cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

የቃሊቲ ሰለፍዮች ጉሩፕ

ያስከፈለንን ከፍለን ለሐቅ እንጣራ በትክክለኛ መረጃ ሠለፍይ እናፍራ በችግር በምቾት አላህን የሚፈራ በተውሒድ በሡና በፅናት የሚሠራ

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
416
المشتركون
-124 ساعات
-17 أيام
-130 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

🔹ወደ አላህ በሚደረገው ዳዕዋ ፣ እንዲሁም ከሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት መቸ ነው የምንለዝበው ፣ መቸ ነው የምንጠነክረው?  ፈዲለቲ አሽሸይኽ ዶክተር ረቢዕ ብን ሃዲ ኡመይር አልመድኸሊ - ሀፊዞሁሏህ - መልስ:- የዳዕዋ መሰረቱ ለዘብታ ፣ እዝነት ፣ ጥበብ ነው። ይህ ነው መሰረቱ። ስለዚህ - ባረከሏሁ ፊክ - የሚቃወም ታገኛለህ ፣ ሀቅን የማይቀበል ፣በእርሱ ላይ ሁጃ ታቆማለህ (መረጃውን ታደርሳለህ)፣  ይቃወማል ፣ በዚህ ጊዜ ረድ ትጠቀማለህ (ምላሽ ትሰጣለህ)፣ ባለስልጣን ከሆንክ ይህ በሰይፍ ስርአት ለማስያዝ ቀስቃሽ ይሆናል። ብልሹነትን በማሰራጨት የሚዘወትር ከሆነ ወደ መገደል ይደረሳል። ከተለያየ መዝሀብ የዚህ ብልሹነት ከሽፍታ የከበደ ነው የሚል እይታ ያላቸው ኡለሞች አሉ። ይህ ይመከራል ፣ ሁጃ ይቆምለታል (ማስረጃው እንዲደርሰው ይደረጋል)። እምቢ ካለ ፣  የሸሪአ ዳኛ ወደ ቅጣት ይሄዳል። (ቅጣቱ) በእስር ሊሆን ይችላል። ከአገር በማባረር ሊሆን ይችላል። በመግደል ሊሆን ይችላል። በጀህም ብን ሶፍዋን ፣ በሌላውም ላይ ፣ በቢሽር አልሚሪሲ - ባረከሏሁ ፊክ - በሌሎችም ላይ - ባረከሏሁ ፊክ - ሞት ነው የወሰኑት። ከእነርሱ መካከል ጀዕድ ብን ዲርሀም ይገኝበታል።  ይህ የኡለሞች ብይን ነው ፣ በእምቢተኛ ላይ ቢድዓውን ዘወትር በሚያሰራጨት  ላይ ፣ አላህ ጠቅሞት ከተመለሰ ይህ ተፈላጊ ነው። (الحث على المودة والإأتلاغ) https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة
إظهار الكل...
👍 1
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته አዲስ ዜና ለእውቀት ፈላጊዎች በሙሉ ከዚህ በፊት በመድረሳችን ውስጥ በዶ/ር ሽይኽ ሑሰይን ሙሐመድ አስሲልጢ ሐፊዘሁሏህ ተጀምሮ የነበረውና ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ የነበረው የደርስ ፕሮግራም የአላህ ፈቃዱ ሆኖ ከፊታችን ሰኞ ቀን 06/1/2017 ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ ሐሙስ ከጠዋቱ 3:00 እስከ 6:00 የሚቀጥል ይሆናል። የሚቀራው ኪታብ ١.  نزهة النظر في توضيح نخبة الفكر في مصطلح أهل الأثر ٢. صحيح مسلم https://t.me/medresetulislah
إظهار الكل...
مدرسة الإصلاح (አል ኢስላሕ መድረሳ)

ይህ ቻናል “❝ከፉሪ ሕይወት ፋና ወደ የስ ውሃ ፋብሪካ በሚወስደው መንገድ በተለምዶ ኑሪ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የአል ኢስላሕ መድረሳ ኦፊሺያል የቴሌግራም ቻናል ነው።❞ በአላህ ፍቃድ በመድረሳው የሚሰጡና በተለያዩ የሰለፊያህ ዱዓቶች፣ ኡስታዞችና መሻኢኾች የሚተላለፉ መልዕክቶች (በድምፅም ይሁን በፅሑፍ) ይተላለፉበታል። ወዳጅ ዘመድዎን ይጋብዙ።

