cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Damot News24 - English version

Show more
Advertising posts
189
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-930 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

17:44
Video unavailableShow in Telegram
የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ የድንበር ከተማዋን መተማ ዮሃንስን መቆጣጠሩን አስመልክቶ ከጎንደር እዝ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የተላለፈ መልእክት https://t.me/rohatv1
Show all...
0903 (2).mp4531.94 MB
የሶማሊያና የግብጽ ቀጠሮ ሶማሊያ የብልፅግናው አገዛዝ “ግዛቶቼን ይዟል” ስትል ክስ አቀረበች በመሆኑም ግዛቶቿን ለማስመለስ "ህጋዊና ከህጋዊ ውጪ” መንገዶችን እንደምትጠቀም ገልፃለች። ሁለቱ ሃገራት ቀጥተኛ ጦርነት ውስጥ ለመግባት ዳርዳር እያሉ ባሉበት ወቅት ነው፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ኢትዮጵያ “የሶማሊያን ግዛቶች መያዟን እንደቀጠለች ነው” ሲሉ የገለፁት። ይህን አካሄድ በሚቀጥሉት ወራት “ህጋዊ እና ከህጋዊ ውጪ” የሆኑ መንገዶችን በመጠቀም እናስቆማለን ሲሉም አስጠንቅቀዋል። “ኢትዮጵያ የሶማሊያን ግዛቶች እንደያዘች” የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ “ይህም መፍትሄ ያልተገኘለት ጉዳይ ሆኖ ሳለ አሁን ደግሞ የበለጠ ግዛቶችን ለመያዝ ህልም አላት” ሲሉ ከሰዋል። በተመሳሳይ ግብጽ እና ሶማሊያ ለወታደራዊ ልምምድ ቀጠሮ ይዘናል ብለዋል። ግብፅ እና ሶማሊያ በቀጠናው የተባባሰውን ውጥረት ተከትሎ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ሊያደርጉ መሆኑ ተሰምቷል። ግብፅ እና ሶማሊያ በዚህ ወር የምድር፣ የአየር እና የባህር ሃይሎችን ያካተተ የጋራ ወታደራዊ ልምምዶችን ሊያደርጉ እንደሆነ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ይህ የሆነው ግብፅ በቅርቡ በአዲስ የትብብር ስምምነት መሰረት ወታደሮቿን እና ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ወደ ሶማሊያ ማሰማራቷን ተከትሎ ነው። "ልምምዱ ሶማሊያን ለማስከበር እና ለመጠበቅ ያለንን ጽኑ የቁርጠኝነት መልእክት ያስተላልፋል" ሲሉ ወታደራዊ ባለስልጣናት ተናግረዋል ከቀናት በፊት በሶማሊያ የግብጽ ጦር መስፈሩን የተቃወሙ የፕሬዝዳንቱ ልዩ ልዑክ እና የምክር ቤት አባል አብዲረሺድ ሞሃመድ ኑር ጂሌይ ከሃላፊነት መነሳታቸውን የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ ገልጿል። https://t.me/rohatv1
Show all...
Repost from Ethio 251 Media
የ14 አመት ህፃን ልጅ በአገዛዙ ሃይሎች ተረሸነ ! በሞጃና ወደራ ወረዳ፣ ብርቃ ቀበሌ ቋት ጊዮርጊሳ አከባቢ ደሳለው ደነቀው የሚባል የ14 አመት ልጅ በአብይ አህመድ ቅጥረኛ ሰራዊት ተረሽኗል። ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ሰሞኑን ሰላድንጋይ ከተማ በነበረው ውጊያ የወገን ጦር በትርን መቋቋም ያልቻለው የአብይ አህመድ ሠራዊት ንፁሃንን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች በመፈፀም በተደጋጋሚ ሽንፈቱን እየገለፀ ይገኛል። በዚህም በትናትናው ዕለትም በፋኖ የተደቆሰው የአብይ ሰራዊት በደረሰበት አሰቃቂ ሽንፈት ምክንያት ወደ ሰላድንጋይ ከተማ ሲመለስ መንገድ ላይ ያገኘውን የ14አመት ወጣት የፋኖ ልጅ ነህ በሚል መረሸኑን የኢትዮ 251 የአካባቢው ምንጮች ገልፀዋል ። ከዚህ ቀደም በቡሄ ጅራፍ ደንግጦ ደብረሲና ከተማ ላይ የ12 አመት ህፃን የቀጠፈው የአገዛዙ ሃይል ተመሳሳይ ነውሩንና የጥፋት ዕቅዱን በንፁሃን ህፃናት ላይ እየፈፀመ ይገኛል ። ኢትዮ 251 ሚዲያ የነጻነት አንደበት! https://t.me/ethio251media
Show all...
