cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA አዲስ ሪፖርተር - NEWS ዜና

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

Show more
Advertising posts
938
Subscribers
-124 hours
+267 days
+20730 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailableShow in Telegram
#ጥንቃቄ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል። ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል። " ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል። " በጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን የዜጎችን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደርገ ነው " ብለው ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ተናግረዋል። #ኢብኮ @tikvahethiopia
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
🔈#ይነበብ (በድጋሚ የተለጠፈ) ወጣቶችን ወስደው ምንድነው የሚያሰሯቸው ? በኦንላይን ወይም በደላሎች አልያም በኤጀንሲዎች " እዚህ ሀገር ጥሩ ስራ አለ ፤ ክፍያውም ከፍ ያለነው " ተብለው ብዙ ወጣቶች ከተለያዩ ሀገራት ይዘዋወራሉ። ለአብነት ያህል ወጣቶች ከሚዘዋወሩባቸው ሀገራት መካከል የሳይበር ማጭበበር ( Cyber Scam) ማዕከላት ተብለው ወደ ሚታወቁት ፦ • ማይናማር ፣ • ካምቦዲያ፣ • ላኦስ • ማይናማር ታይላንድ ድንበር • ቻይና ማይናማር ድንበር በዋነኝነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ አካባቢዎች ባሉ የተለያዩ ቦታዎች በኦንላይን ማጭበርበር ላይ የተሰማሩ በርካታ ድርጅቶች አሉ። በእርግጥ መጀመሪያ ላይ ወጣቶቹን " እልካችኋለን " የሚሏቸው ሌሎች በኢኮኖሚና ደህንነት እጅግ ጠንካራ ፣ ጠንካራ ባይሆኑም እንኳን ያን ያህል የከፋ ሁኔታ ላይ ወደማይገኙ ሀገራት ነው። እዛ ቦታ ከደረሱ በኋላ ግን የሚልኳቸው ወደ ጎረቤት ድሃ እና የህግ ስርዓት ወዳልጠነከረባቸው ሀገራት ይሆናል። የሚሰራው ማጭበርበር ምንድነው ? ስራ ብለው የሚልኳቸው መጀመሪያ ፦ - የኦላንይ ግብይት ስራ ማቀላጠፍ - የኦንላይን ሴልስ ስራ - የሆቴል እንግዳ ተቀባይ - የማርኬቲንግ ስራ ... ሌላም ሌላም ነው። ነገር ግን ስራ አለበት ወደ ተባለው ስፍራ ሲሄዱ የሚሰሩት ስራ መጀመሪያ ላይ ከተነገራቸው ተቃራኒ ነው። የየራሳቸው ጋንግ አለቆች ባላቸው እጃቸውም ረጅም በሆኑ ሰዎች በሚመሩ የማጨበርበር ተግባር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች ያስገቧቸዋል። እነዚህ ሰዎች ስልክ / ኮምፒየተር የሚያቀርቡላቸው ሲሆን በዛም ዓለም አቀፍ የማጨበርበር ስራ ላይ ያሰማሯቸዋል። 