https://t.me/medresetulislah

👉    86 ገፅ ፅፈናል ‼        ነሲሐዎች ከአመታት በፊት መጅሊሱን በአዋጅ ለማፅደቅ ከኢኽዋን ሱፍይና አሕባሽ ጋር እንዲደመሩ ጥሪ በተደረገላቸው ጊዜ ለሙስሊሞች ይጥቅማል ብለን 86 ገፅ ፅፈን ለኮሚቴው አቅርበናል ። ነገር ግን አንድ ገፅ እንኳን መፃፍ ያልቻሉ አካላት በዚህ ይወቅሱናል በጣም ይገርማል እያሉ መጅሊሱ እነርሱ በፃፉትና ለሙስሊሞች ይጠቅማል ባሉት የሚመራ በማስመሰል በሙሪዶቻቸው አማካይነት ዳንኪራ ሲያስደልቁ ነበር ። በዚህ 86 ገፅ ውስጥ ምን እንዳለ የሚያውቁት የፃፉትና እንደጠዋትና ማታ አዝካር የሸመደዱት ሙሪዶቻቸው ናቸው የሚያውቁት ። ለኮሚቴው የቀረበው ፁሑፍ ግን ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ ነው የተጣለው ።       መጅሊሱ እየተመራ ያለው በፍልስፍናና በሰው ሰራሽ ህግ ነው ። አቡበከር አሕመድ ዲሞክራሲ ከተከበረ እምነቴ ተከብሮልኛል ብሎ እንዳወጀው ማለት ነው ። ‼ ይህ ኢኽዋኖች የሙስሊሞቹን ናላ እያዞሩበት ያለው መጅሊስ የሚመሩት አካላት መርሀቸው ዲሞክራሲ ያደረጉ መሆኑ የመጅሊሱ ወንበር ላይ በወጡ ማግስት የፈለገ መውሊድ ያውጣ የፈለገ ጫት ይቃም ይህን መከልከል ነገር መፈለግ ነው ብለው በሰጡት መግለጫ ግልፅ አድርገዋል ። ይህ እንግዲህ የሽርክና የቢዳዓ መናኻሪያ የሆነውን መውሊድ መከልከል መርሀቸውን የሚፃረር እንደሆነ ሲገልፁ ነው ። በአሁኑ የመጅሊስ አመራሮች መግለጫ ግን ሓሚድ ሙሳ በግልፅ ቃል በቃል መርሀችን መሆኑ እንዲታወቅ እንፈልጋለን ብሎ ከማስቀመጡ በፊት በውስጥ ታዋቂ ነበር የሚታወቀው ። የ86 ገፅ ባለቤቶቹ ነሲሓዎች በመጅሊሱ ውስጥ ሆነው ቁርኣንና ሐዲስን የሚቃረን ሽርክና ቢዳዓን የሚያነግስ መመሪያ ሲወጣና ለሙስሊሙ ማህበረሰብ በመግለጫ ሲገለፅ አይቶና ሰምቶ ተስማምቶ ከማሳለፍ ውጪ ሚና የላቸውም ። እያሉ የሞቱ በስማቸው ሽርክና ቢዳዓ እንዲነግስ የፈቀዱ በሰለፍያ ስም ወጣቱን ለሱፍይና አሕባሽ ግብኣት የሚያደርጉ ናቸው ። የኩፍር ንግግር እየሰሙ, የሽርክ ተግባር እያዩ አላየንም አልሰማንም ብለው አውቀው የተኙ ናቸው ። ከዚህ የሚከፋው ኢኽዋኖች እንደ በግ እየጎተቱ ወስደው በሚፈልጉት መድረክ ላይ አብረው እንዲቀረፁ እያደረጉ ከኛ ጋር ናቸው ብለው ሲያስተዋውቁ ይህን እንደ ስልጣኔ በመቁጠር ከኋላቸው እያለከለኩ መሮጣቸውን መቀጠላቸው ነው ። በ86 ገፅ ሽምደዳ ናላቸው የዞረ ሙሪዳቸው ግድፈታቸውን ላለማየትና ላለመስማት ምሎ ቃል የገባ ይመስላል ። ባይሆንማ ኖሮ የአዩሁድ ርዝራዦች የኢስላምን መርህ ለመናድና እስልምናና