✝️ተግባራዊ ክርስትና ቻናል✝️
ይህ ቻናል በዋነኝነት በዘር፣በራስ ሐጢያት እንዲሁም በቅንአትና በምቀኝነት በሰውነታችን ሸምቀው ፍልሚያ ለገጠሙን ጠላቶቻችን እርኩሳን መናፍስት የመልስ ምት የምንሰጥበት እግዚአብሔርን አምነን ከእስራታቸው የምንወጣበት ድንግል ማርያምን አማላጅ አርገን የምንክድበት መላእክትን ተራዳኢ አርገን ቅዱሳንን ይዘን ከመንገዳችን የምናስወጣበት ከስም ወደ ተግባር ኦርቶዶክሳዊነት የምንመጣበት የተግባር ቤታችን ነው።
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
ይህ ግሩፕ በ መልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ እና በመምህር ተስፋዬ አበራ አማካኝነት ስለመናፍስት ውጊያና የአጋንንታዊን ሴራ በማወቃችን እርስ በእርስ የምንማማርበትና የምንድንበት እንዲሁም ከአለማዊ ሴራ በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ የምንነቃበት ነው። የማዳመጥ ጊዜ ላይ ነን!!በስግደት ከኛ ጋራ አብራችሁ መበርታትና ፈጣሪን በስግደት ማመስገን ከፈለጋችሁ
https://t.me/Lemelame_4@getemegn1991
Join this channel to get access to perks:
https://www.youtube.com/channel/UC2Ra_Irca5eETTIdS2bz83Q/joinመስከረም ፲በዚህች ዕለት ጼዴንያ በምትባል አገር ሥጋ የለበሰች ከምትመስል፤ ከሠሌዳዋም ቅባት የሚንጠፈጠፍባት የእመቤታችን የድንግል ማርያም ሥዕል ተዐምር ተገለጠ። ይህችን ሥዕል የሳላት ቅዱስ ሉቃስ ነው። ወደ ጸዴንያ እንዴት መጣች ቢሉ፤ አንዲት ማርታ የምትባል ሴት ነበረች በቤቷም እንግዳ ትቀበል ነበር። ድንግል ማርያምንም አብዝታ ትወዳት ነበር። በአንዲት ቀንም ስሙ ቴዎድሮስ የሚባል መነኩሴ በእንግድነት መጣ። በማግስቱ ስትሸኘው ወዴት ነህ ብላ ጠየቀችው። እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም እንደሆነ ነገራት። እርሷም ሲመለስ የእመቤታችንን ሥዕል አምጣልኝ አለችው። ከዚህም በኋላ ከቦታው ደርሶ ሥዕሏን ሳይገዛ ተመለሰ፤ በመንገድም ሥዕሏን ለምን አልገዛህም? የሚል ድምጽ ሰምቶ ተመልሶ ገዛ። በጎዳናው እየተመለሰ ሳለም የሚያስፈሩ ወንበዴዎች፤ ኋላም አንበሳ ገጠመው፤ የያዛት ሥዕልም ቃል አውጥታ አዳነችው። አባ ቴዎድሮስም ይህን ድንቅ ተአምር ባየ ግዜ ሥዕሏን ወደ ሀገሩ ሊወስዳት ወደደ። በሌላ ከተማም አድርጎ ሊሄድ መርከብ ተሳፈረ። በመርከቧ ሳለም ታላቅ ነፋስ ተነስቶ አቅጣጫውን አስቀይሮ ወደ ጸዴንያ ወሰደው። ኋላም ቢመሽበት ማርታ ቤት ሄደ እራሱን ግን አልገለጠም። በማግስቱም ተሰውሮ ከከተማው ሊወጣ ቢሞክር መውጫው ጠፍቶት ሲዞር ውሎ ተመለሰ። እንዲህም እያለ ሶስት ቀን ሆነው። ማርታም ይህን ተመልክታ ምን እንደሆነ ጠየቀችው። እርሱም ሁሉንም ነገራት። በኋላም የመነኩሴውን እጅና እግር ስማ ሥዕሏን ተቀበለች። በታላቅ ክብርም አስቀመጠቻት። ያም መነኩሴ እስከሚሞትበት ቀን ድረስ የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ሥዕል እያገለገለ ኖረ። የእመቤታችን በረከት ይደርብን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Join this channel to get access to perks:
https://www.youtube.com/channel/UC2Ra_Irca5eETTIdS2bz83Q/joinYour current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.