cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ዮራቶራድ

ፍቅር፣ እምነት፣ጥበብ በግጥም የሚቀርብበት እንዲሁም አዳዲስ ታሪኮች የሚለቀቁበት ቻናል ነው. በንባብ ክህሎታችን አብረን አለምን እናያለን

Show more
Advertising posts
960
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2830 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from ጦብያ
ፀጉረ ልውጡ ክፍል 12 በዛሬው ዕለት ይለቀቅልን የምትሉ
Show all...
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼           ፳፻፲፯ ዓ.ም ዘመነ ማቴዎስ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 መኑ ውእቱ ብእሲ ዘይፈቅድ ሐይወ? ወያፈቅር ይርአይ መዋዕለ ሠናያተ? ክላእ ልሳነከ እምእኩይ፤ ወከናፍሪከኒ ከመ ኢይንብባ ጕሕሉተ። ተገሐሥ እምእኵይ ወግበር ሠናየ፤ ኅሥሣ ለሰላም ወዴግና። መዝ. ፴፫፥፲፪-፲፬ እንቋዕ ለሐዲስ ዓመት ፳፻፲፯ ዓ.ም በሰላም ወበጥዒና አብጽሐክሙ አብጽሐነ። እንቋዕ እምዘመነ ዮሐንስ ኀበ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አዕደወነ። ናፍቅር ሰላመ ወንግበር ሠናየ ከመ ንርአይ ዘመነ ሠናያተ። ሠናያት ምግባረ ሰብእ ይወልዱ ዘመነ ሠናይ። ያርእየነ ሰላማ ወፍቅራ ለቤተክርስቲያን ቅድስት ወለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ጽንዕት። ሠናይ ሐዲስ ዓመት ይኵን ለክሙ ፩ሩ ለመስከረም ፳፻፲፯ ዓ.ም 🌼🌼🌼  🌼🌼🌼  🌼🌼🌼 🌼🌼🌼 🌼🌼🌼   🌼🌼🌼      🌼      🌼🌼🌼      🌼        🌼    🌼       🌼              🌼   🌼 🌼      🌼 🌼         🌼             🌼 🌼      🌼    🌼             🌼             🌼 🌼       🌼    🌼            🌼             🌼🌼 🌼🌼🌼  🌼🌼🌼  🌼🌼🌼   🌼🌼🌼
Show all...
ዓመት በመጣ በሄደ ቁጥር አቤት መከራችን የወደቀ ስንቆጥር ዘመን አዲስ ቁጥር ብቻ ሆኖ እኛው ግን እዛው ግፋችን መዝኖ ደግሞ ተስፋ ይሉትን ቃል በልባችን ይዘን ይኸው ዛሬ ድረስ እንቁዋን ስንመኝ ጣጣዋ እየደረሰን ግና በመዘመን ዓለም እኛጋ ፍቅር የለም እኛጋ ሰላም የለም ምክንያቱም ነውር ነው መተለም ብቻ ተስፋ ነውና የኑረታችን ጥጉ እናንጋጥጣለን ለፈጣሪ ደጉ. እናም አሜን በይ እንቁሽ በአዲስ ዓመት ጣጣሽ በወርሀ ክረምት ይሁን አሜን በይ በእምነት አሜን እንኳን አደረሰን ልጅ ዳን የእናቱ ልጅ @yoratorad777
Show all...