ሙስሊሞችን ለማራራቅ የጀመሩትን ኩፍርና ሽርክ በግልፅ የሚለፈፍበትን መውሊድ ከሙስሊሞች በሚሰበሰብ ገንዘብ ባጀት መድቦ ሲከበር ዝም ሲሉ እንዳላየ ሆነው አብረው ለመስለሓ በሚል ሲተሻሹ እያየ ዝም አይልም ነበር ። ኧረ ለመሆኑ ያ የቀራችሁት ኪታብ የት ሄደ ? ኪታ ተውሒድ ፣ አል ኢርሻድ ፣ ዐቂደቱል ዋሲጢያ ፣ መሳኢሉል ጃሂሊያና ከሽፉ ሹቡሃት የመሳሰሉት የት ደረሱ ? ወይስ የመጅሊስ አመራሮች 86 ገፆቹን ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ ሲከቱ እናንተም የቀራችሁትን ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ ከተታችሁት ? ከዚህ በላይ እየአንዳንዱ አንቀፅ ተውሒድን ከማስረፅና ሽርክን ከማውገዝ የማይለየው ቁርኣንስ የት ደረሰ ? አሕባሹ በመርሁ ላይ ሆኖ ሱፍዩ በመርሁ ሆኖ ትላንት ተውሒድ ተውሒድ እያላችሁ መውሊድን ስታወግዙ የሽርክና ቢዳዓን እንዲሁም መዕሲያን ወደነዚህ አዳራሽ ነው እያላችሁ ደም ስራችሁ ተገታትሮ ስታደርጉት የነበረው ዳዕዋ ምነው ከዳችሁ ? ለማንኛውም እኛ 86 ገፅ አይደለም 86 ሺ ገፅ ብትፅፉም ቆሻሻ ገንዳ ውስጥ እንደሚከተት እናውቅ ስለነበረ ነው በሱና ተርኪያ ( መተው በሚባለው ሱና ) የሰራነው ። በባጢል ላይ የተመሰረተ አንድነት ባጢል መሆኑ ግልፅ ነው ። መርህ ያለገናኘው ስብስብ መጨረሻው ድብድብ ነው የሚሆነው ። ድብድቡ በመርህ ቢሆን ጥሩ ነበር ነገር ግን በብርህ ነው የሚሆነው ። ለማንኛውም እኛ አላህ እንዲመሰክርልን የምንለምነው ከእነዚህ ሸሪዓን ከሚወጉ የመጅሊስ አመራሮች ወደ አላህ የጠራን መሆናችንን ነው ። ነሲሓዎች መዝሀባቸው የባጢኒዮች ( ሸሪዓ ውስጣዊና ውጫዊ ትርጉም አለው) የሚሉና በውጫዊው መስራት ኩፍር ነው ውስጣዊው ደግሞ የሚያውቁት የኛ መሪዮች ናቸው እንደሚሉት ካልሆኑ በስተቀር እየሰሩት ያለው ተግባር በምንም መመዘኛ ለእስልምና መስላሃ የለውም ። ጥሪያችን ለነሲሓ ሙሪዶች ሞት መጥቶ ከንቅልፋች ከመቀስቀሳችሁ በፊት ንቁ የሚል ነው ። አላየንም አልሰማንም ብትሉም ምላሳችሁ ተይዞ የሰራ አካላታችሁ ይመሰክርባችኋል ። በእስልምና ሀጢያትህን አስምርልሀለሁ የሚል የነፍስ አባት የለም ። ማንም ለማንም አይጠቅምም ። ከነ አቡበከርና ካሚል ሸምሱ ጋር እየዞረ መድረክ የሚያሞቀው ሸይኻችሁ እንኳን ለናንተ ሊሆን ለራሱም ጥያቄ ይጠብቀዋል ። ነፍሳችሁን ወደ አላህ በመመለስ ከሽርክና የቢዳዓ አካላት በመራቅና በማስጠንቀቅ አድኑ የሚል ነው ። http://t.me/bahruteka
إظهار الكل...
ባህሩ ተካ - Bahiru Teka

