርግ ከኾነም፥ አክብረኸዋልና እርሱም ለአንተ በጎ የትዳር አጋርን በመስጠት ያከብርሃል፡፡ ስለዚህ በምታደርገው ነገር ኹሉ ሽማግሌህ እርሱ እግዚአብሔር እንዲኾን ዘወትር ጠይቀው፡፡ አስቀድመህ እንደዚህ ካደረግህም፥ ወደ ትዳር ከገባህ በኋላ ፍቺ አይገጥምህም፡፡ ሚስትህ ሌላ ሰውን አትመኝም፡፡ በሌላ ሴት እንድትቀናም አታደርግህም፡፡ በመካከላችሁ [ለክፉ የሚሰጥ] ጠብና ክርክር አይኖርም፡፡ ከዚህ ይልቅ ታላቅ የኾነ ሰላምና ፍቅር በመካከላችሁ ይሰፍናል፡፡ እነዚህ ካሉ ደግሞ ሌሎች በጎ ምግባራትን፣ ትሩፋትን ለመፈጸም አትቸገሩም፡፡”
© ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ፣ ገጽ 33
❤ 5👍 4
"ጠላት በመኾን የተነሣብህን ሰው የምትርቅበት መንገድ አለ ይህውም እርሱን ወዳጅ በማድረግ መቀየር ነው፡፡''
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Show all...
የሕይወት መዓዛ (አቡነ ሺኖዳ)
በዚህ መንፈሳዊ ቻናል የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ በሕይወት ላይ ያተኮሩ ጽሑፎችና ሌሎች ኦርቶዶካሳዊ ትምህርቶች በጽሑፍና በድምጽ ይቀርብበታል
የጸሎት ጊዜ የለኝም
በጃፓን ሀገር የምትኖር አንዲት አረማዊ የነበረች ሴት በኋለኛዋ ዘመን ክርስቲያን ትሆናለች፡፡ ነገር ግን ከድህነቷ የተነሳ የጸሎት ጊዜ አልነበራትም፡፡ አንድ ቀን ክርስቲያን ጎረቤቶችዋ መጥተው አንቺ ክርስቲያን ሆኛለሁ ብለሽ የለ እንዴ? ታድያ እንደ ክርስቲያኖች ስትጸልይ ድምጽሽን ሰምተን አናውቅም አሏት፡፡ እርሷም እኔ ድሃ ስለሆንኩ ስራ ስለሚበዛብኝ ጸሎት ለማድረስ የእረፍት ጊዜ የለኝም አለቻቸው፡፡ ነገር ግን በየጊዜው ጸሎት አቋርጬ አላውቅም፤ ጠዋት ከመኝታዬ ስነሳ ቀሚሴን ስለብስ አቤቱ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን እንደዚህ አልብሰኝ እለዋለሁ፡፡ ውሃ አቅርቤ ፊቴን ስታጠብ አቤቱ የልቤን እድፍ በመንፈስ ቅዱስ አጥበህ ንጹህ አድርግልኝ እለዋለሁ፡፡እሳት አቅርቤ ብዙ እንጨት ጨምሬ ሲነድ ባየሁ ጊዜ አቤቱ ልቤ በፍቅረ መንፈስ ቅዱስ እንዲህ እንዲቃጠል አድርግልኝ እለዋለሁ፡፡ መልካም ሩዝ ቀቅዬ በስሎ በምበላበት ጊዜ አቤቱ ከረሀበ ነፍስ እንድድን መንፈሳዊ ምግብ አዘጋጅልኝ እለዋለሁ፡፡ ልብሴን አጥቤ በመተኮሻ ተኩሼ ቀጥ ሲል ባየሁት ጊዜ አቤቱ ቀጥ ያለና የቀና ልብ ስጠኝ እለዋለሁ፡፡ እንደዚህ እያደረግሁ ሥራዬንና ጸሎቴን በአንድነት እጨርሳለሁ እንጂ የተወሰነ የጸሎት ጊዜ የለኝም አለቻቸው፡፡
ምንጭ፡- ጎሀ ጽባህ ገጽ 97
✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧✧
(ሳናቋርጥ መጸልይ እንዳለብን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል "ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተፀምዶ መዋል አይችልም አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው ድምፅ ሳይኾን አሳብ ነው፤ እጅ ሳይኾን እደ ልቦናን ማንሣት ነው። ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፣ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከኾነ ጸሎትህ ሥልጡን ነው።")
👍 2
ወዳጄ ሆይ መልካም ወዳጅ ትባል ዘንድ