መስከረም 1 ቀን 1914 ዓ.ም #በዛሬዋ_ዕለት ከዛሬ 103 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የዓለም አቀፉ የእግርኳስ ማህበር (FIFA) የስራ አስፈፃሚ አባል ፣ የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ፕሬዚዳንት የነበሩት ታላቁ የስፖርት ሰው ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሠማ የተወለዱበት ዕለት ነበር። 👇👇 www.facebook.com/share/p/rnwdp8e5YyY3ATGt #ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala youtube.com/@TariknWedehuala11
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
ጳጉሜ 5 ቀን 1952 ዓ.ም #በዛሬዋ_ዕለት ከ 64 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ በቂላ በሮም ኦሎምፒክ ላይ በባዶ እግሩ የማራቶን ውድድሩን በ (2:15:16:2) ሰዓት በመግባት የዓለምን ክብረ ወስን በመስበር እና ለኢትዮጵያም ሆነ ለጥቁር አፍሪካውያን የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘበት ዕለት ነበር። በወቅቱ ያለ ጫማ በባዶ እግሩ የተወዳደረበት ምክንያትና ለምን እንደመረጠ የተጠየቀው አትሌት አበበ.......“ አገሬ ኢትዮጵያ ሁል ጊዜ በቁርጠኝነት እና በጀግንነት አሸናፊ መሆኗን ዓለም እንዲያውቅ እፈልግ ነበር ”.....ሲል ተናግሯል። ውድድሩ ከተጠናቀቀ በኃላ ማለትም አርብ መስከረም 5 ቀን 1953 ዓ.ም አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ አዲስ አበባ ሲገባ በብዙ ሺ የሚቆጠር የከተማው ነዋሪዎች በድሮ አይሮፕላን ማረፊያና በሚያልፍበት መንገድ ላይ ሆነው ደማቅ አቀባበል ተደርጎለት ነበር፡፡ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም የቀድሞ ቤተ መንግስት የነበረው የዛሬው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በደማቅ ዝግጅት ተቀብለው የኢትዮጵያ የፈረሰኛ ኮከብ ኒሻን ለአትሌት አበበ ቢቂላ ሽልማት አበርክተውለታል፡፡ በወቅቱ ፓሪ ማች የተባለው ታወቂ የፈረንሣይ መጽሔት ጨምሮ ኢንተርናሽናል ጋዜጦች ወኪሎቻቸውን አስቀድመው ወደ አዲስ አበባ ልከው ስለነበር ሁኔታና የተመለከቱትን በአድናቆት ለዓለም ማህበረሰብ ዜናውን ዘግበውታል፡፡ #ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala youtube.com/@TariknWedehuala11
Show all...
1
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌻2017🌻መልካም🌻አዲስ አመት🌻             🌻🌻🌻      መልካም🌻አዲስዓ መት   መልካም🌻     አ🌻ዲ🌻ስ መልካም 🌻        ዓ🌻መ🌻ት ለወዳጄ 🌻          ዓ🌻መ🌻ት 🌻🌻🌻🌻        አ🌻ዲ🌻ስ                          ዓ🌻መ🌻ት                        አ🌻ዲ🌻ስ                      አ🌻ዲ🌻ስ                    ዓ🌻መ🌻ት                  አ🌻ዲ🌻ስ             ዓ🌻መ🌻ት         አ🌻ዲ🌻ስ       ዓ🌻መ🌻ት    አ🌻ዲ🌻ስ ዓ🌻መ🌻ት               🌻🌻🌻🌻 🌻መ🌻ል 🌻ካ🌻ም🌻🌻🌻🌻 🌻አ🌻ዲ🌻ስ🌻ዓ🌻መ🌻ት 🌻             🌻   🌻   🌻       🌻መል🌻🌻🌻ካም🌻   አ🌻ዲ🌻ስ          ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ            ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ              ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ              ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ              ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ              ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ              ዓ🌻መ🌻ት አ🌻ዲ🌻ስ            ዓ🌻መ🌻ት   አ🌻ዲ🌻ስ          ዓ🌻መ🌻ት        🌻መ🌻ል🌻ካ🌻ም🌻              🌻  🌻  🌻                                      🌻🌻አዲስ            🌻🌻🌻አመት         🌻🌻መ🌻ልካም    🌻🌻አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት             አዲስ🌻ዓመት   🌻መልካም  🌻 አዲስዓመት   🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻    አዲስዓመት🌻ለወዳጄ🌻🌻   🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻 🌺 ይ🌻ህ🌻🌻አ🌻መ🌻ት🌻🌼 የ🌻ሰ🌻ላ🌻ም🌻🌻አመት🌻🌷 የ🌻ፍ🌻ቅ🌻ር 🌻🌻አመት🌻🌷                                የ🌻ሞገስ 🌻                                        የ🌻ክብር  🌻                                     የ🌻ሹመት🌻                            የ🌻ታላቅነት🌻                                     🌻ዓመት 🌼               🌻🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌻🌷🌹🥀               🌻ይ🥀ሁ🌹ን🌷ላ🌼ች🌹ሁ 🌾                  🌻🥀 🌼    🥀🌹🌺   🌷                                  🌻የበረከት 🌻                        🌻የሹመት 🌻                       🌻የምርቃት 🌻                      🌻የመግዛት 🌻                     🌻የከፍታ 🌷🌻                     🌻ዓመት 🌷🌻                     🌻 ይሁን 🌻🌻                    🌻🌻🌻🌻🌻                    🌻🌻🌼🌼🌼 🇪🇹ሀገራችን ሰላም የምትሆንበት 🙏 🕊🌻🌻 🌻🌻🌻  ያሰብነው የሚሳካበት          🌻🌻 🌻🌻🌻                                         🌻🌻 🌻የካሳ🌻የሰላም🌻የጤና🌻የበረከት🌻🌻 🌻🌹⁣🌾ዓመት 💐🌷ይሁንልን።🌻🕊🌻🌻 @abusha_16
Show all...