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته قناة رسمية لمحاضرات ودروس الأستاذ بحرو تكا (أبو عبيدة) الدعوة السلفية በአላህ ፈቃድ በዚህ ቻናል የአማርኛ ትምህርቶችን እንዲሁም አጫጭር የአረብኛና የአማርኛ ፁሁፎችን እንለቃለን ከዚህ ቻናል ውጪ ከሌላ ቦታ ተወስደው ለሚለቀቁ ኦዲዮዎች እውቅና አልሰጥም

https://telegram.me/bahruteka

የቁርኣን ትርጉም ማብራሪያ የአንዓም ምእራፍ ክፍል 02 በሰማያትና በምድር ያለው የማን ነው በላቸው ለአላህ ነው ይሉሀል የሚለውና ሌሎችም አንቀፆች የተብራሩበት
إظهار الكل...
አንዓም 02.mp39.06 MB
የመሳኢሉል ጃሂሊያ ኪታብ ደርስ ክፍል 43 የአላህ መልእክተኛ የመሀይማን ህዝቦችን ከተቃረኑባቸው ነጥቦች ውስጥ አንዱ መሪዮችን በነብያቶች ላይ ማነሳሳት የሚለው
إظهار الكل...
መሳኢሉል ጃሂሊያ 43.mp38.09 MB
👍 1
00:25
Video unavailableShow in Telegram
2.88 MB
👍 1
ገባገባበሉ
إظهار الكل...
رياض الصالحين من كلامي سيد مرسلين በየሳምንቱ ማክሰኞ ከመግሪብ እስከ እሻዕ
إظهار الكل...
👍 2
بسم الله الرحمن الرحيم ሰሞኑን አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ባህርዳር ሰላምበር መስጂድ ላይ መውሊድን ላይቭ  ሲያስተላልፍ ጫት እየተቃመ አስተላልፎ አሳይቷልና ብዙ ሙስሊሞችን አስቆጥቶናል። እጅግ ተንኮለኛ ሚዲያ እንደሆነ በደንብ አውቃለሁ። ከዚህ በፊትም ገታ እና ደገር ላይ ያሉ መውሊዶችን ከነሺርካቸው አስተዋውቋል። ሰውን ማደንዘዝ ሙስሊሞችን ባዕድ አምላኪዎች አድርጎ ማቅረብ አላማቸው ነው። ፋናም የዚህ አይነት ተግባር በአደባባይ ይፈፅማል። ሌሎቹም ዓላማቸው አንድ ነው። ግልፅ ካወጡት በላይ በውስጣቸው የደበቁት የከፋ እንደሆነ ጌታችን አላህ ነግሮናልና አይገርመንም። በጣም የገረመኝ ግን የኛ ለዐቂዳ ትኩረት አለመስጠት ነው። 1. ጫት መቃም ሐራምና አስነዋሪ ተግባር ሲሆን መስጂድ ላይ ሲሆን፣ ዲን ተደርጎ ሲያዝ ደግም ይበልጥ የከፋ ነው። ግን ምነው ብዙዎቻችን በመውሊድ ውስጥ ስለሚፈፀመው ከወንጀሎች ሁሉ እጅግ የከፋ ወንጀል ሺርክ ለምን አላንገበገበንም? ጫት መስጂድ ውስጥ መቃም ከባድ ወንጀል ከመሆኑ ጋር ከሺርክ አይስተካከልም። እንዴት የአላህ መብት ሲደፈር ዝም ብለን የገፅታ ግንባታችን ላይ ብቻ አተኮርን? "ሙስሊሞችን ያሰድባሉ" የሚለውን ብቻ እንዴት አጎላነው? ግን እስልምናን ተረድተነዋል? አላህ ፊት ስንቆም መልሳችን ምንድን ነው? 2. መውሊድ በልዩ ሁኔታ እንዲከበር ያመቻቸውን፣ መውሊድ የፈለገ ያክብር ያልፈለገ አያክበር ብሎ ለቢድዓ ከለላ የሚሰጠውን፣ ጫት ቢቅሙ ምን አገባችሁ በናንተ ገንዘብ አልቃመ በሚል ለወንጀል መፈፀም ሑሪያ የሚሰጠውን ወዘተ መጅሊስና አመራር ትተን ሌላ ወገን ላይ ጣት መቀሰር ምንኛ ነው? ቤታችን ጅብ አስቀምጠን ውጭ ስላለ ውሻ መጨነቅና እየየ ማለትስ? 4.  