የድል መረጃ❗️ ❗️❗️❗️💪💪💪💪 የአማራ ፋኖ በጎጃም ሐዲስ አለማየሁ ክፍለ ጦር፤ በአዋበል ወረዳ፤ በቀን 27/12/16 ዓ.ም በለጋ ከተማ በፈጸመው ልዩ ኦፕሬሽን በሦስት FSR መኪና ሲጓጓዝ የነበረን የጠላት ኃይል፣ በቁጥር 56 የሚሆንን ኃይል የደመሰሰ ሲሆን፤ ተሽከርካሪዎችም ወደ አመድነት ተቀይረዋል። በተመሳሳይ፤ በዛሬው እለት ንጋት 11፡00 ስዓት ጀምሮ ሉማሜ ከተማ መሽጎ በተቀመጠ የአገዛዙ ተላላኪ ሰራዊት ካምፕ ድረስ ዘልቆ በመግባት ከ15 በላይ ሚሊሻን በመሸኘት፤ ቀጥራቸው 24 የሚሆኑትን ደግሞ ቁስለኛ በማድረግ አመርቂ ድል ተገኝቷል። በዚህ በተጠና ኦፕሬሽን የሐዲስ አለማየሁ የክፍለጦሩ ብርጌድ አካል የሆኑት አብራጅት ብርጌድ፣ ተድላ ጓድሉ ብርጌድ፣ የየቦቅላ ዓባይ ብርጌድ፣ የአዋበሉ መብረቁ ብርጌድ እና ጥቁር አንበሳ ኮማንዶ በቅንጅት ተሳትፈዋል። ድሉ ይቀጥላል❗️ ድል ለፋኖ❗️ ድል ለአማራ ሕዝብ❗️ ~ፋኖ አስጨንቅ ታደለ ፤ በአማራ ፋኖ በጎጃም ሐዲስ አለማየሁ ክፈለ ጦር ዘመቻ መምሪያ~ ❗️❗️❗️❗️💪💪💪💪
Show all...
Repost from Mulugeta Anberber
“ሕዝቡ በደስታ ተቀብሎናል!” የአማራ ፋኖ መተማ ዮሀንስን ከተቆጣጠረ በኋላ አስተያየታቸውን ከሰጡት የአማራ ፋኖ አመራሮች መካከል የካራማራ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ሻለቃ ወዳጅ አስፋው አንዱ ነው። ከኢትዮ 251 ሚዲያ ለቀለቡለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል። "የብልጽግና ወታደር ከመተማ ዮሀንስ ወደ ሱዳን ለምን ፈረጠጠ" ለሚለው የኢትዮ 251 ጥያቄ፤ "የጠላት ሠራዊት ድሮስ ወደ ጠላት አገር እንጂ ወደ የት ይፈረጥጥ ብለህ ነው? " ሲል ጥያቄያችንን በጥያቄ የመለሰልን ሻለቃ ወዳጅ፤ የብልጽግና ሠራዊት ወደ ሱዳን የፈረጠጠበት ምክንያት፤ ጸረ ኢትዮጵያነቱን ያረጋገጠበት ነው። የመዋጋት ሞራል እንደሌለው የሚያሳይ ነው ያለው ሻለቃ ወዳጅ፤ ራሷ በጦርነት ወደምትናጥ አገር የሚፈረጥጥ ሠራዊት ምን ያህል የመዋጋት ሞራሉ እንደጠፋበት አመላካች ነው" ብሏል። ኢትዮ 251 ሚዲያ ለሻለቃ ወዳጅ ያቀረበችለት ሌላው ጥያቄ፤ "በአሁኑ ሰዓት ሠተማ ዮለንስ በምን ሁኔታ ላይ ትገኛለች? ሕዝቡስ እንዴት ተቀበላችሁ?" የሚል ነበር። ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥም፤ "ከጠበቅነው ቀላይ በደስታ ወጥቶ ተቀብሎናል። 600 ባለመሣሪያ እኛን ተቀላቅሎናል። የሚገርምህ የወረዳው ዓቃቤ ሕግ ፋኖን ተቀላቅሏል። ሕዝቡም ገና ከመግባታችን የደረሰበትን ግፍ አቤቱታ አቅርቦልናል" ሲል ምላሽ ሰጥቷል። ዝርዝሩን በ251 ዛሬ ይጠብቁን። ኢትዮ 251 ሚዲያ የነጻነት አንደበት! https://t.me/ethio251media
Show all...