* ፀጉረ ልውጡ * ክፍል ሶስት ....እንደልማዴ ማልጄ ተነሳሁ የፀሀይ ብርሀን በመጋረጃው ክፈተት በመስኮት በኩል ወደ መኝታ ክፍሌ ዘልቃለች 12:30 ይላል ሰዓቱ ቁርሴን ከማብሰሌ በፊት የስራ ልብሴን ከቁም ሳጥን ለማውጣት እጀታውን ይዤ በሩን ከፈትኩት በስተግራ ባለው መዝጊያ ግርጌ በመስታወቱ እና በመዝጊያው ክፍተት መሀል የተሸጎጠ የቤተሰብ ፎቶ አየው ብዙም ግድ አልሰጠኝ ልቤሴን አውጥቼ ከመኝታዬ ላይ አኖርኩት በነገራችን ላይ ከአንድ ሻንጣ ፍራሽ አልባሳት በስተቀር ሌላ ምንም ንብረት የለኝም ከነ ሙሉ ዕቃው ነው የተከራየሁት ከረባት ረስቼ ስለነበር ወደ ቁምሳጥሉ ተመለስኩ ከከረባቶቹ መሀል በኮብራ እባብ ቅርፅ የተሰራ ከረባት ላይ አይኔ አረፈ ቀጥኖ ያለው የከረባቱ ክፍል ጭራውን ይወክላል ከታች ያለው ደግሞ ሊናደፍ እንደተዘጋጀ ይመስላል ብቻ ቀርቦ ላላየው ጨርቅ አይመስልም አይኔ ተምዘግዝጎ ከቅድሙ ፎቶ ላይ ሰከነ ከተሸጎጠበት ስቤ አወጣሁት የሀያ አራት ሰዎች ምስል አለበት ግን መልካቸውን በውል መለየት አልቻልኩም ከምስሉ ጀርባ ላይ # የቃልኪዳን_ቤተሰቦች የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበታል ፎቶውን ወዳገኘሁበት ስፍራ መልሼ መዝጊያውን ዘጋሁት...ዛሬ የመስራት ሞራሌ ሞቷል አለቃዬ ጋር ደውዬ ፍቃድ ልጠይቅ ወሰንኩኝ ስልኬን አንስቼ ለመደወል ስል ምንም አይነት ኔትወርክ አጣሁ ከቤት ወጣሁና በአቅራቢያዬ ከሚገኝ ጓዳና ላይ ወጥቼ ስሞክር ሰራ ያለውን ሁኔታ አስረዳሁትና ስልኩን ዘጋሁ ከኔ መቶ ሜትር ያህል ተስፈንጥሮ በሚገኝ የዛፍ ጥላ ስር ሶስት አዛውንቶች ቁጭ ብለዋል አንዳቸው ላንዳቸው ምንም አይባባሉም ዞረውም አይተያዩም ግን ሶስቱም እኔን ያዩኝ ነበር ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍራቸው ቀይ ለብሰዋል ዱላቸው የዝንብ ማባረሪያ ጭራቸው ጫማቸው ባጠቃላይ ሁሉም ቀይ ነበር እጅግ ግራ ተጋባው መንገደኞች ወደ መኖሪያዬ እየጠቆሙ ጭንቅላታቸውን በሀዘን እየነቀነቁ ወደ ሰማይ አምላክ ሲያዩ አስተዋልኩ የዚህ ቤት ነገር ይብስ ከነከነኝ... ....መረጃ አገኝ እንደው ልፈልግ ወደ ቤቱ ተመለስኩ ቁምሳጥኑን ከፍቼ በግርጌ ያሉት መሳቢያዎች ከፈትኳቸው ከአንደኛው መሳቢያ እጅግ ትልቅ አልበም አገኘው ከላዩ የሰፈረውን አቧራ በእስትንፋሴ እያፀዳው ወደ ጠረጴዛው አመራው ከአንዱ ወንበር ቁጭ ብዬ ማየት ጀመርኩ በምስሉ ላይ የተስተካከለ የፊት አቋምና የጭንቅላት ቅርፅ ያለው የለም በሙላ ኮስታራና ቁጡ ይመስላሉ ለፎቶ ብለው እንኳ ፈገግ አላሉም...እስካሁን ካየሗቸው ፎቶዎች አንድ ነገር አስተዋልኩ ሁሉም በግራ እጃቸው ላይ የነጭ ጨሌ አምባር እና የግራ አይን ቅንድባቸው ግማሽ ነበር ግራ የሚያጋቡ ቤተሰቦች ወይ ስብስቦች የማየው ነገር ትንሽ አደከመኝና ነቃ ለማለት ፎቶውን ትቼ ሻይ ለማፍላት ወደ ማጀት ሄድኩ ማንቆርቆሪያ ስላልነበረኝ ቤቱ ውስጥ አይጠፋም ብ ፍለጋ ገባሁ በዕቃ የተሞላ ተለቅ ያለ በርሜል ሳይ ጠጋ አልኩኝ በፌስታል የታሰራ ሃያ አራት የመጠጫ ዋንጫዎች አገኘው ማንቆርቆሪያ ግን አልነበረም በምትኩ ተለቅ ያለ ጣሳ አገኘው አጠቤ ሻዩን ጣድኩኝና ወደ ፎቶው ተመለስኩ ከሃያ አራቱ ቤተሰቦች እናትና አንዲት ሴት ብቻ እንስቶች ነበሩ ሌሎቹ ጎረምሶች ናቸው የድካም ስሜቱ ሊለቀኝ ስላልቻለ ፎቶውን ከድኜ ቦታው መልሼ ወደ ጣድኩት ሄድኩኝ ፈልቶ ስለነበር አውረድኩት እና የሻይ ብርጭቆ አዘጋጀሁ ሻዬን ይዤ ወደ ሳሉን ቤት ሄጄ ቲቪው ፊት ለፊት ካለው ሶፋ ላይ አረፍ አልኩኝ....ይቀጥላል Join us 👉 @yoratorad777
Show all...