አሚኮ ግልፅ ጠላት መሆኑ እየታወቀ እርሱ ላይ እየዘመትን በሙስሊሙ ስር ተቋም ይዘው እስልምናን የሚንዱትን እንዴት ዝም አልን? 5. ወላእና በራእ ተጥሶ የመውሊድ አጋፋሪዎች ጋር እየታዩ ስለመውሊድ መግለጫ ሲሰጥ፣ 3ኛ በዓል ተደርጎ ሲወራ ለምን አፋችን ተለጎመ? ከመጅሊስ በወጣ ደብዳቤ ሽፋን ይሰጠን የሚል ለሙስሊም ሚዲያዎች ሲፃፍ ምን እንዲያደርጉ ነበር? ለሽርክ እውቅና አይደለምን? 5. በሰለፊያ ሽፋን የተሰተሩ ኢኽዋኖች በየቦታውና በየመጅሊሱ የሽርክና ቢድዓ አጋፋሪዎች ጋር ሲደመሩ፣ ለደዕዋ አንድ ላይ ሲንቀሳቀሱ፣ በሒክማ ስም ወጣቱን ለሱፊ ሲያስረክቡ፣ እንዳይናገር፣ ኢንካር እንዳያደርግ ሲያደርጉ ለምን ዝም አልን? በል እንዲያውም በዚህ ተግባር የተሳተፉ ሰዎች ሲኮነኑና ምላሽ ሲሰጥ ለምን አንቧ ከረዩ ተባለ? ለምን ተነኩ በሚል ከዲኑ ይልቅ ለግለሰብ ጥብቅና ለምን ቆምን? 6. ዶክተር ጄይላን ሱሩሪይ ወጣቱን የዛሬ 50 ዓመት ወደነበረበት ዐሽዓሪና ሱፊ እምነት እንመልሰዋለን፣ ጧሀ ሀሩንን የአንዋሩ የሽርክ አጋፋሪ ወጣቶች እንዲከተሉት እናደርጋለን፣ ሐሰን ታጁ  በንናኢ ኢኻዋኒ ሱፊ ወደ ድሮው ተቀባይነቱ እንመልሰዋለን ሲል ለምን ዝም አልን? ለምን ዒድ ሰላት ስታዲየም እየሄድን ጠሀን ተከትለን ስናጨበጭብ ከረምን? ጥያቄውን ለራሳችሁ ጠይቁ። መልስ አላችሁ? ለማንኛውም  ወደ አላህ እንመለስ። በሐቅ ላይ ሆነው የሚታገሉ፣ እነዚህን የዲን አበላሾች የሚያጋልጡና የሚያስጠነቅቁ ዑለማዎችን እንደግፍ። ትምህርታቸውን እናስተላልፍ። ወደ ራሳችን እንመለስ። ከሙሐዶራና ጊዜያዊ ምክር በዘለለ በስርዓት በመማር በእውቀት ላይ ሆነን ለዲናችን ዘብ እንቁም። የባጢል ሀይሎች እስልምናና ሙስሊሞችን ለማጥፋት ቀን ከሌሊት እየተጉ የኛ ማንቀላፋት ምንኛ ነው? እስልምናን መጥፋት ባይችሉም ሙስሊሞችን ግን እንደፈለጉ ማድረግ ችለዋል። የተሰጠውን አጀንዳ ብቻ የሚያራግብ፣ እንዴትና ለምን የማይል ትውልድ፣ መረጃ የማይጠይቅ፣ ንፁሕ ዐቅሉን መጠቀምና ማስተዋል ያቃተው ተውልድ፣ ከዲኑ ይልቅ ለግለሰቦች ጥብቅና የሚቆም ትውልድ፣ ሐላል ሐራም ሳይመርጥ ዱንያ እያግበሰበሰ  የሰመጠ ትውልድ፣ ካለው ጊዜ ትንሽ እንኳን ጊዜ ወስዶ ዲኑን መማር ያልቻለ ትውልድ እንዴት ለእስልምናና ሙስሊሞች ዘብ ይሆናል? አላህ ይዘንልን። ከአንድ ወንድም ፅሑፍ የተወሰደ https://t.me/medresetulislah
إظهار الكل...
مدرسة الإصلاح (አል ኢስላሕ መድረሳ)

ይህ ቻናል “❝ከፉሪ ሕይወት ፋና ወደ የስ ውሃ ፋብሪካ በሚወስደው መንገድ በተለምዶ ኑሪ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ የሚገኘው የአል ኢስላሕ መድረሳ ኦፊሺያል የቴሌግራም ቻናል ነው።❞ በአላህ ፍቃድ በመድረሳው የሚሰጡና በተለያዩ የሰለፊያህ ዱዓቶች፣ ኡስታዞችና መሻኢኾች የሚተላለፉ መልዕክቶች (በድምፅም ይሁን በፅሑፍ) ይተላለፉበታል። ወዳጅ ዘመድዎን ይጋብዙ።

https://t.me/medresetulislah

👍 1
إظهار الكل...
ماذا أفعل إذا دخلت والمؤذن يؤذن فضيلة الشيخ محمد بن العثيمين رحمه الله

اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.