Repost from Damot News24
ሰበር ዜና ቀን 27/12/2016 የአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ይኩኖአምላክ ክፍለጦር ብሩኬ ደምሴ ብርጌድ አንደኛ ሻለቃ በዋይት ወንዝ የአገዛዙን ሰራዊት በደፈጣ  አራግፎታል። ከግሼራቤል ወርዳ  ራቤል ከተማ ተነስቶ ወደ ወረኢሉ በሁለት መኪና ተጭኖ እየተንቀሳቀሰ የነበረው በዋይት ወንዝ ድልድል አካባቢ ቆላማ ቦታ ላይ በተደረገበት የደፈጣ ውጊያ በሁለት መኪና ተጭኖ የነበረው የወራሪው ጦር ተደምስሷል ። ድል ለአማራ ህዝብ !! ድል ለአማራ ፋኖ !! ከአማራ ፋኖ ሽዋ እዝ ህዝብ ግንኙነት ክፍል @damotnews24
Show all...
00:35
Video unavailableShow in Telegram
በጎንደር የጥቁሩ ፋሽስት ብልጽግና ሰራዊት ህዝብ ላይ እየተኮሰ ነው ❗️❗️❗️ የ 2 አመት ህጻን ኖላዌ ዘገየ በአጋቾች በግፍ ተገድላለች:: ብልጽግና ያደራጃቸው የተባሉ ዘራፊ ቡድኖች አግተው የጠየቁት ገንዘብ ተቀብለው ህጻንዋን በግፍ እንደገደሉ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ያሳያሉ:: ይህን ግፍ ለመቃወም ሰልፍ የወጣው የጎንደር ህዝብ ተኩስ ተከፍቶበታል:: ቪድዮው የዛሬ ሁኔታን ያሳያል The story is under development some facts needs clarification & confirmation. ነሐሴ 27, 2016 ዓ.ም አሽሩካ ኢንፎቴንመንት
Show all...
IMG_7348.MP412.57 MB
02:44
Video unavailableShow in Telegram
ፋኖ ሰለሞን ጋሹ (ሰለሞን ዘባህር ዳር) በሰላም እረፍ! የአማራ ህዝብ መደፈር አንገብግቦት በምቾት ከሚኖርበት ጀርመን ሐገር በመምጣት ፋኖን ተቀላቅሎ በአውደ ውጊያ ላይ የተሰዋው የፋኖ ሰለሞን ጋሹ ዝክር በባህርዳር ዙሪያ በጦሩ ተከብሮ ውሏል!
Show all...