👍 1
ልብ አንጠልጣይ ታሪኮች: * ፀጉረ ልውጡ ክፍል ሁለት ......በሩን ከፍቼ ስወጣ አካራዬ ነበሩ እንዴት አደሩ ብዬ ሰላምታ አቀረብኩላቸው እግዜር ይመስገን ልጄ እንዴት አደርክ አሉኝ አንገታቸውን ወደ ውስጥ እያሰገጉ በጠዋት ቀሰቀስኩህ እንዴ አሉኝ አረ ምንም አይደል አልተኛሁም ነበር አልኳቸው ግን ፊታቸው የሆነ ነገር እንደጠበቁና እንዳላገኙ ያሳያል ምን እንደሆን ግን እንጃ በል ደህና ዋል አሉና ሳይገቡ ከደጅ ተመለሱ ግን ደጋግመው እየዞሩ ያዩኝ የከነከናቸው ነገር አለ...በዛው ወደ መኝታዬ ሳልመለስ ቀኔን ጀመርኩ በጉልበቴም ተንበርክኬ እንዲህ አልኩኝ ጨለማዬን ያነጋህ የአብ ልጅ መድሀኒዓለም ተባረክ አልኩኝ ድንገት የሚያጓራ የሚመስል ድምፅ ሰማው ከተንበረከኩበት ስነሳ ድምፁ ጠፋ ፍርሀቴ የፀጠረው ነው ብዬ ብዙም ሳልጨነቅ አለፍኩት ያ ሰው ድንገት ካለ ብዬ በመስኮት አሻግሬ ተመለከትኩ የለም ነበር...ዛሬ አዲስ ቀን ነው ሰንበት ነች ቁርሴን ላበስል ወደ ማጀቱ ሄድኩኝ የምወደውን መዝሙር እየዘመርኩኝ ነበር ከፍሪጅ ውስጥ አራት እንቁላል አወጣው የወንደላጤ ቁርስ ሰርቼ ተመገብኩ ትንሽ እረፍት ካረኩኝ በሗላ ልብሴን ቀያይሬ ወደ ቤተክርስቲያን አመራሁ ቀኑ ደስ ይል ነበር ብሩህ እና አዲስ ቀን...ከቤተክርስቲያን ፀልዬ የቃሉን ትምህርት ተምሬ እንደጨረስኩ በስልኬ መዝሙር ከፍቼ ኤርፎን ሰክቼ በዝግታ ጉዞዬን ጀመርኩ ከፊት ለፊቴ ከሰማዩ ፀዳል ወንዝ ተጨልፎ የተደፋባት የመሰለች ደመ ግቡ ውብ ሴት ተመለከትኩ አይኗ የማለዳን ፀሀይ ያስንቃል ሽፋሽፍቷ እንደ ሮም ወታደር ጦር አይኗን ሊታደግ የቆመ ዘብ ይመስላል አፍንጫዋ ቀጥኖ ስልክክ ያለ ነው ከናፍርቶቿ ከማር ሰፈፍ ይልቅ ያጓጓሉ ብቻ በአጭሩ ክንፍ የሌላት መልአክ ነው ምትመስለው አይኔን አላመንኩም ተላለፍን ዞሬ አየሗት ደግሜም ቆሜ አየሗት አረማመዷ እንደ ብዙ ውሃዎች ድምፅ ነው ፀጉሯ ከአባይ ፏፏቴ ይማሰላል ዳሌዋ ሲተራመስ ምድርና ሰማይ ቦታ ሚላወጡ ይመስላል እጅግ ግሩም ፍጡር ነች በውበት ዛሬ ገና ተገረምኩኝ ከእይታዬ ስትርቅ ፊቴን ወደ መንገዴ መልሼ መዝሙሬን እያዳመጥኩ ወደ ቤቴ አመራሁ...ፀሀይዋ ትጋረፍ ስለነበር እርምጃዬን ጨመርኩ ወደ ቤቴ አቅራቢያ እንደደረስኩ አንድ ነገር አስተዋልኩ ካሉት ቤቶች የኔ ቤት ራቅ ይላል ጎረቤት ሚባል የለም እንደገናም በትላልቅ የወይራና የሾላ ዛፎች ተከቧል አስገረመኝም ጥያቄም አጫረብኝ ደስ የሚል አየር አለው ግን ለምን ከሰዎች ቤት ራቀ ሰዎችስ ለምን እየመጡ በዛፎቹ ጥላ ራሳቸውን ዘና አያረጉም እያልኩ ብዙ አሰብኩ ብዙ ጠየኩ ግን መላሽም ሀሳብ ተካፋይም የለም...