The Ethiopian Economist View
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
ወደ ቻይና የሚደረግ የንግድ ልውውጥ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ብቻ እንዲሆን የሚያዝ ህግ አለ! ይህ ህግ የግል ባንክ ደንበኞችን ወደ ሌላ አማራጭ እየገፋቸው አይደለም? በቻይና የኢትዮጵያ የሰሊጥ ምርት ድርሻ ከፍተኛ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ወደ 5% ዝቅ ብሏል! ከዚህ ምክንያት መካከል አንዱ የኢትዮጵያ እና የቻይና ንግድ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል ግዴታ መሆን አለበት ከሚለው ክልከላ ጋር ግንኙነት የለውም? ይህንን በተመለከተ የሚከተለውን ትንታኔ ይመልከቱ!
ለኢንቨስትመንት እና ለንግድ ተመራጭ የሆኑ ዘርፎች| ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ ካፒታል ሊሰሩ የሚችሉ ቢዝነሶች! በዚህ ወቅት ከፍተኛ ካፒታል ያለውም ሆነ አነስተኛ ገንዘብ ያለው ሰው የኑሮ ውድነት/የዋጋ ንረትን ተቋቁሞ ለመዝለቅ ገንዘብ ከመያዝ ይልቅ ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎቱ አድጓል! ከኢንቨስትመንት ውሳኔ በፊት ከግምት መግባት ያለባቸው ጉዳዮች ብዙ በመሆናቸው ሰዎች በቀላሉ ኢንቨስትመንት ላይ መሳተፍ ቢፈልጉም እየቻሉ አይደለም! ኢንቨስትመንት ላይ ለመሳተፍ የወሰኑ ሰዎች ቢሆኑ እንኳ የትኛውን ሴክተር እና ቢዝነስ ልምረጥ? በምን ያህል ካፒታል ልጀምር? የሚለው ጥያቄ መልስ በቀላሉ የሚገኝ አይደለም! በዚህ ቪዲዮ ከገበያው እና ከመጪ ጊዜ አዝማሚያ በመነሳት ባላችሁ ካፒታል ልክ ኢንቨስት ብታደርጉ ልትሰሩ እና ልታተርፉ የምትችሉባቸው በርካታ ዘርፎችን በምሳሌ እናቀርባለን! እንደምትጠቀሙበት አምናለሁ!
በኢትዮጵያ የባንኮች የሃብት መጠን ከ3.2 ትሪሊዮን ብር በልጧል (ከ2015 አንፃር በ2016 ከ400 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አለው)። ከ30 ንግድ ባንኮች ውስጥ የብሔራዊ ባንክ 5 ቢሊየን ብር የተቀማጭ ገደብ ያሟሉት 17 ባንኮች ሲሆኑ 13 አዲስ እና ነባር ባንኮች ዝቅተኛ የተቀማጭ ሃብት ከቀን ገደቡ በፊት አላሟሉም! በ2016 የባንኮቹን የሃብት (Asset)፤ መጠን፤ በብሄራዊ ባንክ የተቀማጭ ካፒታል መጠን እና በብድር ክምችት አቅም ከፍተኛዎቹን በደረጃ ተመልከቱ! የዚህ መረጃ በቀጣይ የአክሲዮን ገበያ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ልትጠቀሙበት ትችላላችሁ.....
በ2016 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ Busy የነበረበት ዓመት ነው! ብዙ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ፖሊሲዎች ወጥተዋል፤ ተሽረዋል፤ ተሻሽለዋል.....9ኙን እንመለከታለን! በ2017 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሊገጥሙት የሚችሉት እና ሊያከናውናቸው ከሚችላቸው ጉዳዮች.....ዋና ዋናዎቹን እንመለከታለን! በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ስጋት የፈጠሩ በቀጣይ በእድል እና በስጋት ከሚነሱ ብዙ ጉዳዮች......ዋና ዋናዎቹን እንመለከታለን! በዚህ ቪዲዮ የ2016 የኢኮኖሚ (Review) እና የ2017 የኢኮኖሚ (Projection) ዙሪያ ሃሳብ እናቀርባለን ተከታተሉት!
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.