9.43 MB
Repost from Damot News24
ሁለት ጉዳዮች 1) በጨቅላው አብይ አህመድ የሚመራው ፋሽስታዊ ስርዓት በውጊያ አውደ ግንባሮች ያልቻለውን ፋኖን እንደ ስልታዊ የማጥቂያ መንገድ ከወሰዳቸው ነገሮች አንዱ የእርስበርስ መከፋፈልን መፍጠር ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፋኖን ከህዝብ ይነጥልልኛል የሚላቸውን ድርጊቶች (ለምሳሌ እገታ) እራሳቸው ስምሪት በሰጧቸው አካላት መፈፀም ነው። የመጀመሪያው በበዛ የስልጣን ጥምና ኢጎ ምክንያት አገዛዝ ወደሚፈልገው አቅጣጫ ተንቀሳቅሷል። ሁለተኛው ደግሞ ደግሞ በተለይ ባህርዳርና ጎንደር በመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞች መሞከር ከጀመረ ቆየት ብሏል። እኛም በተጨባጭ ማስረጃዎች ላይ ተመስርተን ያለውን የአገዛዙን የውንብድና ሰንሰለት ማጋለጥ ጀምረን ነበር። በተለይ በባህር ዳር ከተማ ስላለው ውንብድና የሰዎቹን ማንነት፣ ገንዘብ የተቀበሉበትን አካውንቶችና መታወቂያቸውን ሳይቀር ማጋለጥ ጀምረን ነበር፤ የነበረው ንፋስ እኛንም ይዞን ሄዶ አቋረጥነው እንጅ። ለማንኛውም ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ላለፉት አንድ ዓመታት የታዮ የውንብድና (የእገታና ዘረፋ ወንጀሎች) ዜሮ በሚባል ደረጃ አልነበሩም ማለት ይቻላል። ችግሩ በስፋት የሚታየው አገዛዙ ተቆጣጥሯቸው ባሉ ከተሞች ላይ ነው። ይህ ብቻ ደግሞ ያለ ተጨማሪ ማስረጃ የውንብድናውን ባለቤት ጠቋሚ ነው። ይህንን የውንብድና ሰንሰለት እየመነጠሩ "እዳሪ" ማስጣት ከወገን የሚዲያ አካላት፣ እርምጃ መውሰድ ደግሞ ከፋኖዎቻችን ይጠበቃል እንላለን። 2) ሌላው ጉዳይ ደግሞ እንደነ አያሌው መንበር ያሉትን የብአዴን ቀደምት የማደጎ ልጆችን ለመቃወም በሚል አማራነትን ያራቀ "የአቻ መንደርተኝነት" አካሄድ ሊገራ ይገባል። ይህ አካሄድ ክፍተትን ይበልጥ የሚያሰፋ እንጅ መፍትሔ የሚሆን አካሄድ አይደለም። አያሌውን መሰል አይጠመጎጥ ቅንጭራሞች ክፍተት ያገኙ ሲመስላቸው በልካቸው ከተሰራች ጉድጓዳቸው ብቅ ብቅ ማለታቸውን ያለፉት ሁለት አስረጅዎች ናቸው። እኩል ጉድጓድ ምሶ፣ ማዶ ለማዶ እንች እናካ መባባሉ a) አንድም እነ አያሌው መንበር የጉድጓድ ተጋሪ የሚያሰባስቡበት በለስ ነው b) ሁለትም አገዛዙም የሚፈልገውን ነገር ነው። የአቻ መንደርተኝነት አካሄድና የመንደርተኝነት አጋፋሪነት ሚዛን ቢያስት እንጅ ለቅንጭራሞች አካሄድ ሚዛን አስጠባቂ ሊሆን ፈፅሞ አይችልም። ስሜታዊነቱና መደማመጥ ማጣቱ የበዛ ቢሆንም፣ እያየነው ላለው ነገር መፍትሔ ግን መንደር ተሻጋሪ የአማራነት አስተሳሰብ ብቻ ነው። የኔ የሆነ ነገር ቅዱስ፣ ያንተ ያንተው ደግሞ እርኩስ የሚለው አካሄድ ልክ አይደለም። የአያሌውንና ቅንጭራም መሰሎቹን አካሄድ በእነሱ መንገድ ሂደህ አትፈታውም። ይህንን የጥቂቶች አካሄድን ባለማስተዋል የምታጋፍሩ ወገኖችም ቆም ብሎ የት ያደርሰናል የሚለውን መመርመሩ መልካም ነው። @BW
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.