እግዚአብሔር አምላክህን ካላወቅክና ካልመሰልከው በቀር ባልንጀራህን፣ ወንድምህን፤ እኅትህን ከዛም አለፍ ሲል እናትህን አባትህን ከዚህም ሲከፋ የገዛ ሚስትህን ጤናማ በሆነ መውደድ ልትወዳቸው አትችልም፡፡ ስለዚህ ወዳጄ ይህን እርከን ተከትለህ ወደ እውነተኛው ወዳጅነት እለፍ፡፡ “በእምነት ላይ በጎነትን፤ በበጎነት ላይ እውቀትን፤ በእውቀት ላይ ራስን መግዛትን፤ ራስንም በመግዛት ላይ መጽናትን፤ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፤ እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማች መዋደድ፤ በወንድማማች መዋደድ ላይ ፍቅርን ጨምሩ” (2ጴጥ.1÷7) እንዲህ አድርጎ ራሱን በቅድስና ያበቃ ሰው ራሱን ከራስ ወዳድነት በጠራ መልኩ ይወዳል፡፡ ስለዚህም ባልጀራውንም መውደድ ለባልንጀራው መልካም ወዳጅ መሆን ይቻለዋል፡፡
ልጄ ሆይ....... ወጣትነት ፈትኖህ፤ለሥጋህ አድልተህ፤ነፍስህን አደከምካት ከአለም የኖርክበትን ዓመትህን ጥለኸው በንሰሐ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ..... በአዲስ ዓመት ለአምላክህ የሚገባህን ግብር ትፈፅም ዘንድ በፍቅሩ አፀድ እንድትገኝ ካለመታዘዘ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ....... በአፈር ከሚሸነፈው ሥጋዊ ዘርህ ወጥተህ ሰማያዊነትን ከሚያለብስህ ከማይጠፋው ሰማያዊ ዘር ክብረት ታደርግ ዘንድ ሰውን ካለመውደድ ጥላቻ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...... በምክንያቶች ተደልለህ አጽዋማትን ዘለህ፤ምስጋናን ነፍገህ፥አገልግሎትን ንቀህ ከዓለም ጫጫታ ውስጥ የዘፈቀውን ማንነትህ እንዳያጠፋህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...... ዲያቢሎስ በቃል እንዳያስትህ፤በማማለል እንዳይጠልፍህ የመንጋውን ጠባቂ ቃልን ስማ፤ የመታዘዝን በረከት ታገኝ ዘንድ ከትምህክትህ እንደ ዘመኑ አንተም ተለወጥ።
ልጄ ሆይ .....ቀናት ሳይሆን መንፈስህ ይለወጥ፤ፀሐይ ሳትሆን የህይወት ጀንበርህ ይለወጥ።
ልጄ ሆይ ......ዕለታት አይሰልጥኑብህ፤ ዘመናት እስከ ሞትህ ጥግ ድረስ እስኪገፉህ ሳትጠብቅ አንተም እንደ ዘመንህ ተለወጥ
ልጄ ሆይ .....የእግዚአብሔር ፍቅር ለተከፈተ ልብ ቸር ነው ። ርህራሄው ጥልቅ ነው ። በአምሳሉ ፈጥሮሃል እና እንዳትጠፋ አንድያ ልጁን ለሞት አሳልፎ እስከመስጠት የደረስ ጥልቅ ፍቅር አሳይቷል ። ስለዚህ ከዘመንህ ቀድመህ ተለወጥ።
ልጄ ሆይ ...አዛኝቷን ተለማመን፤መላአኩን ተማለደው ፤ቀደምት ቅዱሳን አባቶችህን ጥራ፤ ፃድቃንን ዘክር እንጅ ላለመለወጥ ተማምለው ቀናት ብቻ ከሚለወጥባቸው ሰልፈኞች ተርታ አትገኝ
ይህን ዘመን ከወትሮ በተለየ ወደ እግዚአብሔር ቀርበን በንስሐ አምላክን የምንማጸንበት ጥሩ እና መልካም ዘመን ያድርግልን🙏🙏🙏
👍 3❤ 2
"መንፈሳዊ ብቃት፥ የማይደረስበት እሩቅ፣ ወይም ከሰው ልጅ ችሎታ በላይ ነው፥ ብለን ማሰብ የለብንም። ሰዎች ባሕር አቋርጠው የሌላ ሀገር ፍልስፍና ሊማሩ ይሄዳሉ። የእግዚአብሔር ከተማ ግን በልባቸው ውስጥ ነው። እግዚአብሔር የሚጠብቅብን መልካም ምግባርም እዚያው ልባችን ላይ ነው ያለው። የሚጠበቅብን መሻታችንን ከእግዚአብሔር መሻት ጋር ማስማማት (አንድ ማድረግ) ብቻ ነው።"
🔥🔥🔥የአባ እንጦንስ ምክር...🔥🔥🔥
❤ 2
"አቤቱ ሆይ ከሰማየ ሰማያት ወርደህ በማህፀኗ ማደርህን ድንግል ስትሆን ከእርሷ መወለድን ንጽህትም ስትሆን በጡቷ ማደግህን አስብ! አቤቱ ሆይ በጎል መጣልህን በጨርቅ መጠቅለልህን አስብ! አቤቱ ሆይ ይህንን ሁሉ አስበህ እኔን ባሪያህን ስለ ኃጢአቴ አትናቀኝ! በማዳንህ እርዳኝ በመድኃኒትነትህም ጋሻ ጋርደኝ፡፡
አቤቱ ሆይ ስለ ወለደችህ ማርያም አማላጅነት ስለ አሳደጉህ ጡቶቿ ስለ ሳሙህ ከንፈሮቿ ስላቀፉህ እጆቿ ስለ ተቀበለህ ጎልበቶቿ አካልም ይሆን ዘንድ ስለነሣኸው ነፍስና ሥጋዋ እርዳኝ ጠብቀኝ፡፡ አንጋጥቼ እንዳላፍር አምኜህ ተስፋ እንዳልቆርጥ አድረገኝ፡፡"
መፅሐፈ አርጋኖን
❤ 1
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.