ከመኖሪያዬ አጠገብ ከሚገኙት ዛፎች መሀል ለመግባት ወሰንኩኝ ውስጡ ብዙ ብርሀን የሚገባበት አይመስልም ይጨልማል የፀሀይ ጭላንጭል የዛፎቹን ውዝዋዜ ተከትሎ አልፎ አልፎ ይገባል በዝግታ ኸደ ውስጡ ነጎድኩ ግን ምንም የለም ፀጥ ያለ ነው የሰው ልጅ ፀጉር የሚመስል በአንድ ስፍራ ተከምሯል እጅግ የሚሰነፍጥ ሽታ ውልብ ብሎ ጠፋ አሁንም ወደ ውስጥ እየተጓዝኩ በእርምጃዬ መሀል እግሬን የሆነ ነገር ጠለፈኝ አጎንብሼ ሳይ የእግር አጥንት ይመስለኛል በደንብ ሳላየው ከሗላዬ ሊይዘኝ የመጣ ነገር ያለ የሚመስል የኮቴ ድምፅ ስሰማ በቅፅበት ፊቴን አዞርኩ የቅጠል ብናኝ እንጂ ሰው አልነበረም እጅግ የሚሰቅ ቀጭን ድምፅ ጫካውን አናወጠው በስመ አብ አልኩኝ ድምፁ ጠፋ ቀስ ብዬ ወደመጣሁበት ተመለስኩ የዚ አካባቢ ነገር እጅግ እያስፈራኝም እየደነቀኝም ነው ግን በአምላኬ ተምኜ ፈርቼ አላውቅም እሱ ከሁሉ በላይ ነው....የድሮ የቤት አሰራርን የተከተለ ጂ ፕላስ ዋን ነው ምኖርበት እጅግ ሰፊ ቦታ ላይ ነው የተሰራው ግን ለምን ሰው ዝር አይልበትም ግን ከ አካራዬ አቶ አባተ ውጪ ማንም አይመጣም ይሄን ሚስጢር እግዜር ነው ሚያውቀው...ወደ ውስጥ ዘልቄ ሻወር ወሳስጄ ምሳዬን በልቼ የማታውን እንቅልፍ አሁን ለማካካስ ተኛሁ እጅግ ደስ የሚል እንቅልፍ ወሰደኝ እሁድ መልካም ነበረች ....ይቀጥላል.... https://t.me/yoratorad777
Show all...
ዮራቶራድ

ፍቅር፣ እምነት፣ጥበብ በግጥም የሚቀርብበት እንዲሁም አዳዲስ ታሪኮች የሚለቀቁበት ቻናል ነው. በንባብ ክህሎታችን አብረን አለምን እናያለን

👍 1
* ፀጉረ ልውጡ * ክፍል አንድ አጭር ልብ ወለድ ፡ ዕለቱ ቅዳሜ ነው ፀሀይ ገና ወደ ምድር እያዘቀዘቀች ነው ማልዶ የመነሳት ልማድ ስላለብኝ ያለ እንቅልፍ ከመኝታዬ ውስጥ መተኛት አልቻልኩም በዕንቅልፍ የዛለ ሰውነቴን እያሳሳብኩ ወደ መስኮቴ ተጠግቼ መጋረጃው ገለጥኩት ፊቴን ወደ መኝታዬ መለስኩና በውል ሳላስተውል ያየሁትን ሰው ለማየት ወደ መስኮቴ ተመለስኩ ግን ማንም አልነበረም ሰው እንዳየው እርግጠኛ ነኝ ነጭ ጥጥ የመሰለ ፀጉር ያለው በመስኮቴ ትዩዩ ነበር...በስመ አብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ብዬ ልቤን ያዝኩት ራሴን አረጋግቼ መኝታዬን አነጣጥፌ ወደ ሳሎን አመራሁ የግድግዳ ሰዓቴ 12:30 ይላል ቲቪ ከፈትኩና ሶፋ ላይ ቁጭ አልኩኝ ድንገት ቲቪ ውስጥ በመስኮት ያየሁትን ሰውዬ አየሁት የማረገው ጠፋኝ አይኔን ማመን አልቻልኩም ቲቪውን አጠፋውና ከቤት ወጣሁ ያየሁትን ለማን ብናገር ማን ያምነኛል ይብሱኑ ይሳቅብኛል ብዬ ዝም አልኩኝ...