🔴 ዴቲንግ 🔴 የመጀመሪያ ስራቸው ከኢንተርኔት ላይ ውብ የሆኑ ሴቶችን / ስኬታማ ሴቶችን / ስኬታማ ወንዶችን ታዋቂ ሰዎችን ፎቶ በማውረድ የውሸት አካውንት መክፈት ነው። በመቀጠል የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ። ምናልባትም በቅርብ የሚያውቋቸውን ሰዎችንም ሊሆን ይችላል። እነዛን ሰዎች ልክ እንደ ኖርማል ሆነው ያለ ማቋረጥ ጊዜ ወስደው ያናግሯቸዋል። የትኛውንም ጊዜ ይፍጅ ማናገራቸውን ይቀጥላሉ። ስለ ውሸት ስራቸው፣ ስለ ህይወታቸው እየፈጠሩ ያወራሉ። በዚህ ውስጥ ምንም ምልክት አያሳዩም። ወደ ፍቅር ከወሰዷቸውና ከጣሏቸው እምነትም ካገኙ በኃላ መጨረሻው ወደሆነው ዓላማቸው ገንዘብ ማስላክ ይገባሉ። " ለምን እኔ ምሰራው ስራ ላይ ኢንቨስት አታደርም / አታደርጊም " በማለት ለምሳሌ ክሪፕቶ  ላይ ብለው ገንዘብ ይቀበላሉ። በቃ አለቀ ! ገንዘባችሁ ተበልቶ ይቀራል። በኃላም ብሎክ አድርገው ይሸኟችኋል። ቀጣይ ሌላ ሰው ታርጌት ያደርጋሉ። ወጣቶቹ ይሄን ካላደረጉ ምናልባትም ኢ-ሰብአዊ ቅጣት ሊፈጸምባቸው ይችላል። ⚫️ በጎ አድራጎት ⚫️ የውሸት ማንነት ፎቶ ተጠቅመው አካውንት ከፍተው (ሴትን በወንድ ወንድ ደግሞ በሴት ማንነት) አንድ ታርጌት ያደረጉትን ሰው ረጅም ጊዜ ያናግሩ እና ለእርዳታ / ለእርዳታ ድርጅታቸው ገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ያሳምኗቸኣል። እነዛ ሰዎች ላይ እምነት የጣሉባቸው ተጨበርባሪዎች በሀዘን ተሰብረው ገንዘባቸውን ይልካሉ። ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ይደረጋሉ። 🟡 ባለሃብት መምሰል 🟡 የውሸት ማንነት በመፍጠር ፣ ፎቶዎችን በመጠቀም በኦንላይን ሰው ያናግራሉ። እንዲታመኑ ረጅም ጊዜ ሊወስዱም ይችላሉ። ሰዎቹ ካመኗቸው በኃላ ገንዘባቸውን በጋራ አፍስሰው ስለሚሰሯቸው ስራዎች በማናገር ገንዘብ ያስልካሉ። ከዛማ ቀልጦ ይቀራል። ብሎክ ያደረጋሉ ! 🟤 ደንበኞችን ማነጋገር 🟤 ይህም በተመሳሳይ በሀሰተኛ ማንነትና ስራ ከተለያዩ ሰዎች እያነጋገሩ በማጭበርበር ገንዘብ መቀበል ነው። ለምሳሌ ፦ እቃ የሚሸጡ አስመስለው ብር ካስላኩ በኋላ የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ። 🔵 ' ኮሜንት/ሬት በማድረግ ገንዘብ አግኙ ' 🔵 እነዚ አጭበርባሪዎቹ የውሸት ማንነት ተጠቅመው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ ወይም በሌላ መንገድ ተጠቅመው የሚያጭበረብሩትን ሰው ማናገር ይጀምራሉ። " ጎግል ላይ ግቡና ስለዚህ ድርጅት ጥሩ አስተያየት ጻፉ ይከፈላችኋል " ይላቸዋል። ከዛም የመጀመሪያውን ክፍያ በመፈጸም እምነት ያሳድራሉ። " ይሄን ያህል ብር ከላካችሁ ይሄን ያህል ታገኛላቹ " በማለት የሰዎቹን ማንነት ይገመግማሉ። እስከዛ ድረስ ግን ገንዘብ መላካቸውን አያቆሙም። የሚጭበረበረው ሰው ብዙ ብር ካስላኩት በኋላ የውሃ ሽታ ይሆናሉ። በተጨማሪም ... እንደ ፖሊስ፣ደህንነት፣ ባንክ ሰራተኛ ፣ እንደ ድርጅት ኃላፊ ሆነው የሚያስመስሉ አጭበርባሪዎችም አሉ። ስራውን የሚሰሩት ሰዎችም ተጠቂዎች ናቸው። ስራውን ካልሰሩ አሰቃቂ ጥቃት ሊደርስባቸው ይችላል። እንደ ባሪያ ለረጅም ሰአትም ያሰሯቸዋል። እንደ ቅርብ ጊዜ ሪፖርት ፥ በማይናማር፣ ካምቦዲያ፣ ላኦስ፣ ቻይና በመሳሰሉ ሀገራት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች በኦንላይ ማጭበርበር ላይ ተሰማርተዋል። ስራዎቹንም የሚያሰሯቸው ሰዎች እጃቸው በጣም ረጅም ነው። #TikvahEthiopia #CyberScam @tikvahethiopia
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