ሰዓቱ ወደ ምሽት በተቃረበ ቁጥር ወደ ቤት ለመግባት ፈራ ጀመር...ለሰፈሩም ለአካባቢውም አዲስ ነኝ የማውቀው የሚያውቀኝ የለም ከደጅ ሆኜ የለሊት ጅብ ራት ከምሆን ገብቼ የሚፈጠረውን ልይ ብዬ ወሰንኩኝ ጀንበር ለምሽቱ ስፍራዋን ለቃ አሸለበች ለኔ ደሞ ፍርሀትን ሸልማኝ...የሚሆነውን በግልፅ ለማየት በመኝታ ቤቴ ውጪ ሚገኘውን መብራት እና የሳሎኑን መብራት አብርቼ ትራስ ከግድዳው አዋድጄ ፈጥጬ ቁጭ አልኩኝ እስትንፋሴም ፀጥ ያለ እስኪመስል በዝግታ ነበር ምተነፍሰው ሳላስበው እንቅልፍ ሊያሸልበኝ ሲል የፋጭ የቢላ ድምፅ ከሰመመን አነቃኝ ቢላው ያለ ማቋረጥ ይሞረዳል ይፋጫል በብርድልብሴ ጥቅልል አልኩኝ ልብ ምቴን መቆጣጠር አቃተኝ ወንድነቴ ጠፋ ፈራሁ እንደምንም ብዬ ከተሸፈንኩበት አንገቴን ቀና አድርጌ ሳይ የጓዳው በር ላይ ትልቅ የሰው ጥላ አለ ከመቅፅበት ተሸፈንኩኝ በላብ ጎርፍ ተጠመኩኝ ምሞትም መስሎኝ ንስሀ ገባሁ ምንም እንኳ አንደበቴ እየተንቀጠቀጠ ሙሉ ሀጢያቴን ባልናዘዝም የሞት ሞቴን ድፍረቴን ሁላ ሰብስቤ ቀና አልኩኝ ግን ያ ትልቅ ጥላ አልነበረም ኮቴ ሳላሰማ ወደ መዝጊያው ተጠጋው ከጊዜ ብዛት ከማርጀቱ የተነሳ በሰፈረበት ሽንቁር አጮልቄ ሳይ የሳሎኑ በር ተዘግቶ ፀጥ ረጭ ብሏል በሩን ከፍቼ ቀስ እያልኩኝ ወደ ሳሎኑ በር ተጠጋው ዝግ መሆኑን አረጋገጥኩ የውስጥ የነበረው ነገር ቤት ገባ ብዬም አሰብኩ ፊቴን ወደ ሗላ መልሼ ስራመድ እግሬን እርጥበት ተሰማኝ መጀመሪያውኑ ደንግጬ ስለነበር እንጂ ያላስተዋልኩት ሳሎኑ በደም ተጨማልቋል አጎንብሼ አየሁት እሪታዬን አቀለጥኩት ወደ መኝታ ቤቴ በፍጥነት ገባው ደሙን ከእግሬ ላይ ለመጥረግ ጨርቅ አንስቼ እግሬን ሳይ ምንም አይነት ደም አልነበረውም በጣም ገረመኝ ደም አላየሁም ማለት ነው ብዬ ወደ ሳሎን ተመለስኩ ግን ቅድም እንዳየሁት የደም ጭምልቅ ነበር...ልክ ለሊት 6:30 ይል ነበር ሰዓቱ በማለዳ ድንገት አከራዬ ከመጣ ብዬ ኬት እንደመጣ ማላውቀውን ደም ወደ ማፅዳት ገባሁ ውሀውን ወደ ሽንት ቤት እየጨመርኩ አፀዳሁት ገላዬን ታጠብኩና ወደ መኝታዬ አመራሁ ወዲያው እንቅልፍ አሸለበኝ....ማለዳ ላይ ደጄ ተቆረቆረ በውል ካልተኛሁት እንቅልፍ ባንኜ በሩን ስከፍት.....ይቀጥላል.... Join us @utorrr @utorrr
Show all...
👍 1
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.