🔈 #የወላጆችድምፅ • “ ወደ ባሕር ዳር ከተማ ልጆቻችንን ለማስመዘገብ ስንሄድ ለሚቀመጡበት ወንበር 6 ሺሕ ብር ክፈሉ እያሉን ነው ” - የተማሪ ወላጆች “ እኔ የማውቀው ችግር የለም ” - የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ዙሪያ የሚገኙ ወላጆች በጸጥታው ችግር በአካባቢያቸው መማር ያልቻሉ ልጆቻቸውን በባህር ዳር ከተማ ከፍተኛ ትምህርት ቤቶች ለማስመዝገብ ሲሄዱ ከአቅማቸው በላይ የሆነ ገንዘብ ክፈሉ እየተባሉ መሆኑን ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የተማሪ ወላጆች በዝርዝር ምን አሉ ? “ በጸጥታው ችግር ምክንያት በባህር ዳር ዙሪያ ያሉ ወረዳዎች ትምህርት መቀጠል አልቻሉም፡፡ ጫናውን ተቋቁመን አንጻራዊ ሰላም ወዳለበት ወደ ባህር ዳር ልጆቻችንን ለማስመዘገብ መሸኛ ይዘን ስንሄድ ተማሪዎቹ የሚቀመጡበት አንድ ወንበር ለሦስት ይዛችሁ ስትመጡ ብቻ ነው የሚመዘገቡት እያሉን ነው። በወላጅ ተለምነው በድርድር ወደ ገንዘብ ይቀይሩታል፡፡ አንድን ሰው 2 ሺሕ ብር፣ ለአንድ ወንበር 6 ሺሕ ብር ይጠይቃሉ፡፡ ልጆቻችን በጭንቀት ውስጥ ስለሆኑ ገንዘቡን በመክፈል ምዝገባ አካሂደናል፡፡ ተማሪዎቹ ቤተሰቦቻቸው በሚገብሩት ግብር የተሰሩ ትምህርት ቤቶች ነበሯቸው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ስላልቻሉ ነው የመጡት። ከዚሁ ክልል ውስጥ ነው፡፡ ችግሩ ደግሞ የመጣው እራሳቸው መቆጣጠር ባለመቻላቸው ነው መስዋዕትነት እየከፈልን ያለነው። ችግሩን ተቋቁመን ስንሄድ አበረታትተው መቀበል ሲገባቸው ገንዘብ ያስከፍላሉ፡፡ ገንዘቡን ወንበር ይገዙበታል ወይ የሚለውም አጠያያቂ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ገንዘቡን ስንከፍል ደረሰኝ እንኳ አይሰጡንም፡፡ ክፍያውን የሚቀበሉት ለመመዝገብ የተወከሉ ሰዎች ናቸው፡፡ እንዲህ የሚደረገውም በባህር ዳር በሚገኙ ሃይስኩል ትምህርት ቤቶች ነው፡፡ ዞረን በጠየቅንባው ትምህርት ቤቶች ተመሳሳይ አሰራር ገጥሞናል፡፡ በጸጥታ ችግር መማር ሳይችሉ ከሚቀሩ አንጻራዊ ሰላም ወዳለበት አጎራባች ቦታ ሲሄዱ መባል የነበረበት ' እንኳን ደኀና መጣችሁ ' ነበር፡፡ ነገር ግን ተማሪዎቹ ሲሄዱ ሌላ ጫና እየተፈጠረ ነው፡፡ የወንበር ችግር ገጥሟቸውም አይመስለንም፡፡ ወላጅ ላይ የተለዬ ምሬትና ጫና ከመፍጠር በመተዛዘን ተማሪዎቹን ቢያስተናግዷቸው መልካም ነው፡፡ ገንዘቡን መክፈል ያልቻሉ መመዘገብ አልቻሉም። ” ብለዋል። ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባሕር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያን ጠይቋል። ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አንድ ኃላፊ በሰጡት ቃል፣ “ ባሕር ዳር ዙሪያ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሊመዘገብ መጥቶ ሁሉም ትምህርት ቤት ጋር ' ለሦስት፤ ለሦስት አንድ ወንበር አምጡ ወይም ወንበር ይዛችሁ ካልመጣችሁ አላስተናግድም ' ያለ ትምህርት ቤት የለም። ” ብለዋል። “ እኛ ጋ ' ችግር ደረሰብኝ ' ብሎ የመጣም የለም፡፡ ' ወንበር አምጣ ተብያለሁ ' ብሎ መጥቶ የጠየቀኝ ተማሪም የለም፡፡ ሁሉንም ትምህርት ቤት እየዞርኩ እያየሁ ነው፡፡ የትኛውም ትምህርት ቤት ላይ እየተመዘገቡ ነው። ” ሲሉ ተናግረዋል። “ አልፎ አልፎ አንመዘግብም ያሏቸውን እራሴ እየመራሁ ነው ያስመዘገብኳቸው፡፡ ትምህርት ቤቱ የማህበረሰብ ተሳትፎ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ ግን አግሪመንት ወስዶ ማህበረሰቡ የፈረመውን ነው እያስከፈለ ያለው። ” ሲሉ አክለዋል። “ እኔ የማውቀው ችግር የለም ” ያለው ትምህርት መምሪያው፣ እንዲህ የሚያደርጉ ትምህርት ቤቶች ካሉ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ቢያሳውቁት ታች ድረስ ወርዶ እርማት እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡ ወላጆች መሰል ችግር ያለባቸውን ቦታዎች ለትምህርት መምሪያ መጠቆም እንደሚችሉ ተመላክቷል። #TikvahethiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
Show all...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
#Ethiopia🇪🇹 " ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን በቅርበት ትከታተላለች አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ተገቢውን ምላሽ ትሰጣለች " - ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር። በመግለጫቸው ፥ " የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎረቤት ሀገራት ልዩ ትኩረት ይሰጣል " ሲሉ ጠቁመዋል። " ኢትዮጵያ መርህን መሠረት ያደረገ በበጎ መንፈስ የተቃኘ ዘላቂ ዲፕሎማሲ ላይ አተኩራ ትሰራለች "ም ብለዋል። " የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናን የትርምስ ማዕከል ለማድረግ የሚደረግ እንቅስቃሴም ሊቆም ይገባል " ሲሉ አሳስበዋል። ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን በቅርበት እንደምትከታተልና አስፈላጊ በሆነበት ጊዜም ተገቢውን ምላሽ እንደምትሰጥ ገልፀዋል። አምባሳደር ነቢያት ፥ ➡️ ከአውሮፓ ህብረት፣ ➡️ ከአሜሪካ ➡️ ከተመድ ልዩ መልዕክተኞች ጋር ውይይቶች መካሄዳቸውን ጠቁመዋል። " ለሁሉም መልዕክተኞች ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነበት ሆኖ የኢኮኖሚ ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል " ብለዋል። #EPA @tikvahethiopia
Show all...
#Amhara " ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ነው እቅድ የተያዘው ከነሐሴ 20/2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ናቸው - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ እንዳቀደ፣ ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ተማሪዎች መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ " ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 292 ሺሕ በላይ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 1.2 ሚሊዮን በላይ፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ 180 ሺሕ ተማሪዎች ተመዝግበዋል " ብሏል፡፡ " በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምዝገባው እየተካሄደ ነው፡፡ ትንሽ እሱ ላይ መዘግየት ይታያል፡፡ እስካሁን በጠቅላላ ወደ 1.7 ሚሊዮን ተማሪዎች ናቸው የተመዘገቡት የእቅዱን ወደ 24 ፐርሰንት አካባቢ " ነው ያለው፡፡ በጸጥታው ችግር ባለፈው ዓመት በርካታ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ይታወቃል፡፡  በ2017 የትምህርት ዘመንስ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች እጣ ፈንታቸው ምንድን ነው ? እውነት ተመዝግበውስ ለመማር አስቻይ ሁኔታ አላቸው ወይ ? ከዚህ አኳያ ቢሮው ምን አቅዷል ? ምንስ እየሰራ ነው? ስንል ቢሮውን ጠይቀናል፡፡ የቢሮው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን " በክልሉ ከ10 ሺሕ 874 በላይ ትምህርት ቤቶች አሉ፡፡ በአዲሱ የትምህርት ዘመን የእኛ ፍላጎት እነዚህ ሁሉም ትምህርት ቤቶች 7 ሚሊዮን ተማሪዎች እንዲያስተምሩ፣ መማር ማስተማሩ እንዲጀምር/እንዲቀጥል ነው " ብለዋል፡፡ " በተለይ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የጸጥታ ችግር ስላለ የትምህርት ሥራን ከዚህ በፊት እንደምናደርገው ሁሉ የምዝገባ ሥራን ለመስራት እንቅፋቶች ቢኖሩም ምዝገባ ተጀምሯል፡፡ የምዝገባ አፈጸጻሙ በምንጠብቀው ልክ ባይሆንም ምዝገባ እየተካሄደ ነው " ሲሉ አቶ ጌታው ተናግረዋል፡፡ የመማር ማስተማር ሂደቱ እዳይደነቃቀፍ በትጥቅ ትግል ላይ ያሉትን ጨምሮ ሁሉም ሰው ኃላፊነት መውሰድ እንዳለበት ቢሮው አስምሮበታል። " አንድንድ ቦታ ላይ ትላንት ትምህርት ሲጅሩ ልንማር ይገባል የሚል ሞቶ ሁሉ ይዘው የወጡ ተማሪዎች አሉ፡፡ ይሄ በጣም ልብ ይብራል ሰው ሆኖ ለተፈጠረ ሁሉ፡፡ ምሁራን፣ የኃይማኖት አባቶች፣ በዛኛው ወገን ያሉ ወንድሞቻችንም ጭምር ይህን ተረድተው ትምህርትን ነጻ ሆነን እንድንስራ በጎ ሚናቸውን መጫወት አለባቸው " ሲሉ አስገንዝበዋል። " በ2016 ዓ/ም በተለያየ ምክንያት ትምህርት ተቋርጦባቸው የቆዩ አካባቢዎች፤ ሳይማሩ የቆዩ ተማሪዎች፤ ተዘግተው የቆዩ ትምህርት ቤቶች አሉ " ሲልም ቢሮው ገልጿል፡፡ ከውድመት ጋር በተያያዘም አቶ ጌታቸው በሰጡት ቃል፣ " በክልሉ ካለው የጸጥታ ችግር ወይም ግጭት ጋር በተያያዘ ከፍተኛም መካከለኛም ጉዳት የደረሰባቸው ወደ 1115 ትምህርት ቤቶች አሉ " ነው ያሉት፡፡ " እነዚህን ትምህርት ቤቶች መልሶ ግብዓታቸውን በማሟላት ረገድ አንደኛ በአካባቢው ማህበረሰብ የሚሸፈን በዚያው ነው የሚሸፈኑት " ብለዋል፡፡ " የእኛን የክልሉን ኢንተርቬንሽን ሚጠይቁት ደግሞ አጋር አካላትን እያሳተፍን እቅድ አቅደን እያነጋገርን ነው፡፡ ከነርሱ ሀብት እያፈላለግን ትምህርት ቤቶች እንደገና ቁስቁሳቸው እንዲሟላ፣ እንዲገነቡ የማድረጉን ሥራ ወደፊት የምንስራ ነው የሚሆነው " ሲሉ አክለዋል፡፡ በክልሉ በ2016 ዓ/ም መመዘገብ ከነበረባቸው 6.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት እንዳልተመዘገቡ ተገልጾ የነበረ ሲሆን፣ በ2017 ትምህርት ዘመን ደግሞ ቢሮው ለመመዝገብ ካቀደው ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ድረስ ተመዘገቡ የተባለው 1.7 ተማሪዎች ናቸው፡፡ #TIKvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia
Show all...
#Tigray " ህገወጥ ቡድኑ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ አቅዷል " - በህወሓት ጉባኤ ያልተሳተፉት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ማእከላዊ ኮሚቴ አባላት በህወሓት ጉባኤ ላይ ያልተሳፉት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በጋራ መግለጫ አውጥተዋል። በዚህም " ህገመንግስትና ህገ ድርጅት በመጣስ ህገወጥ ጉባኤ ያካሄደ ቡድን ሌላውን የማባረር ሞራልና ስልጣን የለውም " ብለዋል። ከሰሞኑን በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን አቶ ጌታቸውን ጨምሮ 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን ማባረሩ ይታወሳል። የማእከላዊ ኮሚቴ አባላቱ " ህገ-መንግስትና ህገ ድርጅት በመጣስ ህገ-ወጥ ጉባኤ ያካሄደው ቡድን ሌላውን የማባረር ህጋዊና ሞራላዊ ስልጣን የለውም " ከማለት ባለፈ " መፈንቀለ መንግስት ለማካሄድ ማቀዱን ደርሰንበታል " ብለዋል። " የህገወጡ ቡድን መሪ በትግራይ ህዝብ ላይ የተፈፀመ ጄኖሳይድ ፍትህ እንዲያገኝና ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ መታገል ሲገባው ጉዳቱ ወደ ቁጥር ጨዋታ በማውረድ የህዝብ መስዋእትና የወጣቶች ጉዳት ዋጋ እያሳጣው ይገኛል " ሲሉ ገልጸዋል። ከሰሞኑን ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል " ኒው ሆራይዘን " ከተሰኘ የማህበራዊ ሚድያ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር። በዚህ ወቅትም " By the way ከአንድ ሚልየን በላይ አለቀ የሚለው ፤ ማስረጃ የለው፣ ጥናት የለው ፣ ለማስፈራርያ ነው የሚውለው። ተጨፍጭፈናል ለማለትም አይደለም ፣ ጄኖሳይድ ተፈፀመብን ለማለትም አይደለም። አመራሩ አስጨረሰን ይላል ፤ አመራር ለመምታት ፣ ስልጣን ለመያዝ የማይሰራ ነገር የለም። " ሲሉ ተናግረው ነበር። በኃላም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ፤ " በህዝባችን ላይ የተፈፀመው ጄኖሳይድ አሁንም በርካታ በወራሪዎች ስር ያሉ የትግራይ አከባቢዎች ነፃ ባለመውጣታቸው ምክንያት የተሟለ መረጃ መስጠት ባይቻልም የደረሰው እልቂት ግን ከተጠቀሰው ቁጥር በላይ መሆን እንደሚችል ለመግለፅ እፈልጋሎህ " የሚል ማስተባበያ ለመስጠት ሞክረዋል። የአቶ ጌታቸው ቡድን ህገ-ወጥ ሲል የሚጠራውን የዶ/ር ደብረጽዮን ቡድንን " ዓለምአቀፋዊ ወንጀል ሸምጥጦ በመካድ የዓለም ማህበረሰብ የተከራከረለትና የመሰከረውና የህዝብ እልቂት ወደ ጎን በመተው ዋጋ የሌለው እንዲሆን ወሰኖ ጥላሸት በመቀባት ላይ ይገኛል " ሲል ከሷል። " ህገወጥ ቡድኑ ቡድናዊ የስልጣን ፍላጎቱ በፀረ ዴሞክራሲያዊ አካሄድ ፣ በማሰፈራራትና ሃሳቦች በማፈን ለመጫንና ለማሳካት ላይ ታች በማለት ይገኛል " ያለው የማእከላዊ ኮሚቴው " ይባስ ብሎ የመንግስት መዋቅር አንዲፈርስና ትግራይ መንግስት አልባ ሆና የረብሻና ግርግር ማእከል እንድትሆን እየሰራ ነው " ሲል አሳውቋል። " ህገወጥ ቡድኑ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ ማቀዱ ግልፅ ሆኗል " ያለው የማእከላዊ ኮሚቴው " ጊዚያዊ አስተዳደሩና ህዝቡ ከአደገኛ አካሄዱ ሊያስቆሙት ይገባል " በማለት አክለዋል። 50 ዓመት ያስቆጠረ ድርጅት እንደ አዲስ እንዲመዘገብ በማድረግ የትግራይ ህዝብ ትግል የካደው ቡድን ህዝቡና የዳያስፓራ አባላት እንዲታገሉት ጥሪ አቅርቦ የህወሓት ህጋዊ ሰውነት ለማስመለስ ፓለቲካዊ ውይይት መጀመሩን አመልክቷል። መላው ህዝብ ከጎኑ እንዲሰለፍም ጥሪ አቅርቧል። በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ እውቅና ውጪ ባካሄደው 14ኛው ጉባኤ ያልተሳተፉና ሂደቱን የተቋወሙት የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት " ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነታቸው አባርሪያለሁ " ማለቱን መዘገባችን ይታወሳል። #TikvahEthiopiaMekelle @tikvahethiopia            
Show all...
የፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ። የጉምቱው ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ስርዓተ ቀብር በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ተፈፅሟል፡፡ ከስርዓተ ቀብራቸው ቀደም ብሎ የአስክሬን ሽኝት በሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። በሽኝት ስነ-ሥርዓቱ ላይ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ተገኝተው ነበር። በተጨማሪ በሆሣዕና የሀዲያ ዞንና የአከባቢው ህዝብ በፕሮፈሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን በኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ በመገኘት ሲገልጽ ውሏል። @tikvahethiopia
Show all...
#ኢትዮ130 ኢትዮ ቴሌኮም በአዲሱ አመት በነበረው የደንበኞች ጨዋታ በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ደንበኞቹን መሸለሙን ይህም በእጅጉ አዳዲስ ደንበኞችን ለማግኘት ያገዘው እንደሆነ ገልጿል። ኩባንያው ከተመሰረተ 130 ዓመታትን ማስቆጠሩን አስመልክቶ በተያዘው ዓመት ለስድስት ወር የሚቆይ "ኢትዮ 130" የተሰኘ ጨዋታ በተመሳሳይ ለደንበኞቹ እንደሚያቀርብ አስታውቋል። ኩባንያው በስራቴጂው የመጨረሻ ዓመት ሊያከናውናቸው ባቀዳቸው ተግባሮች ዙሪያ በዛሬው ዕለት ተቋሙ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። በዚህም፥ በ2016 በጀት ዓመት የተገኘውን 93 ቢሊየን ብር ገቢ በ74.7% በማሳደግ 163.7 ቢሊዮን ብር ለማድረስ እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት መጠንንም ወደ 282.85 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማሳደግ አቅዷል። በተጨማሪም፦ - የደንበኞችን ብዛትንም በ6% በመጨመር 83 ሚሊዮን ለማድረስ፤ - የሞባይል ደንበኞችን በ5.5% በመጨመር 79.7 ሚሊዮን ለማድረስ፤ - የሞባይል ዳታና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በ16% በመጨመር 47.4 ሚሊዮን ለማድረስ፤ - የፊክስድ ብሮድባንድ ደንበኞችን በ25% በመጨመር 934 ሺህ በማድረስ አጠቃላይ የቴሌኮም ስርጸት መጠንን 73% ለማድረስ ታቅዷል፡፡  - 1,298 አዲስ የሞባይል ጣቢያዎችን ለመገንባት፤ 500 ተጨማሪ ከተሞችን የ4ጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግና 15 ተጨማሪ ከተሞችን የ5ጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ማቀዱንም ነው የገለጸው። ኢትዮ ቴሌኮም “ሊድ” የተሰኘ የሦስት ዓመት ስትራቴጂውን በ2015 በጀት ዓመት ማስተዋወቁ ይታወሳል። አዲሱ የ2017 በጀት አመት የስትራቴጂ ዘመኑ ሶስተኛው አመቱ ይሆናል። ተጨማሪ ያንብቡ https://telegra.ph/Ethio130-09-19 @tikvahethiopia
Show all...
#እንድታውቁት ከጋንቤላ አዲስ አበባ የሚወስደው የአስፋልት መንገድ በቡኖ በደሌ ዞን ደዴሳ ወረዳ፣ ማሳራ ቀበሌ የመሬት መንሸራረት በማጋጠሙ አስፓልቱ ተቆርጧል። በዚህም ምክንያት የትራፊክ እንቅስቃሴ መቋረጡን ኦቢኤን ዘግቧል። @tikvahethmagazine
Show all...
#CRRSA የመታወቂያ ህትመት ለደረሰላቸው ተገልጋዮችን ለማሳወቅ የአጭር መልዕክት አገልግሎት በሙከራ ላይ ነው ተባለ። የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የመታወቂያ ስርጭት ክፍተቶችን ማረም የሚያስችል የአጭር መልዕክት አሰራር በይፋ ወደ ሙከራ አስገብቷል። ነዋሪዎች የነዋሪነት መታወቂያዎን ይውሰዱ መልዕክት ሲደርሳቸው የነዋሪነት መታወቂያ ታትሞ ዝግጁ የሚሆን በመሆኑ ወደ ተመዘገቡበት ጽ/ቤት ሄደው መረከብ የሚችሉበት አሰራር እንደሆነም ነው የተገለፀው። @tikvahethmagazine
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.